በአማራ ክልል ውጊያ የመቀጠል አሳሳቢነት
ከአንድ ሳምንት ቀደም ብሎ በአማራ ክልል ከባድ ጦርነት መቀስቀሱ የተነገረ ሲሆን፣ አሁንም ድረስ መቀጠሉ በሰፊው ይሰማል፡፡ የፋኖ ኃይሎች ‹‹ዘመቻ አንድነት›› ያሉትን ጥቃት በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ላይ መክፈታቸው እየተነገረ ሲሆን፣ መንግሥትም በአፀፋው በታጣቂዎቹ ላይ ዘመቻ መጀመሩ ይነገራል፡፡ በጎንደር፣ በጎጃም፣ በሸዋና በወሎ የተለያዩ አካባቢዎች የጥይት ጩኸት መሰማቱ እንደቀጠለ መሆኑን የአካባቢው ምንጮችም ያረጋግጣሉ፡፡
መከላከያ ሠራዊት ባለፈው ሳምንት መገባደጃ ይፋ ባደረገው መግለጫም፣ በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ምግበይ ኃይለ በተባሉት በትግራይ ሠራዊት ጄኔራል ሥልጠናና ዕገዛ ጥቃት ከፍተውብናል ሲል መግለጹ፣ የአማራ ክልል ቀውስ ወደ ትግራይም ተሻገረ እንዴ የሚል ጥያቄን ያጫረ ነበር፡፡ በአማራ ክልል የተጠናከረውን ውጊያ በማቀነባበር የተወነጀሉት ብርጋዴር ጄኔራል ምግበይ ኃይለ ግን፣ በወቅቱ በሰጡት መግለጫ ከፕሪቶሪያ ውል ውጪ የሚደረግ እንቅስቃሴ በትግራይ በኩል የለም ብለዋል።
ምንጭ፡ ሪፖርተር
ከአንድ ሳምንት ቀደም ብሎ በአማራ ክልል ከባድ ጦርነት መቀስቀሱ የተነገረ ሲሆን፣ አሁንም ድረስ መቀጠሉ በሰፊው ይሰማል፡፡ የፋኖ ኃይሎች ‹‹ዘመቻ አንድነት›› ያሉትን ጥቃት በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ላይ መክፈታቸው እየተነገረ ሲሆን፣ መንግሥትም በአፀፋው በታጣቂዎቹ ላይ ዘመቻ መጀመሩ ይነገራል፡፡ በጎንደር፣ በጎጃም፣ በሸዋና በወሎ የተለያዩ አካባቢዎች የጥይት ጩኸት መሰማቱ እንደቀጠለ መሆኑን የአካባቢው ምንጮችም ያረጋግጣሉ፡፡
መከላከያ ሠራዊት ባለፈው ሳምንት መገባደጃ ይፋ ባደረገው መግለጫም፣ በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ምግበይ ኃይለ በተባሉት በትግራይ ሠራዊት ጄኔራል ሥልጠናና ዕገዛ ጥቃት ከፍተውብናል ሲል መግለጹ፣ የአማራ ክልል ቀውስ ወደ ትግራይም ተሻገረ እንዴ የሚል ጥያቄን ያጫረ ነበር፡፡ በአማራ ክልል የተጠናከረውን ውጊያ በማቀነባበር የተወነጀሉት ብርጋዴር ጄኔራል ምግበይ ኃይለ ግን፣ በወቅቱ በሰጡት መግለጫ ከፕሪቶሪያ ውል ውጪ የሚደረግ እንቅስቃሴ በትግራይ በኩል የለም ብለዋል።
ምንጭ፡ ሪፖርተር