ዩኒቨርሲቲዎች እውነተኛ የመማሪያ፣ የማስተማሪያ እንዲሁም ጥናትና ምርምሮች የሚሰሩባቸው ትክክለኛ የእውቀት መፈለጊያ ሰላማዊ ቦታዎች ሊሆኑ ይገባል። ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
-------------------------------------
(የካቲት 27/2017 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስትሩ ኘሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በወለጋ ዩኒቨርስቲ በመገኘት ከዩኒቨርስቲው አመራሮችና ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት አድርገዋል ።
በዚሁ ወቅት ዩኒቨርሲቲዎች እውነተኛ የመማሪያ፣ የማስተማሪያ እንዲሁም ጥናትና ምርምሮች የሚሰሩባቸው ትክክለኛ የእውቀት መፈለጊያ ሰላማዊ ቦታዎች ሊሆኑ ይገባል፤ ለዚህም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ እየተተገበሩ ያሉ የሪፎሮም ሥራዎች አላማ ይህን ለማሳካት መሆኑን ገልፀዋል።
በዚህም የዩኒቨርሲቲዎችን አስተዳደር፣ አስተሳሰብና አጠቃላይ ባህል መቀየር አስፈላጊ በመሆኑ የዩኒቨርቲውን አመራር የመቀየር ሥራ መሰራቱን ጠቅሰዋል።
ዩኒቨርሲቲዎች የአካባቢያቸውን ፀጋ በመለየት ጥናትና ምርምሮችን በማድረግ የህብረተሰቡን ህይወት መቀየር እና ለሀገራቸው ችግር መፍትሔ መፈለግ ይገባቸዋል ያሉ ሲሆን በዚህ ረገድ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://www.facebook.com/share/p/1YPrspy2UE/
-------------------------------------
(የካቲት 27/2017 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስትሩ ኘሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በወለጋ ዩኒቨርስቲ በመገኘት ከዩኒቨርስቲው አመራሮችና ማህበረሰብ አባላት ጋር ውይይት አድርገዋል ።
በዚሁ ወቅት ዩኒቨርሲቲዎች እውነተኛ የመማሪያ፣ የማስተማሪያ እንዲሁም ጥናትና ምርምሮች የሚሰሩባቸው ትክክለኛ የእውቀት መፈለጊያ ሰላማዊ ቦታዎች ሊሆኑ ይገባል፤ ለዚህም በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ እየተተገበሩ ያሉ የሪፎሮም ሥራዎች አላማ ይህን ለማሳካት መሆኑን ገልፀዋል።
በዚህም የዩኒቨርሲቲዎችን አስተዳደር፣ አስተሳሰብና አጠቃላይ ባህል መቀየር አስፈላጊ በመሆኑ የዩኒቨርቲውን አመራር የመቀየር ሥራ መሰራቱን ጠቅሰዋል።
ዩኒቨርሲቲዎች የአካባቢያቸውን ፀጋ በመለየት ጥናትና ምርምሮችን በማድረግ የህብረተሰቡን ህይወት መቀየር እና ለሀገራቸው ችግር መፍትሔ መፈለግ ይገባቸዋል ያሉ ሲሆን በዚህ ረገድ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://www.facebook.com/share/p/1YPrspy2UE/