Alert News ‼️
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር፣ የትግራይ ጸጥታ ኃይል አባላት በደቡባዊ ምሥራቅ ዞን ሰሓርቲ ወረዳ አዲስ ዓለም በተባለ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር በነዋሪዎች ላይ ጥቃት አድርሰዋል በማለት ዛሬ ባወጣው መግለጫ ድርጊቱን አውግዟል።
ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ የተወሰኑ የክልሉ ጸጥታ ኃይል አመራሮች የጊዚያዊ አስተዳደሩን መዋቅሮች ለማፍረስ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ናቸው በማለት ከሷል። ጸጥታ ኃይሉ የአንድ ቡድን የሥልጣን መወጣጫ መሳሪያ ሊኾን እንደማይችል የገለጠው ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ኹኔታዎች በዚህ ከቀጠሉ ክልሉ ከባድ ቀውስ ሊገባ ይችላል በማለት አስጠንቅቋል።
ጊዜያዊ አስተዳደሩ ይህን ያለው፣ ትናንት የተወሰኑ የጸጥታ ኃይል አባላት የቀበሌ አስተዳደሩ ማኅተሙን እንዲያስረክቡ ባስገደዱበትና፣ በዚሁ ወቅት ድርጊቱን በተቃወሙ ነዋሪዎች ላይ የኃይል ርምጃ በወሰዱበት ወቅት እንደኾነ ተገልጧል ።
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር፣ የትግራይ ጸጥታ ኃይል አባላት በደቡባዊ ምሥራቅ ዞን ሰሓርቲ ወረዳ አዲስ ዓለም በተባለ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር በነዋሪዎች ላይ ጥቃት አድርሰዋል በማለት ዛሬ ባወጣው መግለጫ ድርጊቱን አውግዟል።
ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ የተወሰኑ የክልሉ ጸጥታ ኃይል አመራሮች የጊዚያዊ አስተዳደሩን መዋቅሮች ለማፍረስ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ናቸው በማለት ከሷል። ጸጥታ ኃይሉ የአንድ ቡድን የሥልጣን መወጣጫ መሳሪያ ሊኾን እንደማይችል የገለጠው ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ኹኔታዎች በዚህ ከቀጠሉ ክልሉ ከባድ ቀውስ ሊገባ ይችላል በማለት አስጠንቅቋል።
ጊዜያዊ አስተዳደሩ ይህን ያለው፣ ትናንት የተወሰኑ የጸጥታ ኃይል አባላት የቀበሌ አስተዳደሩ ማኅተሙን እንዲያስረክቡ ባስገደዱበትና፣ በዚሁ ወቅት ድርጊቱን በተቃወሙ ነዋሪዎች ላይ የኃይል ርምጃ በወሰዱበት ወቅት እንደኾነ ተገልጧል ።
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news