#አሁንና_በመጨረሻ
*****
ይህቺ ዓለም ለማንም ደንታ የላትም ። አንተም ለእሷ ደንታ አይኑርህ ። አንተ ኖርክ አልኖርክ ይህቺ ዓለም ምንም አይመስላትም ። አንተ ቁጥር ነህ ። እንዳንተ አይነት የትዬለሌ ሚሊዮኖች በዚያ መንገድ አልፈዋል ። በሚሊዮኖች ከሚቆጠሩት መሀል አንተ አንዱ ቁጥር ነህ ። ማንም ከዚያ መሀል አንተን ለይቶ አያውቅህም ። ስጋ የለህም ፤ ውበት የለህም ፤ ሀብት የለህም ፤ ልጆች የሉህም ፤ እውቀት የለህም ፤ ዝና የለህም ። ምንም የለህም ። አንተ ራስህ የለህም ። ቦርጭህ ፣ ቁመናህ ፣ ዳሌዋ ፣ ሽንጧ ፣ ስንቱን ያደባደበ ውበት ደም ግባቷ ፣ " በየት አለፈች ? " ያስባለ መልኳ በመጨረሻ አንዱ ጋ አፈር ውስጥ ተጥሎ ሁሉም ረግፎ አንዱ ከሌላው የማይለይ ያገጠጠ አጥንት ሆኖ ይቀራል ። ነበር ነህ አንተ ። ነበርሽ ነሽ አንቺ ። ዓለምን በጥፍርህ ቆንጥጠህ የያዝካት የሚመስልህ ነገር በመጨረሻ በቃ ምንም አይደለም ። አንተም ራስህ ምንም አይደለህም ።
" እፀድቃለሁ " እና " እኮነናለሁ " ን ተወው ። እሱ ባንተ እጅ አይደለም ። በሰሪው እጅ ነው ። ራስህን የማታውቅ ፍጡር የሰሪውን ሀሳብ ልትረዳ አትችልም ። አሁን ነህ አንተ ። ነገ አይደለህም ። ነገ የለህም ። ደግ ብትሆን ፤ መልካም ብትሆን ለአሁን ነው ። ለጽድቅ አይደለም ። አሁን ላይ መልካምነት የሚባል የብዙሀን ስምምነት አለ ። ለእሱ ተዘጋጅ ። ነገን ተወው ። ከሞትክ በኋላ የሚሆነውን በማሰብ ጊዜህን አታቃጥል ። ስለማታውቀው ነገ በማሰብ የምታውቀው ዛሬን አታበላሽ ። ከቻልክ ዛሬህ ነገህን እንዲሰራ አድርገው ። ዛሬን ስራው ። ዛሬ አይቆጭህ ። ዛሬህ ተስፋ መሆን ባይችል እንኳን ፀፀት አታድርገው ። ዓለምን ልቀቃት ። ለህሊናህ እንጂ ለዓለም አትጨነቅ ። ዓለምን ለመለወጥ አትነሳ ። ማንም ዓለምን የለወጠ ግለሰብ የለም ። ይልቁን ህሊናህን ለመለወጥ ተነሳ ። ህሊናህ ነው ዓለም ።
አንተ አሁን ማንንም ሁን ። በመጨረሻ ግን ከታች በምስሉ የምታየውን ነህ ። የአሁን ማንነቴ በስተ ቀኝ የተኛው እንደሚሆን በየዕለቱ አስባለሁ ። ማን እንደዚያ ያልሆነ ፤ የማይሆን አለ ? ማንም የለም ። ለወሬ ነጋሪ የሚቀር እንኳን ማንም የለም ። ጠቅላይ ሚኒስትሩን ሁን ፣ ጳጳሱን ሁን ፣ ቱጃሩን ሁን ፣ ማንንም ሁን ፣ ምንንም ሁን ፤ በመጨረሻ ከታች ያለውን ነህ ። ብትፈልግ ለመርሳት ሞክር ። ግን ምንም አይረዳህም ። አይቀርልህም ። እንዳለመታደል ሆኖ ብዙ ሰው መርሳት የሚፈልገው ይህንን ነው ። ለዚህም ይሆናል ክፋታችን የበዛው ። ብትፈልገውም ብትጠላውም በመጨረሻ ላይ " አስከፊ " ውን ምስል ነህ ። እሱን መርሳት ነው ህሊናችንን ሆድ የሚያደርገው ። አፈር ቤት በለው ሰማይ ቤት መቆጨት መናደድ የለም ። መመለስ የለም ። ስህተትን ማረም የለም ። ያኔ ቢቆጭህ የሚቆጭህን ዛሬ አስወግደው ። አውቀን እየካድነው እንጂ ክፋት ይታወቃል ። ሰውን ማስቀየም ፣ ሰውን መበደል ይታወቃል ። እሱን ታገል ።
ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
