[ኢብን ሽፋ - Ibn Shifa]


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


እራስህን ሁል ጊዜ ለቁርኣንና ለሀዲስ ተጎታች አድርግ!
በአንድ ነገር ላይ ከቁርኣንና ከሀዲስ ማስረጃ ሳታገኝ አቋም አትያዝ!
ሁሌም ለሰዎች መልካምን ተመኝ!
ለሀቅ እንጂ ለሰዎች ወጋኝ አትሁን

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций




👉 መልሰው እንዳይደውሉ

አስቸኳይ መልዕክት!

እባካችሁ  ይህንን መልዕክት ለቤተሰብዎና ጓደኛዎ ያስተላልፉ!

ሰሞኑን አንዳንድ ህብረተሰቦች ከማይታወቁ ግለሰቦች ስልክ ጥሪ እየደረሳቸው እንደሆነና ስልክ ቁጥሩም፡፣
      Tel:
+375602605281
       Tel:
+37127913091
       Tel:
+37178565072
       Tel:
+56322553736
       Tel:
+37052529259
       Tel:
+255901130460
ወይም ማንኛውም ቁጥር በ+371,+375,+381የሚጀምሩ እንደሆነ አሳውቀዋል።
    እነዚህን ስልክ ቁጥር የሚጠቀሙት ግለሰቦች ሲደውሉ አንዴ ብቻ ከጠራ ብኋላ ይዘጉታል።
እርስዎ መልሰው ሲደውሉ የርስዎን Contact List በ 3sec ውስጥ ወደ ራሳቸው ኮፒ በማድረግ እንዲሁ ሞባዬልዎ ላይ ስለ እርስዎ ባንክ ወይም ክሪዴት ካርድ መረጃ በአንዴ በመጥለፍ የማጭበርበር ስራ እየሰሩ ይገኛሉ።ከላይ በተጠቀሱት ስልክ ቁጥር ከተደወለሎት አይመልሱ ፡ወይም መልሰው አይደውሉ።እንዲሁም በማንኛውም ደዋይ #90 or #09 በመስመር እንዲነኩ ከተጠየቁ አይንኩ።ምክንያቱም በቀላሉ ሲማችሁን አክሰስ(በመጠቀም)  በናንተ ስም የፈለጉት ወንጀል በመስራት እራሳቸውን ስለሚሸሽጉ ነው።  
ይህንን መልዕክት ለቻላችሁ ሰው ፎርዋርድ በማረግ ህዝባችንን ከዚ መሰል ማጭበርበሮች እንታደግ።


     🔹 መረጃው የህግ ባለሞያው የወንድማችን መህዲ ነው ።

https://t.me/bahruteka






قال شيخ الإسلام ابن تيمية رحمه الله :-

" ‏وكان أصحابه رضي الله عنهم يبتلون بأنواع من البلاء بعد موته فتارة بالجدب وتارة بنقص الرزق وتارة بالخوف وقوة العدو وتارة بالذنوب والمعاصي ولم يكن أحد منهم يأتي إلى قبر الرسول ﷺ ولا قبر الخليل ولا قبر أحد من الأنبياء فيقول : نشكو إليك جدب الزمان أو قوة العدو أو كثرة الذنوب ولا يقول : سل الله لنا أو لأمتك أن يرزقهم أو ينصرهم أو يغفر لهم ؛ بل هذا وما يشبهه من البدع المحدثة التي لم يستحبها أحد من أئمة المسلمين فليست واجبة ولا مستحبة باتفاق أئمة المسلمين."

[مجموع الفتاوى (جـ١صـ١٦١)]


ልዩ የሙሃዶራ ፕሮግራም በስልጤ ዞን ምስራቅ አዘርነት ወረዳ

👉 ነገ እለተ  እሁድ 19 /2017
ከጠዋቱ 3:00 ሰኣት ጀምሮ

ቦታ:- ስልጤ ዞን ምስራቅ አዘርነት ታች ኡምናን ቀበሌ ባረማር ሐጂ ከማል መስጂድ

የእለቱ ተጋባዠ መሻይኾችና
ኡስታዞች


🔹1 ታላቁ አሊም ሸይኽ ዐብዱልሀሚድ አልተሚይ (ሀፊዘሁላህ)
🔹2 ሸይኽ መህቡብ ከሳንኩራ ሀፊዘሁሏህ
🔸3 ኡስታዝ ሰይፈዲን ሳኒ ከወላይታ (ሀፊዘሁላህ)
🔸4 ኡስታዝ ዒዙዲን ከሁልባራግ (ሀፊዘሁላህ)
  🔸5 ኡስታዝ ባህረዲን አወል ከቂልጦ (ሀፊዘሁላህ)


