በሐመር ወረዳ ሴቶች በሕይወት ለሌለ ሰው ተድረው ከሟች ዘመድ እንዲወልዱ የሚያደርገው ባህላዊ ስርዓት መቀጠሉ ተገለጸ
👉በወረዳው በሩብ ዓመቱ ሦስት ሴቶች በሕይወት ለሌሉ ወንዶች ተድረዋል
በደቡብ ኦሞ ዞን ሐመር ወረዳ ሴቶች ለሞተ ሰው ተድረው ከሟች ዘመድ እንዲወልዱ የሚያደርገው ባህላዊ ስርዓት መቀጠሉን የወረዳው ሴቶችና ሕጻናት ጉዳይ ቢሮ አስታውቋል።
"በወረዳው 'ኮይካ' ወይም ጥሎሽ ለማግኘት ሲባል ሴት ልጅ አትማርም፤ ይህም ብቻ ሳይሆን ሴት ልጅ የገቢ ምንጭ ተደርጋ በእርሷ ገቢ ወንድ ልጅ እንዲያገባ ይደረጋል" ሲሉ፤ በቢሮው የሴቶችና ሕጻናት መብት ደህንነት ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ የሆኑት ወይዘሮ ሙሉነሽ ጨረና ለአሐዱ ተናግረዋል።
ይህንን ተከትሎም በወረዳው ያለእድሜ ጋብቻ በስፋት እየተስተዋለ መሆኑን ቡድን መሪዋ ገልጸዋል።
"በተለይም ደግሞ ለ'ቦርከካ' ወይም ለሞተ ሰው ይዳራሉ፤ ይህ የሚሆነው ለሞተ ሰው ሚስት መኖር አለበት በሚል ምክንያት" እንደሆነ የተናገሩት ወ/ሮ ሙሉነሽ፤ "በዚህ ሳያበቃ ሴቷ ከሟች ዘመድ እንድትወልድ ተደርጎ የሚወለደው ልጅ በሞተው ሰው ሥም እንዲጠራ ይደረጋል" ብለዋል።
በዚህም በወረዳው በ2017 ሩብ ዓመት ሦስት ሴቶች በሕይወት ለሌሉ ወንዶች መዳራቸውን ተናግረዋል።
"በሌላ በኩልም ያለአቻ ጋብቻ በሐመር ወረዳ ከሚታዩ ችግሮች አንዱ ነው" ያሉም ሲሆን፤ በጣም በእድሜ የገፋ አባት ከስምንት ዓመት ሕጻን ልጅ ጀምሮ እንደሚያገባ ገልጸዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ አንድ ሰው ሃብት ካለው፤ ድርብ ጋብቻ ወይም ሁለት ሚስት እንደሚኖረው አስረድተዋል፡፡
በተጨማሪም በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ ወንድ ልጅ የሚያገባው ከብት መዝለል ሲችል ብቻ መሆኑን በመግለጽ፤ "በዚህ የተነሳ ለወንዱ ቤተሰቦች እንደ ስጦታ የሚታሰብ እናቶችን ጨምሮ ሴቶች ይገረፋሉ" ብለዋል።
በዚህ ምክንያት የሚገረፉ ሴቶች ሰውነት ስለሚተለተል የእጅና የጡት አካል መጉደልን ጨምሮ በሕመም ሲሰቃዩ ቆይተው ሕይወታቸውን የሚያጡ ሴቶች እንዳሉ ተናግረዋል።
"ይህን መሰሉ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በወረዳው በስፋት ይስተዋላል" የሚሉት ወይዘሮ ሙሉነሽ፤ ሴት ልጆች ወደ ትምህርት ቤት እንደማይላኩም ጨምረው ገልጸዋል።
ወደ ትምህርት ቤት የማይላኩበትን ምክንያት ሲያስረዱም፤ "ሕጻናት ቶሎ ታጭተው ከጥሎሽ ከብት፣ ፍየል፣ ማር እና የተለያዩ መሳሪያዎች የሚገኙ በመሆኑ ነው" ብለዋል።
"ትልቁና ዋነኛው ችግር ሴት ልጅን አሳንሶ ማየት ነው" ያሉት ቡድን መሪዋ፤ ሴት የንብረት ባለቤትነት እንደሌላትም ገልጸዋል።
"ችግሩን ለመቅረፍ ከግንዛቤ መፍጠር ጀምሮ የተወሰኑ ሥራዎች ቢሰሩም፤ ጠንከር ያለ ሥራ ተስራቷል ለማለት አያስደፍርም" ሲሉም ለአሐዱ ተናግረዋል።