*****
ይህቺ ዓለም ለማንም ደንታ የላትም ። አንተም ለእሷ ደንታ አይኑርህ ። አንተ ኖርክ አልኖርክ ይህቺ ዓለም ምንም አይመስላትም ። አንተ ቁጥር ነህ ። እንዳንተ አይነት የትዬለሌ ሚሊዮኖች በዚያ መንገድ አልፈዋል ። በሚሊዮኖች ከሚቆጠሩት መሀል አንተ አንዱ ቁጥር ነህ ። ማንም ከዚያ መሀል አንተን ለይቶ አያውቅህም ። ስጋ የለህም ፤ ውበት የለህም ፤ ሀብት የለህም ፤ ልጆች የሉህም ፤ እውቀት የለህም ፤ ዝና የለህም ። ምንም የለህም ። አንተ ራስህ የለህም ። ቦርጭህ ፣ ቁመናህ ፣ ዳሌዋ ፣ ሽንጧ ፣ ስንቱን ያደባደበ ውበት ደም ግባቷ ፣ " በየት አለፈች ? " ያስባለ መልኳ በመጨረሻ አንዱ ጋ አፈር ውስጥ ተጥሎ ሁሉም ረግፎ አንዱ ከሌላው የማይለይ ያገጠጠ አጥንት ሆኖ ይቀራል ። ነበር ነህ አንተ ። ነበርሽ ነሽ አንቺ ። ዓለምን በጥፍርህ ቆንጥጠህ የያዝካት የሚመስልህ ነገር በመጨረሻ በቃ ምንም አይደለም ። አንተም ራስህ ምንም አይደለህም ።
" እፀድቃለሁ " እና " እኮነናለሁ " ን ተወው ። እሱ ባንተ እጅ አይደለም ። በሰሪው እጅ ነው ። ራስህን የማታውቅ ፍጡር የሰሪውን ሀሳብ ልትረዳ አትችልም ። አሁን ነህ አንተ ። ነገ አይደለህም ። ነገ የለህም ። ደግ ብትሆን ፤ መልካም ብትሆን ለአሁን ነው ። ለጽድቅ አይደለም ። አሁን ላይ መልካምነት የሚባል የብዙሀን ስምምነት አለ ። ለእሱ ተዘጋጅ ። ነገን ተወው ። ከሞትክ በኋላ የሚሆነውን በማሰብ ጊዜህን አታቃጥል ። ስለማታውቀው ነገ በማሰብ የምታውቀው ዛሬን አታበላሽ ። ከቻልክ ዛሬህ ነገህን እንዲሰራ አድርገው ። ዛሬን ስራው ። ዛሬ አይቆጭህ ። ዛሬህ ተስፋ መሆን ባይችል እንኳን ፀፀት አታድርገው ። ዓለምን ልቀቃት ። ለህሊናህ እንጂ ለዓለም አትጨነቅ ። ዓለምን ለመለወጥ አትነሳ ። ማንም ዓለምን የለወጠ ግለሰብ የለም ። ይልቁን ህሊናህን ለመለወጥ ተነሳ ። ህሊናህ ነው ዓለም ።
አንተ አሁን ማንንም ሁን ። በመጨረሻ ግን ከታች በምስሉ የምታየውን ነህ ። የአሁን ማንነቴ በስተ ቀኝ የተኛው እንደሚሆን በየዕለቱ አስባለሁ ። ማን እንደዚያ ያልሆነ ፤ የማይሆን አለ ? ማንም የለም ። ለወሬ ነጋሪ የሚቀር እንኳን ማንም የለም ። ጠቅላይ ሚኒስትሩን ሁን ፣ ጳጳሱን ሁን ፣ ቱጃሩን ሁን ፣ ማንንም ሁን ፣ ምንንም ሁን ፤ በመጨረሻ ከታች ያለውን ነህ ። ብትፈልግ ለመርሳት ሞክር ። ግን ምንም አይረዳህም ። አይቀርልህም ። እንዳለመታደል ሆኖ ብዙ ሰው መርሳት የሚፈልገው ይህንን ነው ። ለዚህም ይሆናል ክፋታችን የበዛው ። ብትፈልገውም ብትጠላውም በመጨረሻ ላይ " አስከፊ " ውን ምስል ነህ ። እሱን መርሳት ነው ህሊናችንን ሆድ የሚያደርገው ። አፈር ቤት በለው ሰማይ ቤት መቆጨት መናደድ የለም ። መመለስ የለም ። ስህተትን ማረም የለም ። ያኔ ቢቆጭህ የሚቆጭህን ዛሬ አስወግደው ። አውቀን እየካድነው እንጂ ክፋት ይታወቃል ። ሰውን ማስቀየም ፣ ሰውን መበደል ይታወቃል ። እሱን ታገል ።
ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