Фильтр публикаций


በዛሬው እለት ከ24 ድርጅቶች እና 3 ግለሰቦች በድምሩ 6,700,000 ብር መቅጣቱን ገለፀ።

#FastMereja I የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ጋር በመተባበር ፍሳሽ ቆሻሻ ወደ ወንዝ የለቀቁ ድርጅቶችና ግለሰቦችን በደንብ ቁጥር 180/2017 መሰረት የገንዘብ ቅጣቶች በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱ ገለጸ፡፡

ባለስልጣኑ በዛሬው እለት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ 1,800,000 ብር፣ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ 1,750,000 ብር፣ በአራዳ ክፍለ ከተማ 1,200,000 ብር፣በጉለሌ ክፍለ ከተማ 600,000 ብር ፣ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ 400,000 ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል።

በተያያዘ ዜና በቦሌ ክ/ከተማ 450,000 ብር በኮልፌ ክ/ከተማ 400,000 ብር ፤በልደታ ክፍለ ከተማ 100,000 ብር በመቅጣት አስተዳደራዊ እርምጃ በመውሰድ ለመንግስት ገቢ አድርጓል።

ባለስልጣኑ በአጠቃላይ በዛሬው እለት 24 ጅርጅቶች እና 3 ግለሰቦች በድምሩ 6,700,000/ስድስት ሚሊየን ሰባት መቶ ሺህ/ ብር መቅጣቱ ገልጿል።

መረጃው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን


#ዓለም ላይ እርሱን የመሰለ ጠቢብ ፈጽሞ አይነሳም 

እስከ ዓለም ፍጻሜ በተሰጠው ጥበብ እርሱን የሚመስል ከሰው ልጅ ወገን እንደማይነሳ ይነገርለታል፡፡ መፍቀሬ ጥበብ፣ ጠቢበ ጠቢባን፣ ንጉሠ እሥራኤል፣ የጽድቅ ነቢየ፣ ሰላማዊው ንጉስ እየተባለ ይጠራል፡፡ አባቱ ታላቁ ነቢይና ንጉሥ ልበ አምላክ ቅዱስ_ዳዊት ነው፡፡ እናቱ ደግሞ ቤርሳቤህ ወይም ቤትስባ ትባላለች፡፡ ከ3ሺ ዓመታት በፊት የተወለደው ቅዱስ ሰሎሞን እስከ 12 ዓመቱ ድረስ በቤተ መንግሥት ከአባቱ ጋር አድጓል፡፡ ቅዱስ ዳዊት 70 ዘመን በሞላው ጊዜ የአካሉን መድከም አይቶ አዶንያስ በጉልበት እነግሣለሁ ቢልም አልተሳካለትም:: እግዚአብሔር ሰሎሞንን መርጧልና ገና በ12 ዓመቱ ነገሠ:: ልበ አምላክ አባቱ ዳዊት ነፍሱ ከሥጋው ከመለየቷ በፊት መከረው:: "ልጄ ሆይ! ልብህን ስጠኝ:: ፈጣሪህንም አምልክ" አለው::

በሰፊው የሚታወቀው ልክ እንደ አባቱ እስራኤልን ለአርባ ዓመት በማስተዳደሩና ታላቁን ቤተ መውደስ በመገንባቱ ነው፡፡ እንደ ነገሠም በገባዖን ለእግዚአብሔር መስዋዕትን አቀረበ፡፡ ጌታም ተገልጾ "ምን ትፈልጋለህ?" አለው፡፡ ሰሎሞንም እንደ አባቱ ማስተዋልን፣ ልቡናን ለመነ፡፡ ጌታም ደስ ስለተሰኘ "ከአንተ በፊትም ሆነ ከአንተም በኋላ እንዳንተ ያለ ጠቢብና ባለጸጋ ሰው አይኖርም" ብሎታል፡፡ ግሩም በሆነ ፍርዱ፣ በልዩ ጥበቡ ስለርሱ የሰማው ዓለም ሁሉ ተገዛለት፡፡ የእኛዋ ታላቅ ንግስተ ሳባ /ማክዳም/ ትፈትነው ዘንድ ሒዳ ምኒልክን ጸንሳ መምጣቷ በሁዋላም ለታቦተ ጽዮንና ሥርዓተ ኦሪት መምጣት ምክንያት ሆኗል፡፡ ቅዱስ ሰሎሞን በተለይ ስለ ድንግል ማርያም የጻፈው ምስጋና እንደ አባቱ ቅዱስ ዳዊት ዛሬም ድረስ በቅድስት ቤተክርስቲያንችን ጥቅም ላይ ይውላል፡፡

ንጉስ ሰሎሞን ድንግል ማርያም ከእርሱ ዘር እንደምትወለድ ሲነገረው፣ አንድም ሥጋ ለባሽ ሰው ነውና ሁለተኛም ከብዙ ሴቶች መካከል ከአንዷ እመ ብርሃን ትገኛለች መስሎት መፍቀሬ አንስት ሆነ፡፡ ከአሕዛብ ወገን ከፈርዖን ልጅ ጋር በመወዳጀቱም ለጣዖት ሰግዶ እግዚአብሔርን ቢያሳዝንም በራዕይ ተገልጦ "ስለ ወዳጄ ስለ ዳዊት ስል በአንተ ላይ ክፉን አላደርግም" አለው፡፡ ታላቁ ነቢይ ሰሎሞን ይህንን ሲሰማ ወደ ልቡ በመመለስ ማቅ ለብሶ፣ አመድ ነስንሶ በፍጹም ልቡ ንስሃ በመግባቱ ጌታችን ንስሃውን ተቀበለው፡፡ አሁን ድረስ ድንቅ ጥበብ የያዙትን መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን፣ መጽሐፈ ጥበብ፣ መጽሐፈ ምሳሌ፣ መጽሐፈ ተግሣጽ፣ መጽሐፈ መክብብ የተባሉ አምስት መጻሕፍት ገለጸለት፡፡