በተጨማሪም "ከጎጂ ልማዳዊ ድርጊቱ ጋር ተያይዞ በተፈጠረላቸው ግንዛቤ መሻሻሎችን ያሳዩ አካላትም የማበረታቻ ድጋፍ አልተደረገላቸውም" ብለዋል።
(አሐዱ ሬዲዮ)
👉በወረዳው በሩብ ዓመቱ ሦስት ሴቶች በሕይወት ለሌሉ ወንዶች ተድረዋል
በደቡብ ኦሞ ዞን ሐመር ወረዳ ሴቶች ለሞተ ሰው ተድረው ከሟች ዘመድ እንዲወልዱ የሚያደርገው ባህላዊ ስርዓት መቀጠሉን የወረዳው ሴቶችና ሕጻናት ጉዳይ ቢሮ አስታውቋል።
"በወረዳው 'ኮይካ' ወይም ጥሎሽ ለማግኘት ሲባል ሴት ልጅ አትማርም፤ ይህም ብቻ ሳይሆን ሴት ልጅ የገቢ ምንጭ ተደርጋ በእርሷ ገቢ ወንድ ልጅ እንዲያገባ ይደረጋል" ሲሉ፤ በቢሮው የሴቶችና ሕጻናት መብት ደህንነት ዳይሬክቶሬት ቡድን መሪ የሆኑት ወይዘሮ ሙሉነሽ ጨረና ለአሐዱ ተናግረዋል።
ይህንን ተከትሎም በወረዳው ያለእድሜ ጋብቻ በስፋት እየተስተዋለ መሆኑን ቡድን መሪዋ ገልጸዋል።
"በተለይም ደግሞ ለ'ቦርከካ' ወይም ለሞተ ሰው ይዳራሉ፤ ይህ የሚሆነው ለሞተ ሰው ሚስት መኖር አለበት በሚል ምክንያት" እንደሆነ የተናገሩት ወ/ሮ ሙሉነሽ፤ "በዚህ ሳያበቃ ሴቷ ከሟች ዘመድ እንድትወልድ ተደርጎ የሚወለደው ልጅ በሞተው ሰው ሥም እንዲጠራ ይደረጋል" ብለዋል።
በዚህም በወረዳው በ2017 ሩብ ዓመት ሦስት ሴቶች በሕይወት ለሌሉ ወንዶች መዳራቸውን ተናግረዋል።
"በሌላ በኩልም ያለአቻ ጋብቻ በሐመር ወረዳ ከሚታዩ ችግሮች አንዱ ነው" ያሉም ሲሆን፤ በጣም በእድሜ የገፋ አባት ከስምንት ዓመት ሕጻን ልጅ ጀምሮ እንደሚያገባ ገልጸዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ አንድ ሰው ሃብት ካለው፤ ድርብ ጋብቻ ወይም ሁለት ሚስት እንደሚኖረው አስረድተዋል፡፡
በተጨማሪም በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ ወንድ ልጅ የሚያገባው ከብት መዝለል ሲችል ብቻ መሆኑን በመግለጽ፤ "በዚህ የተነሳ ለወንዱ ቤተሰቦች እንደ ስጦታ የሚታሰብ እናቶችን ጨምሮ ሴቶች ይገረፋሉ" ብለዋል።
በዚህ ምክንያት የሚገረፉ ሴቶች ሰውነት ስለሚተለተል የእጅና የጡት አካል መጉደልን ጨምሮ በሕመም ሲሰቃዩ ቆይተው ሕይወታቸውን የሚያጡ ሴቶች እንዳሉ ተናግረዋል።
"ይህን መሰሉ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊት በወረዳው በስፋት ይስተዋላል" የሚሉት ወይዘሮ ሙሉነሽ፤ ሴት ልጆች ወደ ትምህርት ቤት እንደማይላኩም ጨምረው ገልጸዋል።
ወደ ትምህርት ቤት የማይላኩበትን ምክንያት ሲያስረዱም፤ "ሕጻናት ቶሎ ታጭተው ከጥሎሽ ከብት፣ ፍየል፣ ማር እና የተለያዩ መሳሪያዎች የሚገኙ በመሆኑ ነው" ብለዋል።
"ትልቁና ዋነኛው ችግር ሴት ልጅን አሳንሶ ማየት ነው" ያሉት ቡድን መሪዋ፤ ሴት የንብረት ባለቤትነት እንደሌላትም ገልጸዋል።
"ችግሩን ለመቅረፍ ከግንዛቤ መፍጠር ጀምሮ የተወሰኑ ሥራዎች ቢሰሩም፤ ጠንከር ያለ ሥራ ተስራቷል ለማለት አያስደፍርም" ሲሉም ለአሐዱ ተናግረዋል።
በተጨማሪም "ከጎጂ ልማዳዊ ድርጊቱ ጋር ተያይዞ በተፈጠረላቸው ግንዛቤ መሻሻሎችን ያሳዩ አካላትም የማበረታቻ ድጋፍ አልተደረገላቸውም" ብለዋል።
(አሐዱ ሬዲዮ)