አውደ Tibeb


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️♥♥♥♥♥♥♥♥♥
ከጥበብ ምንጭ
አብረን እንጎንጭ!!!
መንፈሳዊ፣ሀገራዊና፣ፍቅር ነክ ግጥሞች፤
ትረካ፣መነባንብ እና ለድራማ የሚሆኑ ጽሁፍች ከዚ ቻናል ያገኛሉ!!!
በሚመቾት መንገድ
የሚፈልጉትን ጽሁፍ እንጽፋለን ለትዕዛዞትና
ለአስተያትዎ @zemeden_bot
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️♥♥♥♥♥♥♥♥♥

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций




ስለምን ልናገር?
👉ስለ እኔ የጨለማ ኃጢአት፤ወይንስ ስለ እመብርሃን ርኅርኅተ ልብነት?
👉ስለኔ ደካማነት፤ወይንስ ስለ አዛኝቷ አማላጅነት ስለ ልጇ ብርታት ሰጪነት?
👉ስለ እኔ የኃጢአት በሽተኝነት፤ወይንስ ስለ ማርያም መድኃኒትነት ስለ ልጇ ቤዛነት?
👉ስለ እኔ አለመቻል፤ወይንስ ስለ አንድያ ልጇ ኤልሻዳይነት?
👉ስለኔ ቃል ዓባይነት፤ወይንስ ስለ እሷ የቃል ኪዳን ምሕረት?
👉ስለኔ ድብቅ ኃጢአት፤ወይንስ ስለ ልጇ ከባቴ አበሳነት?
ስለምን መናገር እንዳለብኝ እና እንዴት መጸለይ እንዳለብኝ ግራ ሲገባኝ ከነ ጉድፍ ማንነቴ ከነ ርኩሰቴ ከመቅደሱ እገባና
እመ ብርሃንን አያታለሁ። ኃጢአቴ በመላ እፊቴ ይከመርና አንገት እደፋለሁ፤ አቀረቅራለሁ፤ከልቦናዬ ጋ እነታረካለሁ፤
ምን ጊዜ እንደጀመረ ያላወቅኩት የ ዕንባዬ ጅረት ይበልጡኑ ይጨምራል፤ጉንጮቼ ይርሳሉ፤ልቤ ይንሰቀሰቃል፤የምለው ይጠፋኛል፤የምገባበት አጣለሁ፤
አንዳች የምለውን ቢያቀብለኝ ብዬ ቅዱሱ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫን እማጸነዋለሁ፤
ከሱ  ጋር በመሆን  በአርጋኖን እንዲህ እላታለሁ
" የሰራሁትን ኃጢአት ባስበው ልቡናዬ እጅግ ደነገጠብኝ አእምሮ ሳለኝ አለል ዘለል እያልኩ በጽርዓት መኖሬን ባሰብሁት ጊዜ ልቡናዬ እጅግ ደነገጠ
የኃጢአቴን ብዛት በተቆጣጠርሁ ጊዜ ልቡናዬ እጅግ ደነገጠ አንድ ሰዓት ስንኳን አላቋረጥኩም
በሰውና መላእክት ጉባኤ መሐከል ራቁቴን መቆሜን አሰብሁ
በዓይነ ልቡናዬ እመለከት ዘንድ ወዲህና ወዲያ ተመላለስሁ
ምናልባት የሚረዳኝ ባገኝ ከዚህ እጅግ የሚያስፈራው ከሠራሁት ኃጢአት ፍዳ የተነሳ ምናልባት የሚዋሰኝ ባገኝ ብዬ
ነገር ግን በማማለድ እኔን ለማዳን የምትችይውን አንቺን አማላጅ አገኘሁ ዘወትርም ከጎኔ እንዳትርቂ ዐወቅሁ
እንዲህ በፍቅር ያዝሁሽ በጣቶቼ አይደለም
በሃይማኖት ያዝሁሽ በመዳሰስ አይደለም በእደ ሕሊና ያዝሁሽ በእደ ሥጋ አይደለም"  አርጋኖን ዘሠሉስ
👉ስለምን ልናገር ስለኔ አለል ዘለል ማለት፤ ወይንስ ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ትህትና?
👉ስለ ሀዘኔ፤ ወይንስ የደስታ መፍሰሻ ስለሆነችኝ ስለ እመ ብርሃን፤ወይንስ ደስታ ስለሆነኝ መድኃኔዓለም?
ስለምን ልናገር?
❤እመቤቴ ሆይ የምናገረውን አላውቅምና አንደበት ሁኚኝ፤
ርግማን ከቦኛልና በበረከትሽ ጎብኚኝ፤
አንድ ጊዜ እዪኝ...
https://t.me/felege_tibeb




Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram


@henok_kibebew/video/7272799622198807814?_r=1&u_code=djl9ikmkmefa44&preview_pb=0&sharer_language=en&_d=e8f03lm7cdd3g8&share_item_id=7272799622198807814&source=h5_m×tamp=1693311131&user_id=6989266477879772165&sec_user_id=MS4wLjABAAAAn190Z7c2ZZOWZA0tw8ZymlFtBtIwR-TVQYCvSBsappPMOr9LC3EVap_VrvzZ9E4J&social_share_type=0&utm_source=telegram&utm_campaign=client_share&utm_medium=android&share_iid=7246126020594796294&share_link_id=394e411e-6be3-4a90-9278-31110f79556b&share_app_id=1233&ugbiz_name=Main&ug_btm=b8727%2Cb2878' rel='nofollow'>https://www.tiktok.com/@henok_kibebew/video/7272799622198807814?_r=1&u_code=djl9ikmkmefa44&preview_pb=0&sharer_language=en&_d=e8f03lm7cdd3g8&share_item_id=7272799622198807814&source=h5_m×tamp=1693311131&user_id=6989266477879772165&sec_user_id=MS4wLjABAAAAn190Z7c2ZZOWZA0tw8ZymlFtBtIwR-TVQYCvSBsappPMOr9LC3EVap_VrvzZ9E4J&social_share_type=0&utm_source=telegram&utm_campaign=client_share&utm_medium=android&share_iid=7246126020594796294&share_link_id=394e411e-6be3-4a90-9278-31110f79556b&share_app_id=1233&ugbiz_name=Main&ug_btm=b8727%2Cb2878


#ስለምን_ወደድከኝ???
ፍቅርህን ዘንግቼ ከመንገድ ወጥቼ፤
ትዕዛዝህን ጥሼ ከበለስ በልቼ፤
እንዲያ እያሳዘንኩህ ሁሌ እየበደልኩህ፤
ስለምነው ጌታ ያልቀነሰው ፍቅርህ?
✞✞✞
በጥበብ በተአምር ያዳንከኝ ከሞቴ፤
ነጻ ሁን ልጄ ያልከኝ ፈተህ ከእስራቴ፤
የምታስብልኝ ሁሌም ለህይወቴ፤
ስለምነው ጌታ የሆንክ መድኃኒቴ?
✞✞✞
ከተጠመደልኝ ከጠላቴ ወጥመድ፤
በፍቅር ያወጣኸኝ ከክፋ ሞት መንገድ፤
ማንም በሌለበት ሚያድነኝ ከጎኔ፤
ስለምን አዳንከኝ ታደግከኝ መድኅኔ?
✞✞✞
ለማዳንህ ምክንያት
ለመውደድህ ሥራ፤
መች ልቦና አለኝ ከኃጢአት የጠራ፤
እኮ ለምን ወደድከኝ ለምንስ አዳንከኝ?
ወድቄ ሳለሁኝ ለምን አነሳኸኝ?
ስለኔ ሞት ብለህ ስለምን ሞትክልኝ?
✞✞✞
ኃጢአትን ስሰራ አይተህ እንዳላየህ፤
ሁሌም ስበድልህ በትዕግስት እያለፍክ፤
ሰው የነፈገኝን ብዙ ዕድል ሰጥተኸኝ፤
ከሀሉ አብልጠህ በፍቅር ያየኸኝ፤
ስለምነው ጌታ እንዲያ የወደድከኝ?
✞✞✞
በፅድቅ ጥም እንዳልሞት
በዓለም በረሃ፤
እርካታን ልትሰጠኝ ሆነህ
የህይወት ዉሃ፤
ዕድሜ ለንስሃ ዘመን ለፍስሃ
ሁሉንም ያደልከኝ አድርገህ አምኃ
በዘመኔ ሁሉ ላንተ ጥያቄ አለኝ?
ስለምነው ጌታ ከጥልቁ ያወጣኸኝ?
✞✞✞
አላውቅም!!! እኔ ይሔን አላውቅም!!!
መውደድህ በምክንያት
ሊገደብ አይችልም፤
ኧኽ መቼም ይሔ የሆነው
በጽድቄ ነው አልልም፤
ዛሬ ስለዳንኩኝ ኃጢአቴን አልክድም፤
✞✞✞
ስለ ፍጹም ፍቅርህ ስለድንቅ ውለታህ፤
መድኃኔዓለም ሆይ ላንተ
ምን ልክፈልህ?
ዕንባ እየቀደመኝ ሰግጄ በፊትህ፤
ቢያንስብህም እንኳ
ሰላም እንዲሰማኝ ተመስገን ልበልህ።
ተመስገን!!!
✍ሄኖክ ክበበው
24/06/2012
✍ሄኖክ ክበበው
https://telegram.me/felege_tibeb












