3ኛው «መኖር በጊፍት መንደር» የሽያጭ ኤክስፖ ተከፈተ
#FastMereja I ጊፍት ሪል ስቴት በመንግስትና የግል አጋርነት ልማት ፕሮጀክት 12 ሺህ ቤቶችን ለመገንባት ከተያዘው ስምምነት መካከል የሁለተኛው ምዕራፍ ፕሮጀክት ግንባታ ማስጀመሪያና ማስተዋወቂያ እንዲሁም ሶስተኛው “መኖር በጊፍት መንደር” የሽያጭ ኤክስፖ መርሃ ግብር ተከፈተ።
ለረጅም ዓመታት በኢትዮጵያ የሪል ስቴት ዘርፍ ግንባር ቀደም ተወዳዳሪ የሆነው ጊፍት ሪል ስቴት “መኖር በጊፍት መንደር” በሚል መሪ ቃል ሶስተኛው የሽያጭ ኤክስፖ ከዛሬ ግንቦት 19 እስከ ግንቦት 24 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚያካሄድ አሳወቀ።
የጊፍት ሪልስቴት የሽያጭ እና ማርኬቲንግ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ብርቁ ይርጋ እንደገለጹት ጊፍት ሪል ስቴት ለገዢዎች እስከ 30 በመቶ የሚደርስ የአጭር ጊዜ ቅናሽ ያቀረበ ሲሆን ከ9 በመቶ እስከ 25 በመቶ ቅድመ ክፍያ በመክፈል የቤቶቹ ባለቤት መሆን እንደሚቻል እና የዚህን ታላቅ ቅናሽ ተጠቃሚ እንዲሆኑም ጥሪ አቅርበዋል።
ጊፍት ሪል ስቴት እስካሁን በ165 ሺህ ካሬሜትር ላይ በሲኤምሲ እና ፈረስ ቤት ሦስት ትላልቅ መንደሮችን ገንብቶ ለማኅበረሰቡ ማስረከብ መቻሉ የተመላከተ ሲሆን ዓለም የደረሰበትን የግንባታ ቴክኖሎጂ በመጠቀም ዘመናዊ እና ቅንጡ የመኖሪያና የንግድ አፓርትማ መንደሮችን እየገነባ እንደሚገኝ ተጠቁሟል።
#FastMereja I ጊፍት ሪል ስቴት በመንግስትና የግል አጋርነት ልማት ፕሮጀክት 12 ሺህ ቤቶችን ለመገንባት ከተያዘው ስምምነት መካከል የሁለተኛው ምዕራፍ ፕሮጀክት ግንባታ ማስጀመሪያና ማስተዋወቂያ እንዲሁም ሶስተኛው “መኖር በጊፍት መንደር” የሽያጭ ኤክስፖ መርሃ ግብር ተከፈተ።
ለረጅም ዓመታት በኢትዮጵያ የሪል ስቴት ዘርፍ ግንባር ቀደም ተወዳዳሪ የሆነው ጊፍት ሪል ስቴት “መኖር በጊፍት መንደር” በሚል መሪ ቃል ሶስተኛው የሽያጭ ኤክስፖ ከዛሬ ግንቦት 19 እስከ ግንቦት 24 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚያካሄድ አሳወቀ።
የጊፍት ሪልስቴት የሽያጭ እና ማርኬቲንግ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ብርቁ ይርጋ እንደገለጹት ጊፍት ሪል ስቴት ለገዢዎች እስከ 30 በመቶ የሚደርስ የአጭር ጊዜ ቅናሽ ያቀረበ ሲሆን ከ9 በመቶ እስከ 25 በመቶ ቅድመ ክፍያ በመክፈል የቤቶቹ ባለቤት መሆን እንደሚቻል እና የዚህን ታላቅ ቅናሽ ተጠቃሚ እንዲሆኑም ጥሪ አቅርበዋል።
ጊፍት ሪል ስቴት እስካሁን በ165 ሺህ ካሬሜትር ላይ በሲኤምሲ እና ፈረስ ቤት ሦስት ትላልቅ መንደሮችን ገንብቶ ለማኅበረሰቡ ማስረከብ መቻሉ የተመላከተ ሲሆን ዓለም የደረሰበትን የግንባታ ቴክኖሎጂ በመጠቀም ዘመናዊ እና ቅንጡ የመኖሪያና የንግድ አፓርትማ መንደሮችን እየገነባ እንደሚገኝ ተጠቁሟል።