ለሴቶችም በቂ ቦታ ስላለን ተጋብዛችኋል

በተውሂድና በሡና አምራ እና ተውባ ደምቃ
ትውላለች

በቦታው ለማትገኙ በዚህ ቻናል ቀጥታ LIVE ይተላለፋል ኢንሽ አሏህ
👇👇👇
#join ⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa






ኢንሻአላህ ከሶላት በኋላ ይቀጥላል ሳትርቁ ጠብቁን




السلام عليكم ورحمة الله وبركاته

🌹🎤🎤🎤🎤🎤

    ‼️ አዋጅ አዋጅ  ድንገተኛ ልዩና
   ታላቅ   የሙህዷራ ፕሮግራም  እንደተሰናዳላች ስናበስራቹ በታላቅ ደስታ ነው

👉 ዛሬ  ቅዳሜ 18 /2017

ፕሮግራሙ  የሚካሄድበት ቦታ ስልጤ ዞን
  ታች አዳዘር አቢቴ በሚባለው ቀበሌ  ትልቁ መስጂድ

ተጀምሯል

የእለቱ ተጋባዠ መሻይኾችና
ኡስታዞች


🔹1 ታላቁ አሊም ሸይኽ ዐብዱልሀሚድ አልተሚይ (ሀፊዘሁላህ)
🔹2 ሸይኽ መህቡብ ከሳንኩራ ሀፊዘሁሏህ
🔸3 ኡስታዝ ሰይፈዲን ሳኒ ከወላይታ (ሀፊዘሁላህ)
  🔸4 ኡስታዝ በህረዲን አወል ከቂልጦ (ሀፊዘሁላህ)


ለሴቶችም በቂ ቦታ ስላለን ተጋብዛችኋል
ዛሬ ታች አዳዘር አቢቴ ቀበሌ

በተውሂድና በሡና አምራ እና ተውባ ደምቃ
ትውላለች

በቦታው ለማትገኙ በዚህ ቻናል ቀጥታ LVE ይተላለፋል ኢንሽ አሏህ
ተከታተሉ 👇👇👇
https://t.me/IbnShifa?livestream=bd56f5cca148c8dca4

#join ⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa


የሀገራችን መሐዲስ የሆኑት የሸይኽ አሕመድ ወተር ፈትዋ
"""""""
➢ ሰለፊየህ ማለት፡ የሰለፎችን መንገድ መከተል ሲሆን፣እንዲሁም የሰለፊየህ ጎዳና ትክክለኛ ጎዳና እንደሆነ፣ሰለፊይነት በስም ብቻ ሳይሆን በቃልና በተግባር እንደሆነ አብራርተዋል።

➢  እናንተ "ሰለፊየህ" ብሎ መጠራት (መሰየም) አይበቃም ለምትሉ ሁሉ፣ ይሄው ይህ ታላቁ ሸይኽ "ሰለፊየህ" ብሎ መጠራት (መሰየም) ይቻላል እያሉ ነው። በዚህ ዙሪያ ምን ትላላችሁ?

➢ "ሰለፊየህ" እንድና አንድ ብቻ እንደሆነችና፣እንዲሁም "አዲስ ሰለፊየህ" ሚባል ነገር እንደሌለ ሸይኹ አብራርተዋል!፤ ይህ በንዲህ እንዳለ፣ "ሰለፊየህ" አዲስ የተፈበረከ መንገድ ነው የምትሉ ሁሉ፣ይሄው የናንተ ንግግር ትክክል እንዳልሆነ ሸይኹ አስረግጠው እየነገሯችሁ ነው።

➢ "ኢኽዋን አል-ሙስሊሚን" የተሰኘው አንጃ፣ጠማማ ቡድንና እንዲሁም የሙስሊሞች ጠላት እንደሆኑ ሸይኹ አብራርተዋል።

➢  አሽ-ሸይኽ ሙሐመድ አማን አል-ጃሚን (ረሂመሁላሁ ተዓላ) የሚሳደቡና የሚተቹ "ኢኽዋኖች" እንደሆኑ ሸይኹ አብራርተዋል።

➢ በመጨረሻም በተለይ፣ "በአሰንዳቦ እና በአካባቢዋ" ለሚኖሩ ነዋሪዎች ይህ ታላቅ ሸይኽ የተናገሩትን ንግግር በአግባቡ አድምጣችሁ፣ በቅርብ ጊዜ እየተካሄደ ካለው ዘመቻ ጋር በማመሳከር ትክክለኛው መንገድ ልትለዩ ይገባል። በተለይም "ሰለፊያ" ተብሎ መጠራት አይቻልም ብለው ለሚነዙት... እንዲሁም የነኝህ ግለሰቦች ንግግር ትክክል እንዳልሆነ ሸይኽ በአግባቡ አብራርተዋል።

👌 አላህ "ሐቅን" ተገንዝበው ከሚከተሉት ያድርገን!፤እንዲሁም "ባጢልን" ተረድተው ከሚርቁት ያድርገን!