“ወዳጄ ሆይ፥ እነሆ ውብ ነሽ፤ እነሆ አንቺ ውብ ነሽ፤ ዓይኖችሽም እንደ ርግቦች ናቸው።” ናቸው ሲል ቅድስት ድንግል ማርያምን አመስግኗታል፡፡ ዘመናትን መዋጀት እንደሚገባ ሲነግረንም በተለይ ትልቁን የወጣትነት ጊዜ በጥበብ ቃላት ሲገልጸው “የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ፡፡ ደስ አያሰኙም የምትላቸውም ዓመታት ሳይደርሱ፤ ፀሐይ፣ ጨረቃና ከዋክብትም ሳይጨልሙ፤ አፈርም ወደ ነበረበት ምድር ሳይመለስ፤ ነፍስም ወደ ሰጠው ወደ እግዚአብሔር ሳይመለስ ፈጣሪህን አስብ፡፡” ይለናል፡፡ በመጽሐፈ ምክብብም በዚህ ዓለም ምንም ብንሰበስብ እግዚአብሔር ከሌለበት እንደማይረባ ሲነግረን "ከንቱ፣ ከንቱ፣ ሁሉ ከንቱ ነው" ይላል:: ጠቢብ፣ ነቢይና ንጉስ ሰሎሞን በዚህች ዕለት በ52 ዓመቱ ዐርፎ ወደ ፈጣሪው መሔዱን “ድርሳነ መስቀል” ላይ ሰፍሮ ይገኛል፡፡


በገዳማዊ ኑሮ ያሉትን እየረዳንና በዓታቸውን እያጸናን የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡


ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444




በወ/ሮ ሙሉ ግርማይ የተመሰረተው ላይፍ ሴንተር ነገ የገቢ ማሰባሰብያ ሊያካሄድ ነው

#FastMereja I ላይፍ ሴንተር ኢትዮጵያ የድርጅቱ መስራች ወ/ሮ ሙሉ ግርማይ በስደት ከሚኖሩበት አሜሪካን ሀገር ወደ ኢትዮጵያ ቤተሰብ ለመጠየቅ በመጡበት ወቅት የወላጅ አልባ ህፃናትንና የችግረኛ እናቶችን አስቸጋሪ ህይወት በመመልከት እራሳቸው ያለፉበትን የህይወት ፈተና በማስታወስ ወገኖቻችንን ለመርዳት በ2005 ዓ/ም የተመሰረተ የበጎ አድራጎት ድርጅት ሲሆን ላለፉት 12 ዓመታት ወላጅ አልባ ህፃናትንና መበለቶችን እየረዳ የቀጥለ ድርጅት ነው::

በጥቂት ህጻናት ብቻ የጀመሩት የስፖንሰርሺፕ እርዳታ ፕሮግራም አሁን ከ345 የሚበልጡ ወላጅ አልባ ህፃናትን የተመጣጠነ ምግብ፣ ልብስ፣ የትምህርት መርጃ መሣሪያዎችንና የመሳሰሉትን እያቀረበ የህይወት ክህሎት ስልጠና እና የምክር አገልግሎት እየሰጠ መልካም ዜጋን ለማፍራት አስተዋፅኦ እያደረገ ያለ ድርጅት መሆኑ ተገልጿል።

እንዲሁም ከ919 ለሚበልጡ መበለቶች የቢዝነስ ክህሎት ስልጠና በመስጠት: የአነስተኛ ብድር አገልግሎት ተጠቃሚ በማድረግ ላይ ይገኛል::

በአሁኑ ጊዜ እርዳታ የሚፈልጉ ወገኖቻችን ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመሄዱ፣ ላይፍ ሴንተር የአገልግሎቱን አድማስ በማስፋት ለብዙዎች ተደራሽ መሆን ይፈልጋል ያሉ ሲሆን ይህንን የተቀደስ ህልማችንን እውን ለማድረግ የወገኖቻችን ዕርዳታ ለመጠየቅ ዓመታዊ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር ነገ መጋቢት 4 ቀን 2017 በሂልተን ሆቴል መዘጋጀቱ ተገልጿል።

በዛሬው እለትም አርቲስት ልያት ስዩም የላይፍ ሴንተር የበጎ ፍቃድ አምባሳደር ተደርጋ ተሹማለች።

የላይፍ ሴንተር የበጎ ፍቃድ አምባሳደር ሆና የተሾመችው አርቲስት ልያት ስዩም የበጎ ፍቃድ አምባሳደርነቱ ለሁለት አመታት የሚቆይ ሲሆን ተቋሙን በተለያዩ ስራዎች የምታገለግል ይሆናል።


የፍቅር ጥያቄዬ ምላሽ አላገኘም ያለው ሁለት ሰዎችን ገድሎ ራሱን አጠፋ

በአዲስ አበባ ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስድስት ካርል አደባባይ አካባቢ በሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ አንድ ግለሰብ ሁለት ሰዎችን ገድሎ ራሱን እንዳጠፋ የአዲስ አበባ ፖሊስ ለቢቢሲ ተናገረ።

ክስተቱ ያጋጠመው ትናንት ማክሰኞ መጋቢት 02/2017 ዓ.ም. ሲሆን፤ ለሦስት ሰዎች ሞት ምክንያት የሆነው ሁኔታ የተፈጠረው 'የፍቅር ጥያቄዬ ምላሽ አላገኘም' በሚል ምክንያት መሆኑን ፖሊስ ገልጿል።

አቶ ሽፈራው ረጋሳ የተባለ የባንኩ የጥበቃ ሠራተኛ ለሥራ ባልደረባው የፍቅር ጥያቄ አቅርቦላት ምላሽ ባለማግኘቱ ግለሰቧን እና ከግለሰቧ ጋር የፍቅር ግንኙነት አለው በሚል የጠረጠረውን ሌላ ባልደረባውን በመግደል ራሱን እንዳጠፋ አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

ግለሰቡ የፍቅር ጥያቄ ያቀረበላት ወይዘሪት ሃና ተስፋዬ የተባለች 32 ዓመት ወጣት እና አቶ ንጉሤ ብርሃኑ የተባለ የሥራ ባልደረቦቹን በጥይት ተኩሶ የገደለው።

