+ አክሊልን እንደ አጵሎስ
ወንድማችን አክሊል የአበውን መጻሕፍት በትጋት በማንበብ ራሱን አስተምሮ አስደናቂ የዕቅብተ እምነት ሥራ እንደሠራና በዚህም ለብዙዎች ወደ ኦርቶዶክሳዊት (ርትዕት/ የቀናች) እምነት መመለስ ምክንያት እንደሆነ ይታወቃል፡፡
በቅርቡ ግን ወጣቱ Apologist አክሊል በሚያነሣቸው የነገረ መለኮት እሳቤዎች (theologoumena = ዶግማዊ ውሳኔ ያለተሰጠባቸው አመለካከቶች) ላይ ብዙዎች ጥያቄ ሲያቀርቡና አንዳንዶችም አክሊልን ሲከስሱ ታዝቤአለሁ፡፡ የዚህ ታዳጊ ወጣት አገልግሎት ያስታወሰኝ የሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 18 ውስጥ የምናገኘውን የእስክንድርያ ተወላጁን አጵሎስን ነው፡፡ ጸሐፊው ሉቃስ እንዲህ ከትቦታል፦
የሐዋ ሥራ 18፡ 24 “በወገኑም የእስክንድርያ ሰው የሆነ፣ ነገር አዋቂ የነበረ አጵሎስ የሚሉት አንድ አይሁዳዊ ሰው ወደ ኤፌሶን ወረደ፤ እርሱም በመጻሕፍት እውቀት የበረታ ነበር።
25 እርሱ የጌታን መንገድ የተማረ ነበር፥ የዮሐንስንም ጥምቀት ብቻ አውቆ በመንፈስ ሲቃጠል ስለ ኢየሱስ ይናገርና በትክክል ያስተምር ነበር።
26 እርሱም በምኵራብ ገልጦ ይናገር ጀመር። ጵርስቅላና አቂላም በሰሙት ጊዜ፥ ወስደው የእግዚአብሔርን መንገድ ከፊት ይልቅ በትክክል ገለጡለት።"
አጵሎስ በመጻሕፍት እውቀት የበረታ እንደነበር፣ ወንድማችን አክሊልም የአበውን መጻሕፍት በትጋት በማንበብና የሚያውቀውን በማካፈል ብርቱ ነው፡፡ አጵሎስ በመንፈስ እየተቃጠለ (እንግሊዝኛው "with burning enthusiasm" ይላል) ስለ ኢየሱስ ይናገርና በትክክል ያስተምር እንደነበር፣ አክሊልም ከኦርቶዶክሳውያን አባቶች የተማረውን በትክክል ያስተምር ነበር፡፡
ልዩነቱ ያለው አጵሎስንና አክሊልን ባረሙ (ባቀኑ) ሰዎቸ ላይ ነው፡፡ ባልና ሚስቱ ጵርስቅላና አቂላ የአጵሎስን ቅንዐት (zeal) ተመልክተው፣ አንዳንድ እርማት የሚያስፈልጋቸው ነገሮች እንዳሉ ባስተዋሉ ጊዜ ወደ ቤታቸው ወስደው "የእግዚአብሔርን መንገድ ከፊት ይልቅ በትክክል ገለጡለት" እንጂ አልከሰሱትም፤ አላወገዙትም፡፡
እኛም ለወንድማችን አክሊል ልናደርግ የሚገባው ይህንኑ ነው፡፡ በተሻለ መልኩ በጥበብ ሊቀርቡ የሚገባቸው አስተምህሮዎች ካሉ አክሊልን በፍቅር እናቅናው እንጂ፣ አናውግዘው፡፡ አንዳንድ ጽንፈኞች ስም እያጠፉ በማስደንበር ከኦርቶዶክሳዊት በረት ያስኮበለሏቸው በጎች ብዙዎች ናቸውና ያለፈው ጥፋት ይበቃል!