📝 ትርጉም: አቡ ሀፍሳህ
@semirEnglish


Репост из: BARNOOTA DIINAL ISLAAM(1)
Fatwaa muhaddisa biyya keenyaa Sheikh Ahmad watar
=============================

–Salafiyyaan jechuun karaa salafootaa hordofuu akka ta'e akkasumas Salafiyyaan karaa sirrii akka taate, Salafiyyummaan maqaa qofa osoo hin taane jechaa fi gochaan akka ta'es ibsanii jiru.
Mee warri salafiyyaa jedhanii of waamuun hin jirtu, mubtadi'oota jarri warri jettan Sheekni guddaan kunoo salafiyyaa jedhani of waamuun akka baqqa'u dubbataa jiru maal jettu kanarratti!!??

–Salafiyyaan tokkicha malee salafiyyaa jadiidaa/haaraa wanti jedhamu akka hin jirres dubbataniiru.
Asumaanuu warrii salafiyyaan haaraadha jettan dubbiin keessan Sirrii akka hin taane sheekni isinitti himaa jiru.

–Firqaan ikwaana_muslimaa jedhamtu xalaata/diina muslimaa akka taatee fi firqaa jaalattuu akka taates dubbataniiru.

–Warri Sheikh Muhammad amaan aljaamii arrabsu warra ikwaanaa akka ta'es ibsanii jiru.

–Dhuma irratti keessattuu jiraattoonni M/Asandaaboo fi naannawa ishii waan sheekni guddaan kun jedhan sirriitti dhaggeeffattanii waan dhiheenya kana deemaa tureen walbira qabdanii kamtu akka sirrii ita'e adda baafachuu qabdu.
Keessattuu dhiheenyuma kana "salafiyyaan jedhanii of waamuun hin jiru", "warri salafiyyaa mubtadi'oota" jedhamee dubbatamaa ture garu sheekni dubbiin kun sirrii akka hin taane dubbatanii jiru. Kam akka qabaachuu qabdanu isiniif dhiiseen jira Akka hojii manaatti.

RABBIIN NAMA HAQA HUBATEE HORDOFU, BAAXILAS HUBATEE NAMA IRRAA FAGAATU NUHAA GODHU!!

https://t.me/barnootadiinalislaam/4078


♻️  አዲስ ሙሓደራ

ወጣቶች ለተውሂድ መክፈል ያለባችሁ


🎙በተወዳጁ መካሪያችን ሸይኽ አቡዘር ሀሰን(حفظه الله)
 
📌   የ"አስሃቡል ከህፍ" ገድል በሰፊው የተወሳበት
📌  ቀደምቶች ለተውሂድ የከፈሉት ዋጋ
📌  ሁሉም ሰው የተውሂድ ተጣሪ መሆን እንዳለበት እና ሌሎች አንገብጋቢ መልዕክቶች በማራኪ አንደበት የተላለፉበት ድንቅ ሙሓደራ!
 

📍https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha


የእለተ ጁምዓ ሱንናዎችና ስርኣቶች
—————
መታጠብና መቀባባት
ከሰልማነል ፋሪሲይ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል አለ:- “አንድ ሰው በእለተ ጁምዓ ታጥቦ፣ ከመፀዳዳትም የቻለውንም ተፀዳድቶ፣ ከሚቀባባ ነገርም ተቀባብቶ፣ ቤቱ ውስጥ ከሚገኝ ሽቶ ተቀብቶ፣ ከዚያም ከቤቱ ወጥቶ በሁለት ሰዎች መካከል ካልለያየ፣ ከዚያም የተፃፈለትን ከሰገደ፣ ከዚያም ኢማሙ በተናገረ ጊዜ ዝም ካለ፣ በዚያች ጁምዓ እና በቀጣዩዋ ጁምዓ መካከል ያለውን ወንጀል ይቅር ይባላል።” [ቡኻሪ 883 ላይ ዘግበውታል]

ከሌላ ጊዜ የተሻለ ቆንጆ የሆነውን ልብስ መልበስ
ከሙሀመድ ኢብን የህያ ኢብን ሂባን (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “አንዳችሁ ለእለተ ጁምዓ ከሌላ ጊዜ የተሻሉ ሁለት ልብሶችን ብይዝ የተሻለ ነው” [አቡዳውድ 1078 ላይ የተዘገበ ሲሆን አልባኒ ሶሂህ ብለውታል]