የአዲስ አበባ ፖሊስ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለቢቢሲ እንደገለጹት ወንጀሉን የፈፀመው የጥበቃ ሠራተኛ ካልተራው ሌላ ሠራተኛን ተክቶ በመግባት እና ከምሽት የጥበቃ ሠራተኞች የጦር መሳሪያ በመቀበል ግድያውን ፈፅሟል።

ግለሰቡ ግድያውን የፈጸመው ተጠርጣሪው ወደ ዕለታዊ ሥራቸው እስኪገቡ ድረስ በመጠበቅ መጀመሪያ አቶ ንጉሤ ብርሃኑ የተባለውን ግለሰብ በሁለት ጥይት መትቶ መግደሉን ኮማንደር ማርቆስ ገልጸዋል።

ግድያው ማክሰኞ መጋቢት 2/2017 ዓ.ም. ጠዋት ከአንድ ሰዓት ተኩል እስከ ለሁለት ሰዓት ሩብ ጉዳይ ድረስ ባላው ጊዜ ውስጥ መፈፀሙን የተናገሩት የአዲስ አበባ ፖሊስ ቃል አቀባይ፤ በሁለቱ ግድያዎች መካከል እስከ 15 ደቂቃ የሚሆን የጊዜ ክፍተት እንደነበረ አመለክተዋል።

ግድያውን የፈጸመው ግለሰብ ባልደረባውን ተኩሶ ከገደ በኋላ ሌላኛዋን የጥቃቱ ሰለባን ከመግደሉ በፊት ከድርጊቱ እንዲቆጠብ መጠየቁን ነገር ግን ፈቃደኛ እንዳልነበረ ተገልጿል።

ግለሰቡ መሳሪያውን እንዲያስቀምጥ እና እጁን እንዲሰጥ በተደጋጋሚ በተደጋጋሚ ጥያቄ ቀርቦለት የነበረ ሲሆን፣ በዚህ መካከልም ወደ ባንኩ አንደኛ ፎቅ በማምራት የፍቅር ጥያቄውን አልተቀበለችም ያላትን በተመሳሳይ ሁኔታ በጥይት መትቶ መግደሉን ፖሊስ ገልጿል።

ግለሰቡ ሁለቱን ባልደረቦቹን ከገደለ በኋላ በያዘው መሳሪያ የእራሱንም ሕይወት እንዳጠፋ የአዲስ አበባ ፖሊስ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ለቢቢሲ ገልጸው በክስተቱ በአጠቃላይ የሦስት ሰዎች ሕይወት ጠፍቷል።

ሁለቱ ሟቾች ወ/ሪት ሃና ተስፋዬ እና አቶ ንጉሤ ብርሃኑ የፍቅር ግንኙነት እንደነበራቸው የሚጠቁም ፎቶግራፎች መገኘታቸውን የጠቆሙት ኃላፊው፤ ፖሊስ በምርመራው ስለግንኙነታቸው እንደሚያጣራ ገልፀዋል።

ከዚሁ ክስተት ጋር በተያያዘ ፖሊስ እያካሄደ ያለውን የምርመራ ሂደት እንደሚቀጥል አስታውቋል።

ቢቢሲ ስለ ግድያው ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኃላፊዎችን ለማነጋገር ያደረገው ጥረት አልተሳካም።

ዘገባው የቢቢሲ ነው።




የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንሰል መገለጫ ሰጠ።

ከቅርብ ዓመታት ጀምሮ ወደ ምድራችን የሚመጡ የንስሐ ግቡ ሐልዕክቶች ሰለሆኑ ባላፈው ዓመት ታላቅ የአገራዊ ንስሃ ጊዜን በአደባባይ አከናውነናል። ይህንን ንስሃ መቀጠል ስለታመነበት የአገራዊ ንስሃ የሚያስተባብር ግብረ ኃይል በወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል ይሁንታ ተቋቁሞ ተግባሮቹን በተሻለ መንገድ ለመወጣት በመሥራት ላይ ይገኛል።

ስለዚህ ፦

1.ከሚያዝያ 6 እስከ 11/2017 ዓ.ም ከሰኞ- ቅዳሜ በሉት የህማማቱ ሳምንት በመላው አገሪቱ ባሉ ማህበር ምዕመናን ቢቻልም በከተሞች አመቺ በሆኑ በተመረጡ አብያተክርስቲያናት በአንድነት በመሰባሰብ የኑዛዜና የንስሐ ቀናቶች እንዲሆኑ።

2. ከሚያዝያ 19 እስከ ግንቦት 17/2017 ዓ.ም ባሉት ሳምንታት ኑዛዜ ያደረግንባቸው ጉዳዮችን ወደ ፍሬ እንዲመጡ በየአጥቢያው የንስሐ አቅጣጫዎች የትምህርት እና ንስሃውን ከሕይወት ጋር የምሰናዛምድባቸው ጊዜያቶች እንዲሆኑ።

3.ግንቦት 24 ቀን 2017ዓ.ም በሁሉም ከተሞችና አካባቢዎች የማጠቃለያ የንሰሐ ጊዜ መሪዎች በየክልሎቻቸው የካውንስል እና የኀብረቶች አደረጃጀቶች እንዲያደርጉና በአዲስ አበባ ለሚካሄደው ለአገር አቀፉ የማጠቃለያ የንስሐ ጊዜ ከልሉን የሚወክሉ መሪዎችን ወክለውና በክልሉ ቤተክርስቲያን መለኮታዊ ሥልጣን ጸልየውላቸው ወደ አዲስ አበባ እንዲልኩ።

4.ከግንቦት 25 አስከ 27 2017 ዓ.ም ለሦስት ቀናት ከመላው ኢትዮጵያ ክልሎች እና ከዲያስፖራ በክልሎች ቤተክርስቲያን መለኮታዊ ሰልጣን በሚወከሉ መሪዎች በአዲስ አበባ ከተማ ማጠቃለያውን በተወከሉ መሪዎች የንስሐ ጊዜ በማድረግ የንሰሐ ማጠቃለያ እንዲሆን ታቅዷል።

