Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ድኻ ጠሉ በጋሻው ደሳለኝ!
"የድኾችን ጩኸት ለመስማት ፈቃደኛ ያልሆነ ሰው እርሱም ተቸግሮ በሚጮኽበት ጊዜ የሚረዳው አያገኝም።" (ምሳ. 21፥13)
በተቸገርን ጊዜ እግዚአብሔር አምላክ ጸሎታችንን ይሰማን ዘንድ፣ የወገኖቻችንን ችግር በመስማት በፍቅር ልንደርስላቸው ይገባል። ጌታችን ኢየሱስ የታረዘውን ስናለብስ ርሱን እንዳለበስን እንደሚቆጥር በግልጥ ተናግሮአል፤ (ማቴ. 25፥40)። በአዲስ ኪዳን የጥበብ መጽሐፍም እንዲህ ይላል፣ “የእግዚአብሔር ፍርድ ምሕረት ለማያደርግ ሰው ምሕረት አያደርግም፤ ሆኖም ምሕረት ፍርድን ያሸንፋል።”(ያዕ. 2፥13)።
እግዚአብሔር ምሕረት የሚያደርገው፣ ለሚምሩና ለሚራሩ ነው። የሚምሩ ምስጉኖች ናቸው ፍጹም ይማራሉና እንዲል። ስለ ድኾች የጌታ ትምህርት አጭርና ግልጽ ነው። ለኹል ጊዜ ከእኛ ጋር አብረውን እንዳሉ፤ ደግሞም ይኖራሉ።“ድሆችስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ይኖራሉና”(ዮሐ. 12፥8) እንዲል። ድኾች ቤት ፈርሶባቸው ቢጮኹና ቢያለቅሱ ቅንጦት ወይም አዚም ተደርጎባቸው አይደለም። አልያ ድኾች መሻሻል የሚጠሉ፤ ድህነት ወይም ችጋር ወይም ሰቆቃ እንደ ዕጣ ፈንታ የተጣባቸው አይደሉም። ማንም ልማት የሚጠላ ጤነኛ ሰው የለም፤ ቁስ ግን የቱንም ያህል ቢጌጥና ቢያምር፣ ሰውን ካልጠቀመ፤ ለእግዚአብሔር ክብር ካልኾነ፤ ከንቱ የከንቱ ከንቱ ነው!
ስለ አንዳንድ "ወንጌላውያን" ነን ስለሚሉ አገልጋዮች አዝናለኹ። ከኦርቶዶክስ ያልተማሩ "አዚማሞች" ናቸው። ትላንት ኦርቶዶክስ መንግሥትን ተጠግታ የሠራችውን ስህተት እነርሱ ዛሬ በአደባባይ በብዙ ማስረጃ ፊት ይፈጽሙታል። ለምን መከራ ታጎመሩልናላችኹ? እንደ ከረመ ወይን ለምን መከራ ታሰነብቱልናችሁ? ለተጣለላችኹ ቅልጥም እዚያው ለፍልፉ እንጂ በወንጌል ታክካችኹ መጥታችኹ ወንጌሉን በማያምኑ ዘንድ አታሰድቡ፤ ለደካሞችም የማሰናከያ ዐለት አታኑሩ!
"የድኾችን ጩኸት ለመስማት ፈቃደኛ ያልሆነ ሰው እርሱም ተቸግሮ በሚጮኽበት ጊዜ የሚረዳው አያገኝም።" (ምሳ. 21፥13)
በተቸገርን ጊዜ እግዚአብሔር አምላክ ጸሎታችንን ይሰማን ዘንድ፣ የወገኖቻችንን ችግር በመስማት በፍቅር ልንደርስላቸው ይገባል። ጌታችን ኢየሱስ የታረዘውን ስናለብስ ርሱን እንዳለበስን እንደሚቆጥር በግልጥ ተናግሮአል፤ (ማቴ. 25፥40)። በአዲስ ኪዳን የጥበብ መጽሐፍም እንዲህ ይላል፣ “የእግዚአብሔር ፍርድ ምሕረት ለማያደርግ ሰው ምሕረት አያደርግም፤ ሆኖም ምሕረት ፍርድን ያሸንፋል።”(ያዕ. 2፥13)።
እግዚአብሔር ምሕረት የሚያደርገው፣ ለሚምሩና ለሚራሩ ነው። የሚምሩ ምስጉኖች ናቸው ፍጹም ይማራሉና እንዲል። ስለ ድኾች የጌታ ትምህርት አጭርና ግልጽ ነው። ለኹል ጊዜ ከእኛ ጋር አብረውን እንዳሉ፤ ደግሞም ይኖራሉ።“ድሆችስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ይኖራሉና”(ዮሐ. 12፥8) እንዲል። ድኾች ቤት ፈርሶባቸው ቢጮኹና ቢያለቅሱ ቅንጦት ወይም አዚም ተደርጎባቸው አይደለም። አልያ ድኾች መሻሻል የሚጠሉ፤ ድህነት ወይም ችጋር ወይም ሰቆቃ እንደ ዕጣ ፈንታ የተጣባቸው አይደሉም። ማንም ልማት የሚጠላ ጤነኛ ሰው የለም፤ ቁስ ግን የቱንም ያህል ቢጌጥና ቢያምር፣ ሰውን ካልጠቀመ፤ ለእግዚአብሔር ክብር ካልኾነ፤ ከንቱ የከንቱ ከንቱ ነው!
ስለ አንዳንድ "ወንጌላውያን" ነን ስለሚሉ አገልጋዮች አዝናለኹ። ከኦርቶዶክስ ያልተማሩ "አዚማሞች" ናቸው። ትላንት ኦርቶዶክስ መንግሥትን ተጠግታ የሠራችውን ስህተት እነርሱ ዛሬ በአደባባይ በብዙ ማስረጃ ፊት ይፈጽሙታል። ለምን መከራ ታጎመሩልናላችኹ? እንደ ከረመ ወይን ለምን መከራ ታሰነብቱልናችሁ? ለተጣለላችኹ ቅልጥም እዚያው ለፍልፉ እንጂ በወንጌል ታክካችኹ መጥታችኹ ወንጌሉን በማያምኑ ዘንድ አታሰድቡ፤ ለደካሞችም የማሰናከያ ዐለት አታኑሩ!