በጊዜ ወደ መስጂድ መግባት
ከአቢሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “በእለተ ጁምዓ ለጀናባ የሚታጠብ አይነትን ትጥበት የታጠበ፣ ከዚያም (ወደ መስጂድ) የተጓዘ ሰው ልክ ግመል ለሶደቃ እንዳቀረበ ነው፣ በሁለተኛው ጊዜ ወደ መስጂድ የተጓዘ ሰው ልክ ለሶደቃ ከብት (ላም) እንዳቀረበ ነው፣ በሶስተኛው ጊዜ የተጓዘ ሰው ልክ ቀንዳማ የሆነ ሙክት እንዳቀረበ ነው፣ በአራተኛው ጊዜ ወደ መስጂድ የተጓዘ ሰው ለሶደቃ ዶሮ እንዳቀረበ ነው፣ በአምስተኛው ጊዜ ወደ መስጂድ የተጓዘ ሰው ለሶደቃ እንቁላል እንዳቀረበ ነው፣ ኢማሙ  ሚንበር ላይ ከወጣ መላኢካዎች ኹጥባውን ለማዳመጥ ይሳተፋሉ።” [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል]

መስጂድ ከገቡ በኋላ በሁለት ሰዎች መካከል አለመለያየት (በሁለት ሰዎች ትከሻ ላይ አለመረማመድ)
ጃቢር ኢብን ዐብደላህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ አለ:- የአላህ መልእክተኛ ﷺ እየኾጠቡ እያለ አንድ ሰው ገባ፣ ሰዎች ላይ እየተረማመደ ነበርና የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ አሉት:- “ቁጭ በል! በእርግጥም አስቸግረሃል አርፍደሃልም።” [ኢብን ማጀህ 923 ላይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒ ሀሰን ብለውታል]

ሱረቱል ከህፍን መቅራት (ማንበብ)
ከአቢ ሰዒድ አል-ኹድሪይ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “በእለተ ጁምዓ ሱረቱል ከህፍን ያነበበ ሰው በእርሱና በበይተል ዐቲቅ መካከል ብርሃን ይበራለታል።” [አልባኒ በሶሂሁል ጃሚዕ 6471 ላይ ሶሂህ ነው ብለውታል።]

ዱዓ ማብዛትና በእለተ ጁምዓ ዱዓ ተቀባይ የሚሆንባትን ሰኣት መጠባበቅ
ዐብደላህ ኢብኑ መስዑድ (ረዲየላሁ ዐንሁ)  የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል አለ:- “የጁምዓ ቀን አስራ ሁለት ሰኣት ነው፣ ከእርሷ ውስጥ አንዲት ሰኣት አለች ሙስሊም የሆነ ባሪያ በዚያች ሰኣት አላህን ከጠየቀ አላህ የጠየቀውን ይሰጠዋል፣ (ያቺን ሰኣት) በመጨረሻ ሰኣት ከአስር በኋላ አካባቢ ፈልጓት።” [ሶሂሁል ጃሚዕ 8190 ላይ አልባኒ ሶሂህ ነው ብለውታል።]

ከአነስ ኢብን ማሊክ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “የዱዓ ተቀባይነት የሚከጀልባትን ሰኣት ከአስር በኋላ ፀሀይ ወደ መግቢያዋ እስከምትቃረብ ድረስ ባለው ጊዜ ፈልጓት።” [ትርሚዚይ 1237 ላይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒ ሀሰን ብለውታል።]

በነቢዩ ﷺ ላይ ሶለዋት ማብዛት
ከሶፍዋን ኢብን ሱለይም (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “የጁምዓ ቀን እና የጁምዓ ሌሊት ከሆነ (ከገባ) በኔ ላይ ሶለዋት አብዙ።” [በሶሂሁል ጃሚዕ 776 ላይ አልባኒ ሶሂህ ብለውታል።]

ማሳሰቢያ:- ይህ ተግባር የሚመለከተው ወንዶችን ነው። በተለይ ሽቶ ተቀብቶ መውጣት ለሴት ልጅ ሙሉ በሙሉ ሀራም ነው። ሴቶች ምንም አይነት ጌጣጌጥ ያለውን እና ወንዶችን ሊፈትን የሚችል ልብስም ሆነ ሽታ ያለው ቅባትና ሽቶ ሳይጠቀሙ ሙሉ በሙሉ የሴቶችን ሸሪዓዊ ስርኣት ያሟላ አለባበስ ለብሰው በአደብ ወደ መስጂድ መሄዱ አይከለከሉም።
✍🏻ኢብን ሽፋ (t.me/ibnshifa)
የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችን ⤵️ #join በማድረግ ይቀላቀሉ
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa


Репост из: Bahiru Teka
🚫 ጥምር የመጅሊስ አመራሮች ምን እየሰሩ ነው ?