በመላው ኢትዮጵያ እና በውጭ ሀገር የምትኖሩ የወንጌላውያን አማኞች ሁሉ በዚህ በወጣው ፕሮግራም መስረት አሰተባባሪ ግብር ኃይል በልዩ ልዩ መገናኛ ዘዴዎች በሚያሰራጫቸው የንስሐ አቅጣጫዎች እና የኑዛዜ የጸሎት ርዕሶች አየታገዛቸሁ የንስሐ ጊዜውን አብረን በጋራ እንድናከናውን ጥሪዬን አቀርባለሁ።

“ኢየሩሳሌም ሆይ፥ ጕበኞችን በቅጥርሽ ላይ አቁሜአለሁ፤ ቀንና ሌሊት ከቶ ዝም አይሉም፤ እናንተ እግዚአብሔርን የምታሳስቡ፥ ኢየሩሳሌምን እስኪያጸና በምድርም ላይ ምስጋና እስኪያደርጋት ድረስ አትረፉ ለእርሱም ዕረፍት አትስጡ።”ትንቢተ ኢሳይያስ 62፥6-7

ልዑል አግዚአብሔር አገራችንን ኢትዮጵያን ይባርክ!!

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ከርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ጸሐፊ ቁስ ደረጀ ጀምበሩ




የመጀመሪያው ምዕራፍ 92 በመቶ የደረሰው የአርባ ምንጭ ስታዲየም በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው።

#FastMereja I የአርባ ምንጭ ስታዲየም የመጀመሪያ ምዕራፍ የግንባታ ሂደት 92 በመቶ መድረሱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ፡፡

ግንባታው እየተከናወነ ያለው በሕብረተሰብ ተሳትፎ፣ በመንግሥት እና በልማት አጋሮች ድጋፍ መሆኑ ተገልጿል።

የመጀመሪያው ምዕራፍ የግንባታ ሂደት ሲጠናቀቅ ሁለተኛው ምዕራፍ እንደሚቀጥል ተነግሯል።

ዲዛይኑ በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ስታንዳርድ መሰረት የተነደፈው ስታዲየሙ፤ ከዓለም አቀፉ እግር ኳስ ማኅበር የበላይ ጠባቂ (ፊፋ) ስታንዳርድ የተወሰደ መሆኑ ተገልጿል።

ግንባታው ሲጠናቀቅ፤
📌 የወንዶች አፍሪካ ዋንጫ (እስከ ሩብ ፍፃሜ)፣
📌 የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ (እስከ ፍፃሜ)፣
📌 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ማጣሪያዎች፣
📌 የወንዶች አፍሪካ ዋንጫ (ቻን) እና
📌 የሴቶች ሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታዎችን ማስተናገድ እንደሚችል አብራርተዋል፡፡

ስታዲየሙ የስፖርት ሜዳ፣ የተመልካች አካባቢ፣ የሚዲያ እና ደጋፊ አገልግሎቶች እንዲሁም የቡድን እና የባለስልጣኖች ክፍሎች እንደሚኖሩት አመላክተዋል፡፡

በቅርቡ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል የሚካሄድ ሲሆን በዚህም የገቢ ማሰባሰቢያ ላይ የተለያዩ ሚኒስትሮች የክልል መስተዳደሮችና ባለሀብቶችን ጨምሮ ከ350 በላይ እንግዶች እንደሚገኙ ተገልጿል።

ከዚህ በተጨማሪም ለስቴድየሙ ቋሚ ገቢ ለማሰባሰብ የቶምቦላ ሎተሪ እጣ ሽልማት የሚካሄድ ሲሆን ይህም ሎተሪ በአርባምንጭ ከተማ ሰፊ የካሬ መሬት፣ የኤሌክትሪክ ባጃጅ፣ የሞተር ሳይክል፣ የእንግሊዝ ሀገር ደርሶ መልስ ትኬትና የ5 ቀን የኳስ እይታና ምሽት እንዲሁም ሌሎች ሽልማትን የያዘ እንደሆነ የገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ እሺ ሚዲያ ገልጾልናል።

ስቴድየሙ ግንባታው ተጠናቆ ሲያልቅ እስከ 30ሺ ሰው የመያዝ አቅም እንዳለው ተነግሯል።

#ስፖርት


ቆሎ ሻጩ ሽልማት ተበረከተለት

ወላይታ ዲቻ ቅ/ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብን 1ለ0 ባሸነፈበት ጨዋታ ለውዝ እና ቆሎ ለግብ አስቆጣሪው አብነት ደምሴ የሸለመው አንድ ታዳጊ ትላንት ምሽት ወላይታ ዲቻዎች ወልዋሎ አዲግራት ዩንቨርስቲን 1ለ0 ካሸነፏ በኋላ ለደጋፊው ቅንነት ተጨዋቾቹ ያዋጡትን ብር ሸልመውታል ።

📷 Aku Images


ምንድነው የተፈጠረው?

#FastMereja I የድምፃዊ አንዱአለም ጎሳ ማናጀር የሆነው ለሊሳ እንድሪስ የተፈጠረውን ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ከሰጠው ምላሽ በፋስት መረጃ እንደሚከተለው እናቀርበዋለን።
ንጋት 11:00 ሰዓት ስልክ ተደውሎ «ቀነኒ ተጎድታ ሆስፒታል ገብታለች ቶሎ ድረስ» እንደተባለ የሚናገረው ለሊሳ እሱ ሩቅ በመሆኑ በሰዓቱ መድረስ እንዳልቻለ ይናገራል።

ቦሌ አራብሳ ከአመት በላይ በጋራ ከሚኖሩበት መኖሪያ ቤታቸው ከአምስተኛ ፎቅ እንደወደቀች እና ምን እንደተፈጠረ ፖሊስ እያጣራ መሆኑ ተነግሯል።

ክስተቱ ከተፈጠረ በኋላ በቅርብ በሚገኘው ያኔት ሆስፒታል ከገባች በኋላ ጠዋት ፖሊስ መጥቶ ሬሳዋን ወደ ሚኒሊክ ሆስፒታል ለምርመራ ከወሰደ በኋላ የምርመራ ውጤት እስኪወጣ አስክሬኗ ወደ ቤተሰቦቿ ሱሉልታ መሄዱ ነው የተገለፀው።

ድምፃዊ አንዱዓለም ጎሳ ለጥያቄ ትፈለጋለህ ተብሎ ከሆስፒታል ወደ ፖሊስ ጣቢያ ተወስዶ እዛ የሚገኝ ሲሆን እኛ የምናውቀው እስካሁን አለመታሰሩን ነው ምርመራ እናድርግ ብሎ ነው ፖሊስ የወሰደው ሲል ማናጀሩ ይናገራል።

ለሁለት አመታት በፍቅር ከቆዩ በኋላ በቅርቡ ጋብቻቸውን ለመፈፀም እየተዘጋጁ እንደሆነ አውቃለሁ ሲል ለሊሳ ይናገራል።

6.2k 0 13 14 52

ምንድነው የተፈጠረው?