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
@dnzema
@dnzema
@dnzema
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯
ወንድማችን አክሊል የአበውን መጻሕፍት በትጋት በማንበብ ራሱን አስተምሮ አስደናቂ የዕቅብተ እምነት ሥራ እንደሠራና በዚህም ለብዙዎች ወደ ኦርቶዶክሳዊት (ርትዕት/ የቀናች) እምነት መመለስ ምክንያት እንደሆነ ይታወቃል፡፡
በቅርቡ ግን ወጣቱ Apologist አክሊል በሚያነሣቸው የነገረ መለኮት እሳቤዎች (theologoumena = ዶግማዊ ውሳኔ ያለተሰጠባቸው አመለካከቶች) ላይ ብዙዎች ጥያቄ ሲያቀርቡና አንዳንዶችም አክሊልን ሲከስሱ ታዝቤአለሁ፡፡ የዚህ ታዳጊ ወጣት አገልግሎት ያስታወሰኝ የሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 18 ውስጥ የምናገኘውን የእስክንድርያ ተወላጁን አጵሎስን ነው፡፡ ጸሐፊው ሉቃስ እንዲህ ከትቦታል፦
የሐዋ ሥራ 18፡ 24 “በወገኑም የእስክንድርያ ሰው የሆነ፣ ነገር አዋቂ የነበረ አጵሎስ የሚሉት አንድ አይሁዳዊ ሰው ወደ ኤፌሶን ወረደ፤ እርሱም በመጻሕፍት እውቀት የበረታ ነበር።
25 እርሱ የጌታን መንገድ የተማረ ነበር፥ የዮሐንስንም ጥምቀት ብቻ አውቆ በመንፈስ ሲቃጠል ስለ ኢየሱስ ይናገርና በትክክል ያስተምር ነበር።
26 እርሱም በምኵራብ ገልጦ ይናገር ጀመር። ጵርስቅላና አቂላም በሰሙት ጊዜ፥ ወስደው የእግዚአብሔርን መንገድ ከፊት ይልቅ በትክክል ገለጡለት።"
አጵሎስ በመጻሕፍት እውቀት የበረታ እንደነበር፣ ወንድማችን አክሊልም የአበውን መጻሕፍት በትጋት በማንበብና የሚያውቀውን በማካፈል ብርቱ ነው፡፡ አጵሎስ በመንፈስ እየተቃጠለ (እንግሊዝኛው "with burning enthusiasm" ይላል) ስለ ኢየሱስ ይናገርና በትክክል ያስተምር እንደነበር፣ አክሊልም ከኦርቶዶክሳውያን አባቶች የተማረውን በትክክል ያስተምር ነበር፡፡
ልዩነቱ ያለው አጵሎስንና አክሊልን ባረሙ (ባቀኑ) ሰዎቸ ላይ ነው፡፡ ባልና ሚስቱ ጵርስቅላና አቂላ የአጵሎስን ቅንዐት (zeal) ተመልክተው፣ አንዳንድ እርማት የሚያስፈልጋቸው ነገሮች እንዳሉ ባስተዋሉ ጊዜ ወደ ቤታቸው ወስደው "የእግዚአብሔርን መንገድ ከፊት ይልቅ በትክክል ገለጡለት" እንጂ አልከሰሱትም፤ አላወገዙትም፡፡
እኛም ለወንድማችን አክሊል ልናደርግ የሚገባው ይህንኑ ነው፡፡ በተሻለ መልኩ በጥበብ ሊቀርቡ የሚገባቸው አስተምህሮዎች ካሉ አክሊልን በፍቅር እናቅናው እንጂ፣ አናውግዘው፡፡ አንዳንድ ጽንፈኞች ስም እያጠፉ በማስደንበር ከኦርቶዶክሳዊት በረት ያስኮበለሏቸው በጎች ብዙዎች ናቸውና ያለፈው ጥፋት ይበቃል!
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
@dnzema
@dnzema
@dnzema
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