      ከአሕባሽና ሱፍይ ጋር የተደመሩት ኢኽዋንና ሙመዪዓዎች የመጅሊስ ወንበር ላይ ሲፈናጠጡ ለእስልምናና ሙስሊሞች እንደሚሰሩ ሲደሰኩሩ ሰፊሁ ህብረተሰብ በሐሴት ተሞልቶ ነበር ። ደስታቸውን በተለያየ መንገድ ሲገልፁ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው ። በተለይ የኢኽዋን የእንጀራ ልጆች የሆኑት ነሲሐዎች ደስታቸውን የገለፁበት መንገድ የሚገርም ነበር ።
   የተውሒድና ሱና የበላይነት የሚረጋገጥበት እድል እንተገኘ በማስመሰል በዚህ ያልተደሰተ ሙናፊቅ ነው እስከማለት የተደረሰበት ንቅናቄ ተደርጓል ። እንዳይፈረድባቸው የእንጀራ አባቶቻቸው በስሜት ስካር ውስጥ ሆነው " እንግዲህ እድሉ መጥቶልናል አሁን ያገኘነው እድል ሙሳም ቢመጡ ፣ ዒሳም ቢመጡ ፣ ነብዩና ሙሐመድም ቢመጡ ይህን እድል  …… " አናገኘውም ነበር በሚል መሀላ ሲደረድሩ ከዛሬ ጀምሮ ከናንተ ከኮሚቴዬች አንስቶ ሱፍይ ፣ ሰለፍይ ፣ ኢኽዋንይ የሚለውን መስማት አንፈልግም እኛ የኢትዮዽያ ሙስሊሞች ነን ሲሉ መስማታቸው እነርሱንም አስክሯቸው ሊሆን ይችላል ።
    የኢኽዋን መሪዮች የመጅሊሱን ወንበር ገና ከመፈናጠጣቸው የፈለገ መውሊድ ያውጣ የፈለገ ጫት ይቃም ብለው በአደባባይ በማወጅ አላማቸውና ፍላጎታቸው ምን እንደሆነ ሲገልፁ የስልጣን ፍርፋሬ የደረሳቸው ነሲሐዎች ምን እንደተሰማቸው ራሳቸው ይወቁ ። በአብዛኛው ምስኪን ተስፋ ላይ ግን ውሃ ነበር የቸለሱበት ። ራሱን እንዲጠይቅም አደረጉት ። ነገር ግን ማን ምን ሊያመጣ ዋናውን ስልጣን የተቆጣጠረው የኢኽዋን አንጃ ስልጣኑን ለማቆየት ኡማውን ቀብር አምላኪና ስሜቱን ተከታይ ማድረግ እንዳለበት ስለሚያውቅ ይህን ወደ መተግበር ገባ ።
    አመራሮቹ የተውሒድ ዳዒ የሚባል ነገር መስማት አንፈልግም አሉ ። መጀመሪያውኑ እንደገለፁት አሕባሽ ፣ ሱፍይ ፣ ኢኽዋንይ የሚል ድምፅ ማጥፋት ዋና ተግባራቸው ሆነ ። የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው በሚል ስሜት ይህን እድል ተጠቅመው የነሲሓ ርዝራዦች ከመጅሊስ ባገኙት የስልጣን ፍርፋሬ ሰለፍዮችን ማፈናቀልና ማባረር ዋነኛው ስራቸው አድርገውታል ።
በአሁኑ ሳአት በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ አካባቢ ፣ በስልጤ ዞን ፣ በኦሮሚያ የተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች ፣ በስብጥር ከላይ እስከታች የተቀመጡ የመጅሊስ አመራሮች በጣም አሳፋሪ በሆነ መልኩ ኢኽዋኖችና ነሲሓዎች ከአሕባሽና ሱፍዮች ጋር በመሆን በተለያየ የመንግስት ተቋማት ላይ ያሉ አመራሮችን መጠቀሚያ በማድረግ የሕብረተሰቡን ህገ መንግስታዊ መብት በመርገጥና በመጣስ በሀይል መስጂዶችን መንጠቅና ኢማሞችንና ኡስታዞችን ማፈናቀልና ማባረር ይህን የሚቋወም ኮሚቴም ሆነ የሕብረተሰብ አካል ካለ ማሰር ግንባር ቀደም ተግባር እንዲሆን አድርገዋል ።
    በተለይ በተጠቀሱት አካባቢ ላይ ያሉ የመንግስት ተቋም አመራሮች የተጣለባቸውን ህገመንግስታዊ አደራ ወደ ጎን በማለት ስልጣንን ለግል ስሜትና አመለካከት ማስፈፀሚያ እያደረጉ ይገኛሉ ። የሚገርመው የዚህ አይነት አፈናና የመብት ጥሰት በብልፅግና ዘመን ላይ መሆኑ ነው ።
    በኢሀዲግ ዘመን የፀደቀው ህገ መንግስት አይደለም የህዝብ የግለሰብም የእምነት ነፃነት ይረጋገጣል የሚል ነው ። እንደሚታወቀው በኢሀዲግ ዘመነ መንግስት በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ የማይፈልገውን አመለካከትና እምነት በመጅሊስ አማካይነት በመጫን ተግባራዊነቱ ትላልቅ የመንግስት ተቋማቶች ያስፈፅሙ ነበር ።