#FastMereja I የድምፃዊ አንዱአለም ጎሳ ማናጀር የሆነው ለሊሳ እንድሪስ የተፈጠረውን ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ከሰጠው ምላሽ በፋስት መረጃ እንደሚከተለው እናቀርበዋለን።
ንጋት 11:00 ሰዓት ስልክ ተደውሎ «ቀነኒ ተጎድታ ሆስፒታል ገብታለች ቶሎ ድረስ» እንደተባለ የሚናገረው ለሊሳ እሱ ሩቅ በመሆኑ በሰዓቱ መድረስ እንዳልቻለ ይናገራል።

ቦሌ አራብሳ ከአመት በላይ በጋራ ከሚኖሩበት መኖሪያ ቤታቸው ከአምስተኛ ፎቅ እንደወደቀች እና ምን እንደተፈጠረ ፖሊስ እያጣራ መሆኑ ተነግሯል።

ክስተቱ ከተፈጠረ በኋላ በቅርብ በሚገኘው ያኔት ሆስፒታል ከገባች በኋላ ጠዋት ፖሊስ መጥቶ ሬሳዋን ወደ ሚኒሊክ ሆስፒታል ለምርመራ ከወሰደ በኋላ የምርመራ ውጤት እስኪወጣ አስክሬኗ ወደ ቤተሰቦቿ ሱሉልታ መሄዱ ነው የተገለፀው።

ድምፃዊ አንዱዓለም ጎሳ ለጥያቄ ትፈለጋለህ ተብሎ ከሆስፒታል ወደ ፖሊስ ጣቢያ ተወስዶ እዛ የሚገኝ ሲሆን እኛ የምናውቀው እስካሁን አለመታሰሩን ነው ምርመራ እናድርግ ብሎ ነው ፖሊስ የወሰደው ሲል ማናጀሩ ይናገራል።

ለሁለት አመታት በፍቅር ከቆዩ በኋላ በቅርቡ ጋብቻቸውን ለመፈፀም እየተዘጋጁ እንደሆነ አውቃለሁ ሲል ለሊሳ ይናገራል።


#እመቤታችን ሰማያትን ያሳየችው ቅዱስ

የትውልድ ሃገሩ ሶርያ ውስጥ ሮሃ አካባቢ ነው፡፡ ተወልዶ ባደገባት ሃገር ይህ ቀረው የማይባል ኃጢአተኛ ሰው ቢሆንም እመቤታችን ቅድሰት ድንግል ማርያምን በፍፁም ልቡ ይወዳት ነበርና በመዳን ቀን ጥሪ ለንስሐ አበቃችው፡፡  ከዚያች ዕለት ጀምሮም ቅዱስ የእግዚአብሔር ሰው፣ ንጹሕ የቤተ ክርስቲያን መስዋዕት፣ ጽኑዕ የበርሃ ምሰሶ ሆነ፡፡ ድንግል እመቤታችንም ከነሥጋው ወደ ሰማያት ወስዳ ገነትና ሲዖልን አሳይታ፣ ከአዳም ኖኅ፣ ከአብርሃም እስከ ሙሴና ዳዊትን ከመሰሉ ቅዱሳን ጋር አገናኘችው፡፡ ከዚህም በላይ የሆነና በሰብአዊ አንደበት የማይነገር ብዙ ምሥጢር አሳይታ ወደ ምድር መልሳዋለች፡፡ ይህም በቅድስት ቤተክርስቲያናችን ቅዱስ ጎርጎርዮስ ረዓዬ ኅቡዓት ምሥጢራትን የተመለከተ እየተባለ እንዲጠራ አድርጎታል፡፡

ቅዱስ ጎርጎርዮስ በሰማይ በነበረው ቆይታ ክብረ ቅዱሳንን ተመልክቶ አድንቋል:: በተለይ በፍጹምነት ድንግልናቸውን የጠበቁ ቅዱሳንና ቅዱሳት ደናግል አኗኗራቸው ከአምላክ እናት፣ ከሰማይ ንግሥት፣ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር መሆኑን አይቷል፡፡ "የለበሱት ልብስም በፍጡር አንደበት ተከናውኖ ሊነገር የሚቻል አይደለም" ይላል፡፡ የደናግል ፊታቸው ከፀሐይ 7 እጅ ያበራልና ግርማቸው ያስፈራል፡፡ ቅዱስ ጎርጎርዮስ በዚያው በሰማይ ሳለ ደግሞ ይህንን ተመለከተ፡፡ አንድ አረጋዊ፣ ጽሕሙ ተንዠርግጐ፣ የብርሃን ካባ ላንቃ ለብሶ ይመጣል፡፡ ቅዱሳን መላእክት በፊት በኋላ፣ በቀኝ በግራ ከበውት ሳለ እግዚአብሔርን በበገናው ሊያመሰግን ጀመረ፡፡ "አቤቱ ጌታችን በምድር ሁሉ ስምህ የተመሰገነ ሆነ" ሲል መላእክቱ በዝማሬ አጀቡት::

በዚህ ጊዜም ታላቅ መናወጥ ሆነ፡፡ ደናግሉም የቅዱሱን ሽማግሌ በረከቱን ተሳተፉ፡፡ ይህ አመስጋኝ ሽማግሌ ልበ-አምላክ፣ ጻድቅ፣ የዋህና የእሥራኤል ንጉሥ ዳዊት ነበር፡፡ አንድም እመቤታችን "አባቴ ዳዊት!" ብላ ስትጠራው ቅዱስ ጎርጎርዮስ ሰምቷልና፡፡ በመጨረሻም እመቤታችንን በፍጹም ክብርና ግርማ ተመልክቷት ሐሴትን አድርጓል፡፡ እመ-ብርሃንም "ተወዳጅና ንጹሕ ሰው ነህ" ስትል ቅዱስ ጎርጎርዮስን አመስግናዋለች፡፡ ስለዚህ ዓለምም እንዲህ የሚል መልእክትን ልካለች:: "ልጆቼ ሆይ! ከብርሃን ጨለማን፣ ከደግነት ክፋትን፣ ከጽድቅ ይልቅ ኃጢአትን ምነው መምረጣችሁ? እኔ ስለ እናንተ በየቀኑ እየለመንሁ እነሆ አለሁ:: ወደ ጨለማ ገሃነም እንዳትወርዱ እባካችሁ ንስሐ ግቡ!"