#ልዪ_ነህ_ገብርኤል
ገ=ገብቶናል ማዳንህ፣ከ'ሳት እንዲያወጣ፤
ብ=ብርሃንህ ተገልጦ፣ምህረት እንዲያመጣ፤
ር=ርዳን ብለን ስንጮህ፣ስምህን ስንጠራ፤
ኤ=ኤሎህም ልኮሃል፣ተአምር እንድትሰራ፤
ል=ልዩ ነህ ገብርኤል ለሰዎች ስትራራ።
ሄኖክ ክበበው
አውደ Tibeb
https://t.me/felege_tibeb


#ብፅዕት_ሆይ ሉቃ 1:48
#ማርያም_ማርያም_ሲባል 'ሚቃጠል በጅምላ፤
#ባርነቱን አምኖ የተቀበለ ነው #ልጅ መባል የጠላ።
“የባሪያይቱን ውርደት ተመልክቶአልና። እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፤”
— ሉቃስ 1፥48
ሄኖክ ክበበው
አውደ Tibeb
https://t.me/felege_tibeb


#ስማችንን_መልስ
ያነሳህ ቢመስልህ ዐቢይ ኑፋቄ፣
አለማወቅህን ልንገርህ አጥብቄ፣
በጥርጣሬአቸው እውነትን ቢያብሉ፤
የቀደሙ አሳቾች ካንተ ብዙ ያውቃሉ፤
ሌላውን ተውና...
ስሙን የነጠቅከው #ዮናታን የሳኦል፤
ታላቅ መድኃኒትን አድርጓል ለእስራኤል።
ግለጥና አንብበው ይንገርህ ሣሙኤል፤(1ሣሙ 14:45)
በግብርህ ረክሰህ፣የእንጀራህን መሶብ፤
መድኃኒታችንን፣ማርያምን ስትከስ፤
አንተን ባይገባህም....
ከትርጓሜው ጋራ፣ይጣረሳልና፣ስማችንን መልስ።
“ሕዝቡም ሳኦልን፦ በውኑ በእስራኤል ዘንድ ታላቅ መድኃኒት ያደረገ ዮናታን ይሞታልን? ይህ አይሁን፤ ዛሬ ከእግዚአብሔር ጋር አድርጎአልና ሕያው እግዚአብሔርን! ከራሱ ጠጕር አንዲት በምድር ላይ አትወድቅም አሉት። ሕዝቡም እንዳይሞት ዮናታንን አዳነው።”
— 1ኛ ሳሙኤል 14፥45
ዮናታን መድኃኒት ከተባለ #መድኃኒታችን_ማርያም_መባል_ቢያንስባት_እንጂ_አይበዛባትም
የእንጀራህን መሶብ ያልኩት👉(ያው በሀሰት እየጠራኸውም ቢሆን በልጇ ስም በመነገድ እንጀራ እንደምትበላ ስለምናውቅ ነዎ ለእኛ ግን ድንግል ማርያም መሶበ ወርቅ የዘላለም ሕይወት እንጀራችን የኢየሱስ ክርስቶስ መገኛ ናት)
አውደ Tibeb
ሄኖክ ክበበው
ቴሌ ግራም
https://t.me/felege_tibeb


