በስዕሉ ላይ የወጣትነትና የስተርጅና ሥዕሎች ይታያሉ፣ ጋሽ ስብሐት የጠላውና የተቸው ዕርጅና መጥቶ እፊቱ ገጭ አለ። ጋሽ ስብሐት በመስተዋት ራሱን እያየ በርጅናው ይቀልድ እንደነበረ ይወሳል፣ ቀስ ብሎ ራሱንና ፊቱን እያሻሸ፦
"ተይኮ ተይኮ ተይኮ ተይኮ
እኔ ሰሞንኛ ቆራቢ ነኝኮ
እያሉ በናፍቆት መሰንቋቸው
ወጣትነቴን አስታወሱኝ
ባይቀሰቅሱኝ ምንቸገራቸው?
ውብ ወጣትነቴ ሄደች
እየተንሳፈፈች
ያመጣት የግዜ ወንዝ ወሰዳት
እንግዲህ
ቀስ በቀስ
ሳይታወቀኝ
ግንባሬ እየገፋ
በራዬ እየሰፋ
ሽበቴ እየበዛ
ዕድሜዬ እየገፋ ሄደ
አልፈልግም እምቢ
ማርጀት አልፈልግም
መሞት አልፈልግም
እምቢ አልፈልግም
እምቢ እምቢ እምቢ"
ብሎ ነበር በሌሊቱ አይነጋልኝ ሌላው መፅሐፉ። ዋ! ጋሽ ስብሐት ምስኪንና አሳዛኝ ሠው፣ እምቢ አላረጅም አለ ግን አረጀ፣ እምቢ አልሞትም አለ ግን ሞተ።
ነፍስ ይማር እንላለን፣ ትኩሳት እንደ ተገለፀው ትምህርት አዘል ነው፣ ወጣትነታችሁን ተንከባከቡ ይላል፣ እንዴት ? አንብቡ መልሱ እዚያው አለ።
በቸር እንሰንብት።
"ተይኮ ተይኮ ተይኮ ተይኮ
እኔ ሰሞንኛ ቆራቢ ነኝኮ
እያሉ በናፍቆት መሰንቋቸው
ወጣትነቴን አስታወሱኝ
ባይቀሰቅሱኝ ምንቸገራቸው?
ውብ ወጣትነቴ ሄደች
እየተንሳፈፈች
ያመጣት የግዜ ወንዝ ወሰዳት
እንግዲህ
ቀስ በቀስ
ሳይታወቀኝ
ግንባሬ እየገፋ
በራዬ እየሰፋ
ሽበቴ እየበዛ
ዕድሜዬ እየገፋ ሄደ
አልፈልግም እምቢ
ማርጀት አልፈልግም
መሞት አልፈልግም
እምቢ አልፈልግም
እምቢ እምቢ እምቢ"
ብሎ ነበር በሌሊቱ አይነጋልኝ ሌላው መፅሐፉ። ዋ! ጋሽ ስብሐት ምስኪንና አሳዛኝ ሠው፣ እምቢ አላረጅም አለ ግን አረጀ፣ እምቢ አልሞትም አለ ግን ሞተ።
ነፍስ ይማር እንላለን፣ ትኩሳት እንደ ተገለፀው ትምህርት አዘል ነው፣ ወጣትነታችሁን ተንከባከቡ ይላል፣ እንዴት ? አንብቡ መልሱ እዚያው አለ።
በቸር እንሰንብት።