ቅድስት ድንግል ማርያም ይህንን ለቅዱሱ ሰው ነግራው፣ ቅዱስ ዳዊትን አስከትላ በግሩማን መላእክት ታጅባ የእሳት መጋረጃዎች ወደ ተተከሉበት ድንኳን ገባች፡፡ በዚያም ተመሰገነች፡፡ ታላቁ አባት አባ ጊዮርጊስ ዘጋሰጫም "ይዌድስዋ መላእክት ለማርያም በውስተ ውሳጤ መንጦላዕት፣ ወይብልዋ፣ በሐኪ ማርያም ሐዳሲሁ ጣዕዋ"፤ “መላእክት ማርያምን በመጋረጃዎች ውስጥ ላንቺ ምስጋና ይገባሻል እያሉ አመሰገኗት” የሚለንም ለዚህ ነው፡፡ ቅዱስ ጐርጐርዮስም ከሰማይ ቆይታው መልስ ያየውን ሁሉ ጽፎ ለአበው ሰጥቷል፡፡ ስለዚህም ረዓዬ ኅቡዓት “ምሥጢራትን ያየ” ይሰኛል፡፡ ቅዱሱ ተረፈ ዘመኑን በተጋድሎ ፈጽሞ በመጋቢት ሁለት ቀን አርፏል፡፡ የቅዱሱ እመቤት ድንግል እመ ብርሃን መዓዛ ፍቅሯን ታብዛልን፡፡ በቅድስና ሕይወት፣ በገዳማዊ ኑሮ ያሉትን እየረዳንና በዓታቸውን እያጸናን የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡


ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444




ቤቲ እና ናቲ ላይ ትኩረት አድርጓል የተባለለት «እንግዱ» ፊልም ለእይታ ሊቀርብ ነው።

#FastMereja I በልባም ፒክቸርስ ተዘጋጅቶ በሳዳም ፊልም ፕሮዳክሽን እና በሶሎዳ ስቱዲዮ የቀረበው «እንግዱ» ፊልም ለእይታ ሊቀርብ ነው።

ፊልሙን ለማዘጋጀት ከ8 ወር በላይ እና በወጪ በኩል 2.5 ሚሊዮን ብር እንደወጣበት የተገለፀ ሲሆን በፊልሙም ላይ በትወና ሰለሞን ሙሄ፣ ኤደን ገነት፣ ደረጄ ሀይሌ፣ ጌዲዮን ፍቃዱ፣ አሰፋ ገ/ሚካኤልና ሌሎች ከ35 ሰዎች በላይ ታዋቂ እና አጃቢ ተዋናዮች እንደተሳተፉበት ተገልጿል።

የፊልሙ ይዘት ልብ አንጠልጣይ ትሪለር ይዘት ያለው ሲሆን በሶሻል ሚዲያ የሚታወቁ ቤቲ እና ናቲ ላይ ትኩረት ያደረገ እንደሆነ እንዲሁም ተዋናይ ጌድዮን ፍቃዱ ሰባት ካራክተር ወክሎ በፊልሙ ላይ መተወኑ ተነግሯል።

በቀይ ምንጣፍ ስነ ስርዓት መጋቢት 1/2017 ዓ.ም በአለም ሲኒማ የፊልም ተዋናዮች የተለያዩ የሚድያ ሰዎች ተፅኖ ፈጣሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ይመረቃል።

#ኪነ_ጥበብ

6k 0 12 8 17

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ - ለሰላም፣ ለመተባበር እና ለአብሮነት
ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይባርክ
መጋቢት 2 ቀን 2017
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ


በኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የተሠጠ መግለጫ

“የሃይማኖት ንጽጽር - በከፍተኛ የሃይማኖት ሊቃውንቶች መካከል በሕግ፣ በሥርዓት እና በጥብቅ ዲሲፕሊን የሚመራ በዶግማዊ ጉዳዮች ላይ የሚደረግ የሰከነ ውይይት ነው፤ በአማኞች መካከል የሚደረግ ሥርዓት የለሽ እና አንዱ ሌላውን የሚያውገዝ፣ የሚያጠልሸ እና ክብረ-ነክ መሆን ወንጅል ነው፤” ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የማኅበራዊ ሚዲያውን እድገትና ተደራሽነት መስፋትን ተከትሎ በተለያዩ ርዕሠ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩሩ አጀንዳዎች ላይ በአወንታዊነት እና በአሉታዊነት የሚፈረጅ ይዘት ያላቸው ሥራዎች ተሠርተው አየር ላይ ሲውሉ እናያለን፤

አንዳንዶች ደግሞ የራሳቸውን የማኅበራዊ ሚዲያ መድረክ በመክፈት የተለያዩ ግለሰቦችን ወደመድረካቸው በመጋበዝ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በደጋፊነት እና በነቃፊነት ላይ ተሰልፈው የጦፈ ክርክር ሲደርጉም እንመለከታለን፡፡

