በወ/ሮ ሙሉ ግርማይ የተመሰረተው ላይፍ ሴንተር ነገ የገቢ ማሰባሰብያ ሊያካሄድ ነው
#FastMereja I ላይፍ ሴንተር ኢትዮጵያ የድርጅቱ መስራች ወ/ሮ ሙሉ ግርማይ በስደት ከሚኖሩበት አሜሪካን ሀገር ወደ ኢትዮጵያ ቤተሰብ ለመጠየቅ በመጡበት ወቅት የወላጅ አልባ ህፃናትንና የችግረኛ እናቶችን አስቸጋሪ ህይወት በመመልከት እራሳቸው ያለፉበትን የህይወት ፈተና በማስታወስ ወገኖቻችንን ለመርዳት በ2005 ዓ/ም የተመሰረተ የበጎ አድራጎት ድርጅት ሲሆን ላለፉት 12 ዓመታት ወላጅ አልባ ህፃናትንና መበለቶችን እየረዳ የቀጥለ ድርጅት ነው::
በጥቂት ህጻናት ብቻ የጀመሩት የስፖንሰርሺፕ እርዳታ ፕሮግራም አሁን ከ345 የሚበልጡ ወላጅ አልባ ህፃናትን የተመጣጠነ ምግብ፣ ልብስ፣ የትምህርት መርጃ መሣሪያዎችንና የመሳሰሉትን እያቀረበ የህይወት ክህሎት ስልጠና እና የምክር አገልግሎት እየሰጠ መልካም ዜጋን ለማፍራት አስተዋፅኦ እያደረገ ያለ ድርጅት መሆኑ ተገልጿል።
እንዲሁም ከ919 ለሚበልጡ መበለቶች የቢዝነስ ክህሎት ስልጠና በመስጠት: የአነስተኛ ብድር አገልግሎት ተጠቃሚ በማድረግ ላይ ይገኛል::
በአሁኑ ጊዜ እርዳታ የሚፈልጉ ወገኖቻችን ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመሄዱ፣ ላይፍ ሴንተር የአገልግሎቱን አድማስ በማስፋት ለብዙዎች ተደራሽ መሆን ይፈልጋል ያሉ ሲሆን ይህንን የተቀደስ ህልማችንን እውን ለማድረግ የወገኖቻችን ዕርዳታ ለመጠየቅ ዓመታዊ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር ነገ መጋቢት 4 ቀን 2017 በሂልተን ሆቴል መዘጋጀቱ ተገልጿል።
በዛሬው እለትም አርቲስት ልያት ስዩም የላይፍ ሴንተር የበጎ ፍቃድ አምባሳደር ተደርጋ ተሹማለች።
የላይፍ ሴንተር የበጎ ፍቃድ አምባሳደር ሆና የተሾመችው አርቲስት ልያት ስዩም የበጎ ፍቃድ አምባሳደርነቱ ለሁለት አመታት የሚቆይ ሲሆን ተቋሙን በተለያዩ ስራዎች የምታገለግል ይሆናል።
#FastMereja I ላይፍ ሴንተር ኢትዮጵያ የድርጅቱ መስራች ወ/ሮ ሙሉ ግርማይ በስደት ከሚኖሩበት አሜሪካን ሀገር ወደ ኢትዮጵያ ቤተሰብ ለመጠየቅ በመጡበት ወቅት የወላጅ አልባ ህፃናትንና የችግረኛ እናቶችን አስቸጋሪ ህይወት በመመልከት እራሳቸው ያለፉበትን የህይወት ፈተና በማስታወስ ወገኖቻችንን ለመርዳት በ2005 ዓ/ም የተመሰረተ የበጎ አድራጎት ድርጅት ሲሆን ላለፉት 12 ዓመታት ወላጅ አልባ ህፃናትንና መበለቶችን እየረዳ የቀጥለ ድርጅት ነው::
በጥቂት ህጻናት ብቻ የጀመሩት የስፖንሰርሺፕ እርዳታ ፕሮግራም አሁን ከ345 የሚበልጡ ወላጅ አልባ ህፃናትን የተመጣጠነ ምግብ፣ ልብስ፣ የትምህርት መርጃ መሣሪያዎችንና የመሳሰሉትን እያቀረበ የህይወት ክህሎት ስልጠና እና የምክር አገልግሎት እየሰጠ መልካም ዜጋን ለማፍራት አስተዋፅኦ እያደረገ ያለ ድርጅት መሆኑ ተገልጿል።
እንዲሁም ከ919 ለሚበልጡ መበለቶች የቢዝነስ ክህሎት ስልጠና በመስጠት: የአነስተኛ ብድር አገልግሎት ተጠቃሚ በማድረግ ላይ ይገኛል::
በአሁኑ ጊዜ እርዳታ የሚፈልጉ ወገኖቻችን ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመሄዱ፣ ላይፍ ሴንተር የአገልግሎቱን አድማስ በማስፋት ለብዙዎች ተደራሽ መሆን ይፈልጋል ያሉ ሲሆን ይህንን የተቀደስ ህልማችንን እውን ለማድረግ የወገኖቻችን ዕርዳታ ለመጠየቅ ዓመታዊ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር ነገ መጋቢት 4 ቀን 2017 በሂልተን ሆቴል መዘጋጀቱ ተገልጿል።
በዛሬው እለትም አርቲስት ልያት ስዩም የላይፍ ሴንተር የበጎ ፍቃድ አምባሳደር ተደርጋ ተሹማለች።
የላይፍ ሴንተር የበጎ ፍቃድ አምባሳደር ሆና የተሾመችው አርቲስት ልያት ስዩም የበጎ ፍቃድ አምባሳደርነቱ ለሁለት አመታት የሚቆይ ሲሆን ተቋሙን በተለያዩ ስራዎች የምታገለግል ይሆናል።