የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር የመድረክ ቴአትሮችን ለተመልካች ማቅረብ ሊጀምር ነው!
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር የኮቪድ-19 መከላከል መመሪያን ተግባራዊ ባደረገ መልኩ በሚቀጥለው ሳምንት የመድረክ ቴአትሮችን ለተመልካች ማቅረብ ሊጀምር መሆኑን አስታውቋል።
ቴአትር ቤቱ በአንድ ጊዜ 1 ሺህ 200 ተመልካቾችን የመያዝ አቅም ቢኖረውም አሁን ላይ በአንድ ጊዜ 300 ተመልካቾች ብቻ ይስተናገዳሉ ሲሉ የቴአትር ቤቱ የቴአትር ክፍል ዳይሬክተር ደስታ አስረስ ገልጸዋል።
“ተመልካቾች ወደ ቴአትር ቤት ሲመጡ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል በማድረግ፣ ሳኒታይዘር በመጠቀም እና ተራርቆ በመቀመጥ እንዲመለከቱ ይገደዳሉ” ብለዋል።
ከታህሣሥ 7 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ቴአትር ቤቱ ለተመልካች ክፍት ሆኖ በሳምንት ሶስት ቴአትሮችን ለማሳየት ዝግጅት መደረጉንም ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል። (ENA)
@ebs_official @ebs_official
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር የኮቪድ-19 መከላከል መመሪያን ተግባራዊ ባደረገ መልኩ በሚቀጥለው ሳምንት የመድረክ ቴአትሮችን ለተመልካች ማቅረብ ሊጀምር መሆኑን አስታውቋል።
ቴአትር ቤቱ በአንድ ጊዜ 1 ሺህ 200 ተመልካቾችን የመያዝ አቅም ቢኖረውም አሁን ላይ በአንድ ጊዜ 300 ተመልካቾች ብቻ ይስተናገዳሉ ሲሉ የቴአትር ቤቱ የቴአትር ክፍል ዳይሬክተር ደስታ አስረስ ገልጸዋል።
“ተመልካቾች ወደ ቴአትር ቤት ሲመጡ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል በማድረግ፣ ሳኒታይዘር በመጠቀም እና ተራርቆ በመቀመጥ እንዲመለከቱ ይገደዳሉ” ብለዋል።
ከታህሣሥ 7 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ቴአትር ቤቱ ለተመልካች ክፍት ሆኖ በሳምንት ሶስት ቴአትሮችን ለማሳየት ዝግጅት መደረጉንም ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል። (ENA)
@ebs_official @ebs_official