#ልጥራው_ሚካኤልን🥰🥰🥰
https://t.me/felege_tibeb


~#እይታ~~#reposted
የሚወደኝ ቢኖር
ገልጦ ያነበኛል
ያለብኝን ግድፈት
ሊሸፍን ይጥራል.......
እንድታረም ከጥፋቴ
እንድመለስ ከስህተቴ
እንድነሳ ከውድቀቴ
እንዳይጎድፍ ማንነቴ
ምንጊዜም ይመኛል
ራሴን ሳልገልጥለት
እሱ ብዙ ያውቀኛል!!!
~~~
ሚጠላኝም ካለ
ጥቂቱ ጉድፌን
ሊያጎላ የሾለ!!!
የሽፋኔን ስዕል
ላዩን ብቻ አይቶ
ውስጤን ሳያነበው
ማንነቴን ገልጦ
በጭፍን ጥላቻው
በስሜት ተመርቶ
ለዓለም ያወራል
"ስሁት! "ነው እያለ
"ክፋ ሰው ነው!" ይላል
በውሸት እየማለ!
ልክ ሆኜ ብኖር
ባልሳሳት እንኳ
ይውላል ከደጄ
ጥፋቴን ሲያንኳኳ
ጥቂቱ ጉድፌን
ለሌላው ሊያውካካ
አጉልቶ ያሳየኛል
መውደቂያዬን ብቻ
ከሰነፎች ተርታ
እንደሌለኝ አቻ
~~~~~
እኔነቴን ሳያወቅ
ፊት ገፄን አንብቦ
በተንኮል ምላሱ
ስድብ ተከናንቦ!
"ክፋ ነህ አትጠቅምም
ላንተም ሆነ ለሠው
አታገለግልም"
እያለ ይወቅሰኛል
ደርቦ ደራርቦ!
~~
ስለዚህ ምን ገዶኝ
ሰው እንዳያየኝ እከናነባለሁ
ማየት ስፈልግ ግን
ክንብንቤን እገልጣለሁ........
"መጥፍው"ልምድ ይሆናል
"ክፋው" ማስጠንቀቂያ
ገመድ ለማበጀት
ጥላቻን ማነቂያ!
ከ"ጥሩ "ሰው ደስታ
ከ"ምርጡ" ትዝታ
መርጬ እቀስማለሁ!
እንዳልታይ ሆኜ
ራሴን ጨምሮ
ብዙ ሰው አያለሁ!!!
ሄኖክ ክበበው
አውደ Tibeb
(H~K)25_12_2010
https://t.me/felege_tibeb