የህገ መንግስቱ የዜጎች መብት የሚያትቱ ህይወት አጥተው ወረቀት ላይ የነበሩ ቃላቶችን እንባ የሚያብስም ሆነ የህዝቡን ጩኸት የሚሰማ አልነበረም ።
     የዶ/ር አብይ የብልፅግና ዘመን ሲቀየር ግን ሁሉም እነዚህ ህይወት አልባ ሆነው ወረቀት ላይ የቀሩ መብቶች ህይወት ዘርተው እውን እንደሚሆኑ ባለ ሙሉ ተስፋ ነበር ። ነገር ግን በየደረጃው ያሉ የኢሀዲግን ጃኬት አውልቀው የብልፅግና ጃኬት ያጠለቁ የህዝብን መብት ማክበር የሚለውን መርሕ ያልተቀበሉ አመራሮች አሁንም ተመሳሳይ ተግባር እየፈፀሙ ይገኛሉ ።
    አብዛኛዎች ከላይ እስከታች በመንግሰት መዋቅር ያሉት አመራሮች ሀገሪቷንና ሕዝቦቿን እያስተዳደሩ ያሉት በህገ መንግስቱ ሳይሆን ከመጅሊስ አመራሮች በሚመጡ መመሪያዎችና ደንቦች ይመስላል ። ‼
    የትኛውም የመንግስት አመራር በየትኛውም ቢሮ ወንበር ላይ ሲቀመጥ የግል እምነቱን አመለካከቱንና ስሜቱን ከቢሮ በራፍ ውጪ አስቀምጦ ሁሉንም ህዝብ ህገ መንግስቱ ባስቀመጠው መመሪያ መሰረት መብቱን እንዲያገኝና ግዴታውን እንዲወጣ በማድረግ ማገልገል ይኖርበት ነበር ። ነገር ግን ይህ የሚታሰብ አይመስልም ። አብዛኛው በሀላፊነት ቦታ የተቀመጡ አመራሮች ማን ይጠይቀኛል የፈለኩትን መስራት መብቴ ነው የሚሉ ይመስላሉ ።
    በተለይ የፀጥታ አካላት ከማንም በላይ የሀገርና ህዝብ አደራ የተሸከሙ ከመሆናቸው አንፃር የሀገርና የህዝብን ሰላም በማስጠበቅ ፍትህን ማስፈን አላማቸው አድርገው ሊንቀሳቀሱ ይገባል ። የሚያሳዝነው ግን በተጠቀሱት አካባቢዮች በሚደርሰው የዜጎች መብት ረገጣ ድራማና ተውኔት ላይ አብዛኛዎች የድራማና ተውኔቱ ገፀ ባህሪ ጥቂቶች ደግሞ የድራማው ደራሲ ሆነው እያየን ነው ።
    በተለያዩ አካባቢዮች እየሆነ ያለው ይህ  ነው ። ሰላማዊ የሆኑ መስጂዶችና ጀማዓዎች ላይ ችግር አለ የሚል ድራማ እየሰሩ ለምን የሚልን ሰብስበው ማሰር ምን ይሉታል ። የህግ አካል ችግር አለ ካለ የመጀመሪያው እርምጃ በሰከነ ሁኔታ ነገሮቹን ማጣራትና መለየት ነበር የሚያስፈልገው ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አጣርተን ነው የምናስረው አስረን አናጣራም ሲሉ ያልተደመመ አልነበረም ። ይህ ማለት እሳቸው በተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች እንዲሁም የሆነ ቀበሌ ላይ ወርደው ይፈፅሙታል ሳይሆን እሳቸው የሚመሩት ፓርቲ መርህ ተብሎ ስለሚታመን ነው ። በመሆኑም በየደረጃው ያሉ የፀጥታ ሀይሎች ይህን መርህ ተከትለው ይሰራሉ የሚል አንድምታ ስለተወሰደ ነው ቃሉን ሁሉም በአግራሞት የተቀበለው ።
    ለመሆኑ የመጅሊስ አመራሮች እንዳሉትም የሀገር መሪዮች ናቸው ወይስ የአንድ የሌሎችን መብት መከልከል የማይችል ተቋም መሪዮች ? የአሁኑ ተግባራቸው ንግግራቸውን እውነት ነው እንዴ እንዲባል የሚያደርግ ነው ። ከክልል ጀምሮ እስከ ፌዴራል ድረስ አንዳንድ ተቋማትን ህገ መንግስቱን በተቃረነ መልኩ በደብዳቤ ሲያዙና ተፈፃሚ እንዲሆን ሲያስደርጉ እየታየ ስለሆነ አንድ ሊባሉ ይገባል ። በልካቸው እንዲቆሙ ካልተደረገ ሀገሪቷን እየመራ ያለውን ፓርቲ ገፅታ የሚያበላሽ ተግባር እየፈፀሙ መቀጠላቸው አይቀርም ።
   ለማንኛውም የሀገራችን ሙስሊሞች ባጠቃላይ ሰለፍዮች በተለይ የመጅሊስ አመራሮች ተውሒድና ሱናን የበላይ ያደርጋሉ ብላችሁ እንዳትጠብቁ ። ይልቁንም ትልቁ ጠላታቸው አድርገው የያዙት የተውሒድ ዳዕዋና የተውሒድ ዱዓቶችን ነው ።

