የአሜሪካ እና ዩክሬን ከፍተኛ ባለስልጣናት በሳኡዲ አረቢያ ተገናኝተው ሊመክሩ ነው
የአሜሪካ እና የዩክሬን ከፍተኛ ባለስልጣናት ልዑካን ቡድን ጦርነቱን ለማስቆም አላማውን ያረገ ውይይት በነገው ዕለት በሳኡዲአረብያ ያካሄዳል፡፡
ባለፈው ወር በፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና በዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮለዲሚር ዘለንስኪ መካከል የተደረገው ውይይት ወደ ውዝግብ ከተቀየረ በኋላ ዩክሬናውያን ከትራምፕ አስተዳደር ጋር ያላቸውን ግንኙነት ለማሻሻል ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳዩ ምልክቶችን የአሜሪካ ልዑካን እንደሚከታተሉ ተነግሯል፡፡
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርክ ሩብዮ ፣ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪው ማይክ ዋልትዝ እና የመካከለኛው ምስራቅ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ለጉባኤው ወደ ጂዳ አቅንተዋል፡፡ሮይተርስ ከልዑካን ቡድኑ አባላት መካከል ስማቸውን ያልጠቀሳቸው አንድ ባለስልጣን ዩክሬናውን ከ2014 እና 2022 ድንበር ጥያቄ ባለፈ ለሰላም ያላቸውን ቁርጠኝነት መመልከት እንፈልጋለን ብለዋል፡፡
የትራምፕ አስተዳደር ኪቭ ከሞስኮ ጋር ሰላም መፍጠር የምትፈልግ ከሆነ አንዳንድ የግዛት ጥያቄዎችን መተው እንደሚኖርባት ሲናገር በተደጋጋሚ ተደምጧል፡፡የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትላንትናው ዕለት ለጋዜጠኞች ባደረጉት ንግግር ከነገው የከፍተኛ ባለስልጣንት ውይይት ፍሬያማ ውጤት እንደሚጠብቁ ተናግረዋል፡፡በዛሬው ዕለት ወደ ሳዑዲ ያቀኑት የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮለድሚር ዘለንስኪ በበኩላቸው “ሰላምን ለማስፈን የማደርገውን ጥረት ለመቀጠል ወደ ሳኡዲ እጓዛለሁ” ብለዋል፡፡
ዘለንስኪ የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ሰላምን እንደማይፈልጉ እና ሩሲያ በዩክሬን ላይ በጀመረችው ጦርነት ግልፅ የሆነ ሽንፈት ካላስተናገደች ሌሎች የአውሮፓ ሀገራትን ታጠቃለች ሲሉ ተናግረዋል፡፡አውሮፓውን የዩክሬን አጋሮች ደግሞ ኪቭ ከሩስያ ጋር ለመደራደር ጠንካራ ቁመና ላይ መሆን እንደሚገባት እና ወደ ድርድር ጠረጴዛ እንድትገባ ግፊት ሊደረግባት እንደማይገባ ያነሳሉ፡፡ ትራምፕ በበኩላቸው ምስራቃዊ አውሮፓዊቷ ሀገር የሰው ሀይል እና ሃብት እየመነመነ እንደሚገኝ አሳስበው ከሩሲያ ጋር ለመስማማት በፍጥነት ወደ ጠረጴዛው መምጣት እንደሚኖርባት አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
የአሜሪካ እና የዩክሬን ከፍተኛ ባለስልጣናት ልዑካን ቡድን ጦርነቱን ለማስቆም አላማውን ያረገ ውይይት በነገው ዕለት በሳኡዲአረብያ ያካሄዳል፡፡
ባለፈው ወር በፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና በዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮለዲሚር ዘለንስኪ መካከል የተደረገው ውይይት ወደ ውዝግብ ከተቀየረ በኋላ ዩክሬናውያን ከትራምፕ አስተዳደር ጋር ያላቸውን ግንኙነት ለማሻሻል ያላቸውን ቁርጠኝነት የሚያሳዩ ምልክቶችን የአሜሪካ ልዑካን እንደሚከታተሉ ተነግሯል፡፡
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርክ ሩብዮ ፣ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪው ማይክ ዋልትዝ እና የመካከለኛው ምስራቅ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ለጉባኤው ወደ ጂዳ አቅንተዋል፡፡ሮይተርስ ከልዑካን ቡድኑ አባላት መካከል ስማቸውን ያልጠቀሳቸው አንድ ባለስልጣን ዩክሬናውን ከ2014 እና 2022 ድንበር ጥያቄ ባለፈ ለሰላም ያላቸውን ቁርጠኝነት መመልከት እንፈልጋለን ብለዋል፡፡
የትራምፕ አስተዳደር ኪቭ ከሞስኮ ጋር ሰላም መፍጠር የምትፈልግ ከሆነ አንዳንድ የግዛት ጥያቄዎችን መተው እንደሚኖርባት ሲናገር በተደጋጋሚ ተደምጧል፡፡የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በትላንትናው ዕለት ለጋዜጠኞች ባደረጉት ንግግር ከነገው የከፍተኛ ባለስልጣንት ውይይት ፍሬያማ ውጤት እንደሚጠብቁ ተናግረዋል፡፡በዛሬው ዕለት ወደ ሳዑዲ ያቀኑት የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮለድሚር ዘለንስኪ በበኩላቸው “ሰላምን ለማስፈን የማደርገውን ጥረት ለመቀጠል ወደ ሳኡዲ እጓዛለሁ” ብለዋል፡፡
ዘለንስኪ የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ሰላምን እንደማይፈልጉ እና ሩሲያ በዩክሬን ላይ በጀመረችው ጦርነት ግልፅ የሆነ ሽንፈት ካላስተናገደች ሌሎች የአውሮፓ ሀገራትን ታጠቃለች ሲሉ ተናግረዋል፡፡አውሮፓውን የዩክሬን አጋሮች ደግሞ ኪቭ ከሩስያ ጋር ለመደራደር ጠንካራ ቁመና ላይ መሆን እንደሚገባት እና ወደ ድርድር ጠረጴዛ እንድትገባ ግፊት ሊደረግባት እንደማይገባ ያነሳሉ፡፡ ትራምፕ በበኩላቸው ምስራቃዊ አውሮፓዊቷ ሀገር የሰው ሀይል እና ሃብት እየመነመነ እንደሚገኝ አሳስበው ከሩሲያ ጋር ለመስማማት በፍጥነት ወደ ጠረጴዛው መምጣት እንደሚኖርባት አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