#ይነጋል!!!
.....(✍በሄኖክ ክበበው)......
ህይወት ብትከበብ
በድቅድቅ ጨለማ፤
በሌት ተስፋ ሌቦች ልብ ብትደማ፤
ድረሱልኝ ስትል ጭራሽ ባትሰማ፤
ላትደመጥ እሪ ብትል.....
ብታቃስት በሀዘን ዜማ፤
..........ሳግ ቢተናነቃት፣
...ቢጨንቃት ቢጠባት፣
.......ሰው ያልሰማውን፣
......... ወገን ያላየውን፣
.......ጥሎት የሄደውን፣
.........ፈጣሪ ያየውና፤
በተስፋ ይነቃል ሌቱ ይነጋና።
..........#ይነጋል!!!...........
ራዕዬ ብትቆስል
በክፋ ሀሳብ ጩቤ፤
በተስፋ አምካኞች
ብትነረት ቀልቤ፤
ዙሪያዬ በሙሉ በሰው ተከብቤ፤
እንጀራ ብበላም ፍቅርን ተርቤ፤
ትራፊ እንኳ ሳጣ
ከወዳጅ መሶቤ፤
ባዶ ብትመለስ
ባትሞላም መረቤ፤
ሌትና ቀን ሚያፈራርቅ፣
የሚኮንን የሚያጸድቅ፣
ሆን ብሎ የማይጠላ፣
መረቤንም የሚሞላ፣
ፈጣሪዬ አይጨክንም፣
በጭለማ አይተወኝም፣
ለሌት አውሬ አይሰጠኝም፣
ብሩሁን ቀን አይነሳኝም።
..... .......#ይነጋል............
ዛሬዬ ቢጨልም ይነጋል ነገዬ፤
ታሪክ ሆኖ ይቀራል መከራ ስቃዬ።
ያኔ..................
"በኔ ችግር ሲተረቡ፣
ሲጨላልም ቤት የገቡ፣
በሰው እጦት 'ኔን ያስራቡ፣"
.................................
ይመጣሉ ከተስፋዬ ሊመገቡ።
.................................
የእውነት ይነጋል
አይቀርም ጨልሞ፤
እልፍ ፍሬ ያፈራል ደረቁ ለምልሞ።
✍ሄኖክ ክበበው
የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት
የፌስቡክ ገጻችንን ይውደዱ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
https://t.me/felege_tibeb


#እስከ_ማእዜኑ!!!
❤❤❤ክፍል ሁለት❤❤❤
...ማያዬን ብሰጥሽ፣ነጥዬ ከራሴ፤
ማንቢያዬን መልሰሽ፣ረጠበች ትራሴ፤
መበርቻዬን ወስደሽ፣ደከመች መንፈሴ፤
ውሎሽ ብቻ ሆነ፣ቅኔ መወድሴ፤
የጆሮዬ ረሃብ፣የዐይን ጥማቴ፤
የአካሌ መላወስ፣የርምጃ ሁነቴ፤
የመሞቴ መኖር፣ማያ ለእኔነቴ፤
ያንቺ ኑረት ሆኖ፣ሙሉ ማንነቴ፤
ትመጪ እንደው ሆኗል...
የለት መላምቴ፤
ምን አለብሽ አንቺ፣አንብበሽው ሳቂ፤
በመንፈስ ጠንስሰሽ፣ግጥሞቼን ጥመቂ፤
ከሁሉ በፊት ግን ይሕንን እወቂ..
....
ይቀጥላል
https://t.me/felege_tibeb


#ሳልበጠስ_ፍታኝ!!!
ክፍል አንድ
©ሄኖክ ክበበው
......................
ያኔ ትዝ ይልኃል...?
እኔን ባየህበት አፍታ፤
ልብህ በፍጥነህ ሲመታ፤
ድው..ድው....ድው.......
በለው...በለው..ኧረ ተው.....
ድም....ድም...ድም......
ብልጭ...ቡግግ..ድርግም....
ፍግም...ብቅ.....እልም.....
ሕምምምምምምም!!!
ስልኬን ለመጠየቅ፣የጣርክበት ጊዜ፤
በቃላቶችህ ላይ የዙረት አባዜ፤
ትዝ አለህ ያ ጊዜ?
😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭
ሳልጨርስ ዜሮ ብዬ፣
ስትተነፍስ በዙሪያዬ፣
ዘጠኝ ብዬ ስቀጥል፣
ቀልብህ በደስታ ሲቃጠል፤
በቁጥር ድርደራ ነፍስያህ ስትረካ፤
ዘለህ የተመለስከው አድማሷን ሳትነካ፤
ትዝ ይልኃል ያኔ ውብ ፊትህ ስትፈካ?
😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭
ከሰው ተሽቀዳድመህ፣
ከሰዓታቱ ፈጥነህ፣
በመጀመሪያ ቀን ስትደውል ወደኔ...
ሃ...ሎ...ስል.......
ይቀጥላል....
እያየን እንቀጥላለን
አውደ Tibeb
ቴሌግራም
https://t.me/felege_tibeb

Показано 20 последних публикаций.

686

подписчиков
Статистика канала