ከተወሰነ ማስተካከያ ጋር በድጋሚ የተለቀቀ ወቅታዊ ማስገንዘቢያ ።

https://t.me/bahruteka


Репост из: Muhammed Mekonn
👌 ሀላፊነታችንም እንወጣ!
     ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯💬

🏝 እንደሚታወቀው የሐቅ ጠላቶች እጅግ በጣም በርካታ ናቸው። እስልምናን ለመዋጋት የሚሰለፈው ቁጥር ስፍር የለውም። በተለይ የጴንጤዎች እና መሰል የአክፍሮች ሀይሎች የሚያደርጉት እንቅስቃሴ በሙስሊሞች ላይ ከባድ አደጋ ነው። በእርግጥ በእስልምና ላይ ምንም ተፅዕኖ የላቸውም በደንብ እየተረዳ የሚሰልመው ብቻ በቂ ነው። ግን በየገጠሩ የሚገኘውን ሚስኪን (ከእውቀትም ከንብረትም ደካማውን) ሙስሊም ማህበረሰብ ወደ ኩፍር በማስገባት የጀሃነም ማገዶ እያደረጉት ነው።

👉 መሆን ያለበት እኛ ከኩፍር ጨለማ ወደ ተውሂድ ብርሃን ጥሪ ማድረግ ነበር። አሁንም በዚሁ አይነት አቋም በርትተን በጎን ደግሞ ጠላቶቻችን መታገል አለብን።

👌 የምንታገላቸው በዕውቀት ነው። ታላቁ መሳሪያችን ትክክለኛ እምነታዊ ግንዛቤ ነው። አዎ ስለ እስልምናችን በዝርዝር ካወቅን ሌላውንም በደንብ እንገነዘባለን። ለዚህ ሁሉም የድርሻውን መወጣት አለበት።

🚥 የነ ሸይኽ ረቢዕ እና የነሸይኽ ሙሐመድ አሊ አደም ተማሪ የሆኑት የሀገራችን ሊቅ ሸይኽ ሁሴን በዚሁ ዙሪያ ኪታብ በመፃፍ ለበርካታ መድረሳዎች ተከፋፍሎ እየተቀራ ይገኛል።

◉ ይህ ኪታብ ለእያንዳንዳችን (ለተማሪ፣ ለደረሳ፣ ለሴቶች...) በተለይ በንፅፅር ዘርፍ እንቅስቃሴ የሚያደርግ ማንኛውም አካል ወይም ለመንቀሳቀስ ያሰበ ሰው ይህንን ኪታብ በደንብ መቅራት ያስፈልጋል። በተለያዩ አካባቢዎች ያላችሁ በወራቤ ዩኒቨርስቲ አንደበተ-ሩቱዕ በሆነው ኡስታዛችን እየተቀራ ያለውን ደርስ ተከታተሉ!

👉 የኪታቡ ስም፦ ➴➴➴
🔍 📚 «تعظيم الإسلام لعيسى عليه السلام وأسباب الارتداد عن دين الإسلام»
🔎 📚 «እስልምና ዒሳን {ዓለይሂ ሰላም} ማላቁ እና ከእስልምና ሀይማኖት የመካድ ምክንያቶች»

📝  አዘጋጅ:- የተከበሩ ሸይኽ ዶ/ር ሑሰይን ቢን ሙሐመድ ቢን አብዲላህ አስ-ስልጢ አላህ ይጠብቃቸው!

💺 የሚያስተምረው
🎙 ኡስታዝ አቡ ሙዓዝ ታጁዲን አብዱረህማን አላህ ይጠብቃቸው! ❴በወሬቤ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ጀመዓ አል-አቅሷ መስጂድ❵

የኪታቡ 𝑷𝑫𝑭 👇👇👇👇
https://t.me/AbuImranAselefy/8893

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 01 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10374

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 02 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10383

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 03 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10390

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 04 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10395

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 05 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10400

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 06 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10410

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 07 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10426

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 08 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10440

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 09 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10442

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 10 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10448

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 11 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10450

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 12 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10458

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 13 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10465

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 14 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10471

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 15 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10473

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 16 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10482

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 17 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10491

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 18 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10495

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 19 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10501

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 20 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10502