ዘርፉና የመገናኛ መድረኩ የራሱ የሆነ የአጠቃቀም መመሪያ ያለውና በጥብቅ ዲሲፕሊን እንዲመራ የሚጠበቅ ቢሆንም አንዳንድ ግለሰቦችና ቡድኖች መድረኩን ከዓላማው ውጪ ለሆነና ለግልና ቡድናዊ ፍላጎታቸው መጠቀሚያ በማድረግ በተለያዩ ሃይማኖት/እምነት ተከታዮች መካከል መተማመኑ እና መከባበሩን የሚሸረሽሩ ይዘቶችን፣ ክብረ ነካዊ በሆነ አቀራረብ ግልፅ ጥላቻን የመስበኩ ልምምድ ከጊዜ ወደጊዜ እየተባባሰ ይገኛል፡፡

ይህ ዓይነቱ አቀራረብና ልምምድ አልፎ አልፎ በአንዳንድ የሃይማኖት ተቋማት ውስጥ በመደበኛ የአምልኮ መርሀ ግብር ላይ በፊት ለፊት መድረኮች ሲቀርብ አይተናል፡፡ ልምምዱና አቀራረቡ ከወዲሁ ሊታረምና በሕግና ሥርዓት ሊከናውን እንደሚገበው ጉባኤያችን በጽኑ ያምናል፡፡ ከዚህ አንፃር ከሰሞኑ የሁለቱ ታላላቅ ሃይማኖቶች የተቀደሰ የጾም፣ የጸሎትና በከፍተኛ ደረጃ የመንፈሳዊ እነፃ ላይ በሚገኙበት ጊዜ ከመንፈሳዊነትና ከሃይማኖቶች መሠረታዊ ዕሴት ጋር የሚቃረን ተግባር በማኅበራዊ ሚዲው በስፋት እየተሠራጨ ይገኛል፡፡

በተለይም አንዳንድ የኦርቶዶክስ ክርስትና አማኝ ነን የሚሉ ግለሰቦች፣ የእስልምና ሃይማኖት ነቢይ በሆኑት በነቢዩ መሐመድ (የአላህ እዝነትና ሰላም በእሳቸው ላይ ይሁንና) ላይ ድፍረት የተሞላበት ክብረ ነክና ጽያፍ ንግግር ሲያደርጉ ታየረተዋል፡፡ ይህም ሙስሊሙን ወገን ብቻ ሳይሆን ሰላም ወዳዱን ወገን ሁሉ አሳዝኗል፡፡

ጉባኤችንም ይህ ዓይነቱ ኢ-ሥነምግባራዊ እና ሕገ ወጥ ተግባር የትኛውንም የሃይማኖት ተቋም የማይወክል፣ ይልቁንም የሚወገዝ ተግባር መሆኑን ለመግለጽ ይወዳል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘም አንዳንድ የኦርቶዶክስ አማኝ ነን የሚሉ ወንድሞችና እህቶች የግለሰቡን ሕገ-ወጥ ተግባር ተቋማዊ ለማድረግ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ እንዲያጤኑና ግለሰብንና ተቋምን እንዲለዩ እንመክራለን፡፡

በአንፃሩ አንዳንድ ሙስሊም ነን የሚሉ ግለሰቦች ተደፈርን በሚል ስሜት የክርስትና አስተምህሮንና የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር የሚነቅፍና የሚያጠለሽ፣ መላውን ክርስቲያን በሚያዋርድ መልኩ ምላሽ ሲሠጡ እና ድርጊቱን በፈፀመው ግለሰብ ላይ የደቦ ፍርድ ሲያስተላልፉ ይታያሉ፡፡

ይህም ሕገ-ወጥነትን ከማስፋፋት ባለፈ ጥፋትን በሌላ ጥፋት ማረም ፈጽሞ የማይቻል መሆኑን ተገንዝበው ከድርጊታቸው በመታረም የሕግ የበላይነትን እንዲስቀድሙ ጉባኤያችን በአጽንኦት ይመክራል፡፡ በየትኛውም አካል የተፈፀሙትና የሚፈፀሙት ይህን መሠል ሕገ-ወጥ ተግባራት በሁሉም ሃይማኖቶች አስተምህሮ ተቀባይነት
የሌላቸው ብቻ ሳይሆን የሚወገዙ ተግባራት መሆናቸውን ጉባኤያችን እያስገነዘበ ድርጊቱ በወንጀል የሚስጠይቅ ስለመሆኑም ለማስታወስ ይወዳል፡፡

ሀገራችን ኢትዮጵያ የብዝሀ ሀይማኖት መገኛና መኖሪያ ከመሆኗ አንፃር የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የትኛውንም ዓይነት የሃይማኖት ተቋማትን፣ አስተምህሯቸውንና መገለጫዎቻቸውን የሚያንቋሽሹና የሚያዋርዱ ንግግሮችንም ሆነ ተግባራትን በጽኑ ያወግዛል። እንዲህ ያሉት ክብረ-ነክ የሆኑ ተግባራትና አስተያየቶች ሁሉ ድርጊቱ ለተፈፀመባቸው እምነት ተከታዮችን በእጅጉ የሚያስቆጡ ብቻ ሳይሆኑ መላ ኢትዮጵያዊያንን በእጅጉ የሚያስቆጡ ናቸው፡፡ የመከባበርና የአብሮነት እሴቱን በመሸርሸር በሀገራችን የሰላምና የሰላማዊ ማህበረሰብ ግንባታ ሂደቱንና ጥረቱን እንዳይያሳካ ያደርጋሉ፡፡

ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት አንዱ የሌላውን እምነት ለመስደብ ወይም ለማዋረድ በፍፁም ጥቅም ላይ መዋል የለበትም። የእምነት ነፃነት እና የማምለክ መብት ለሁሉም ማህበረሰቦች የተጠበቀ ሲሆን ይህ መብት የሌሎች አማኞችን መብት በመጋፋና ስሜት በመንካት ለጠብ ማነሳሽነት ሲውል በዝምታ ሊታለፍ አይገባውም፡፡
ይህንን ከባድ ጥፋት በዘላቂነት እንዲታረም የሚመለከታቸው አካላት አግባብነት ባላቸው ሕጎች መሰረት ይህንንና ተመሳሳይ ተግባር በፈፀሙና በሚፈጽሙ አካላት ላይ አፋጣኝ ሕጋዊ እርምጃ እንዲወስዱ እንጠይቃለን። ለእንደዚህ አይነት ወንጀሎች ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ለወደፊቱ የሃይማኖትን ስም ማጥፋት ለመከላከልና የሁሉም እምነት ተከታዮች ክብርን ለመጠበቅና
ለማስጠበቅ በእጅጉ ይረዳል።

በተጨማሪም የሃይማኖት መሪዎች፣ የሃይማኖት ምሁራን እና መላ ሕብረተሰቡ በሃይማኖቶች መካከል መከባበር፣ መግባባትና መረዳዳት ይበልጥ ሊያጠናክሩ በሚያስችሉ የጋራና የተመረጡ አጀንዳዎች ላይ በሕግ፣ በሥርዓትና በጥብቅ ዲሲፕሊን የሚመሩና ግልጽ ዓላማና ግብ የተቀመጠላቸው ውይይቶችና ምክክሮች በተጠናከረ መልኩ በማከናውን በሃይማኖቶች መካከል ትብብራቸውንና አጋርነታቸውን እንደ ሚያጠናክሩ ይጠበቃል፡፡

በቅርቡ ጉባኤያችን ወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታዎችን በመዳሰስና በመተንተን ሀገራዊ ዓውዱንና ተግዳሮቶች ታሳቢ በማድረግ፣ እንዲሁም ተቋሙ ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆን ለማስቻል የመተዳደሪያ ደንቡን አሻሽሏል፡፡ የተሻሻለው ደንብም በተቋማት መካከል አለመከባበርን፣ አለመቻቻልን የሚሰብኩ፣ ጥላቻን የሚቀሰቅሱና ግጭትን የሚያባብሱ ተንኳሽና ክብረ-ነክ ንግግሮችንና ተግባራትን የሚፈፅሙ ግለሰቦችና ቡድኖች በራሳቸው ተቋም ተጠያቂ የሚያደርግ ሥርዓት እንዲኖር የሚያደርግ ድንጋጌ በደንቡ ላይ እንዲካተት ተደርጓል፡፡

የችግሩ ስፋትና ጥልቀት እየጨመረ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞም ችግሮን በዘላቂነት ለመፍታትም ከአባል የሃይማኖት ተቋማት የሚወከሉ የሕግና አግባብነት ያላቸው ባለሙያዎች የሚካተቱበት የተከላካይ ግብር-ኃይል አደረጃጀት በጊዜያዊነትና በቋሚነት በማደራጀት የቅደመ መከላከል ሥራዎች ለመስራት ተዘጋጅቷል፡፡

ግብር-ኃይሉም ችግሮችንና የችግር አዝማሚያዎችን በማሰባሰብ፣ በመተንተንና የመፍትሔ ሀሳቦችን በመስጠት ሙያዊ እገዛ በማድረግ ሕግና ሕጋዊነትን የማስጠበቅ ሥራ በመስራት የሀገር ሰላምንና የሃይማኖት ተቋማትን ክብርና ልዕልና የማስጠበቅ ኃላፊነቱን ይወጣል፡፡

የሁለቱም እምነት ተከታዮች እና አማኞች በማኅበራዊ ሚዲያው ባለው አሉታዊ ዘመቻና በተፈጠረው ወቅታዊ ችግር ሳይረበሹ የጾም፣ ጸሎትና የንስሀና ተግባሮቻቸው ላይ እንዲያተኩሩ ጉባኤያችን ይመክራል፡፡

የሕግ አስከባሪ አካሉም፣ በአማኞች መካከል ያለው ሰላምና መከባበር የሚያውኩ፣ ሕገ-ወጥ ግለሰቦችና ቡድኖች ከድርጊታቸው እንዲታረሙ በማድረግ ሕግና ሥርዓት የማስጠበቅ የተለመደ ሕጋዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጉባኤያችን ጥሪውን ያቀርባል፡:

በመጨረሻም ሁላችንም የሃይማኖት ተቋሞቻችንንና የአስተምህሯችንን ክብር፣ ልዕልናና ቅድስና እንጠበቅ በማለት ጉባኤያችን የአደራ መልዕክቱንና ጥሪውን ያቀርባል፡፡




“የጊዜያዊ አስተዳደሩ በሶስት ጄነራሎች ላይ ያሳለፈው የእግድ ውሳኔ ተቋማዊ አሰራርን እና ህግን ያልተከተለ ነው” - የክልሉ የሰላምና ጸጥታ ቢሮ

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በክልሉ በተለያዩ ግንባሮች አዛዦች መሆናቸው የተገለጸ ሶስት ጄነራሎችን፤ ሜጀር ጀነራል ዮሃንስ ወ/ጊዮርጊሰ፣ ሜጀር ጀነራል ማሾ በየነ እና ብርጋዴር ጀነራል ምግበይ ሀይለ በግዜያዊነት ማገዳቸውን አስታወቁ።

በፕሬዝዳንቱ የተጻፈው ደብዳቤ እንደሚያሳየው ጄነራሎቹ በግዜያዊነት የታገዱት “ከመንግስት ውሳኔ ውጭ መላ የክልሉን ህዝብ እና ወጣቱን ወደ ግርግር፣ የጸጥታ ሀይሉን ወደ እርስ በርስ ግጭት የሚያስገባ እንቅስቃሴዎች እያደረጉ በመሆኑ ነው” ብሏል፤ የጀነራሎቹ እንቅስቃሴ “ህዝቡ ወደማይወጣው አዘቅት የሚከት ነው” ሲል አስታውቋል።

የፕሬዝዳንቱን ውሳኔ ተከትሎ የክልሉ የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ “የወንጀለኞች ጠበቃ መሆን ይብቃ” በሚል ርዕስ ዛሬ መጋቢት 2 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ውሳኔውን እንደማይቀበለው አስታውቋል፤ “ያልሾመውን ያወረደ ነው” ሲል ገልጿል።

በተመሳሳይ በደብረጺዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ባወጣው መግለጫ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ውሳኔን ህገወጥ ሲል ኮንኗል፤ “የትግራይ ሰራዊትን ለማፍረስ ሲያደርግ የነበረው ሴራ ወደ ከፍተኛ እና አደገኛ ደረጃ አሸጋግሮታል” ሲል ገልጿል።



Показано 20 последних публикаций.