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 21 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10506

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 22 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10512

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 23 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10517

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 24 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10525

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 25 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10537

ዒሳ እና ኢስላም ክፍል 26 👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10547
    
        ቀ
           ጥ
                ላ
                  ል


💬 የባጢል ባለቤቶች መሰናክሎችን ሁሉ ተቋቁመው እየለፉ የሐቅ ሰዎች ከተኙ ሐቅ ቢይዙም ይሸነፋሉ። ላለመሸነፍ እንቀሳቀስ። ብዙ ሳንደክም እናተርፋለን።


ጥብቅ ማስጠንቀቂያ!!
በምስሉ በምትመለከቱት መልኩ በቴሌግራም እና ዋትሳፕ የውስጥ መልእክት በምታውቁት ሰው ስም መስለው የሚመጡላችሁን ሊንኮች ከመክፈት ተጠንቀቁ!!
እንደሚታወቀው ሃከሮች በተለያየ ጊዜ ዘዴዎችን ቀያይረው የሰዎችን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስሮችን ይጠልፋሉ፣ አሁን ደግሞ በዚህ መልኩ የአንድን ሰው ከጠለፉ በኋላ የሱን ጓደኞች ደግሞ በተጠለፈው ሰው ስም አድርገው ሊንክ እየላኩ በቀላል መንገድ የብዙዎችን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስሮችን መጥለፍና የፈለጉትን ማድረግ ይችላሉ።
"ሊንኩን ተጭናችሁ ፎቶዋችሁን ተመልከቱ" እያሉም በስልካችሁ የከፈታችሁትን አካውንት ከመጥለፍ ባሻገር የብልግና ምስሎችን እያሰራጩ ይገኛሉ፣ በምንም ተኣምር በዚህ መልኩ በምታውቁት ሰው ስም የተላኩ ምንነታቸው ግልፅ ያልሆኑ ሊንኮችን ከመክፈት ተጠንቀቁ!!
#join ⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa


በቅርብ ቀን ይጠብቁ
ጀማሪዎችና ህፃናት አስተዳደግ ላይ የሚያተኩር
አዲስ ኪታብ

📚 سبيل الرشاد في هدي خير العباد
📒 ሰቢሉ-ረ'ሻድ ፊ`ሃዲ ኸይል’ዒባድ

🏝 رسالة مختصرة في تربية الأبناء والبنات على تعليم التوحيد و السنة، وصفة الصلاة ومحاسن الأخلاق لطلاب التحفيظ والمبتدئين.

✅ ለልጆች፣ ለሂፍዝ እና ጀማሪ ተማሪዎች ተውሂድን፣ ሱናን፣ የሶላት ስርዓትን እና መልካም ስነ-ምግባርን በማስተማር ማሳደግን አስመልክቶ አጠር ያለች ኪታብ

📝 جمع وإعداد: الشيخ الدكتور حسين بن محمد بن عبد الله الإتيوبي السلطي حفظه الله

📝 አዘጋጅ ፦ በሸይኽ ሁሰይን ብን ሙሐመድ ብን አብደላህ አል-ኢትዮጵይ አስልጢ አላህ ይጠብቃቸው
#join ⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://t.me/HussinAssilty
https://t.me/HussinAssilty


🛑 የሀራ ደረሶች ብዛት እንቅልፍ የነሳቸው የሀራ ኢኽዋኖች..!!

ሰለፊዮች እንዲረዱ ያክል ብቻ

➥ እንዲህ ነው ነገሩ የሀራ ሰለፊዮች ለኢኽዋን እጅ ባለመስጠታቸውና ሰላም አስጠባቂና ለሰላም ተዋጊ በመሆናቸው ይታወቀሉ..!! እነዚህ ኢኽዋኖች በተደጋጋሚ የሀራ ሙስሊሞችን አባረው መስጂዱን ለመቆጣጠር ወጣቱን የሱስ ባሪያ አድርገው የነሱ ጭፍን ተከታይ ለማድረግ ያልፈነቀሉት ዲንጋይና ያልሞከሩት ሙከራ የለም.!! ግን አልተሳካላቸውም አይሳካምም ኢንሻአሏህ

በሰሞኑ ወደ ሀራ መድረሳ በየ አቅጣጫው የሚገርፉት የደረሶች ብዛት ደሞ በጣሙን ተለየባቸው አላስቻላቸውም የዞኑ መጅሊስ መሪ ተብዬዎች መጥተው ገበሬውንና አህባሾችን ሰብስበው ኢየደነፉ ዋሉ..!! ሆኖም ይህ ድንፊያ ምንም አይነት ለውጥ አላመጣምና በነሱ ቤት ትልቅና ገዢ የሆነ ነው የሚሉትን ነገር በድንገት ለማካሄድ ሴራቸውን አሲረው በትላንትናው እለተ ሰኞ ማለትም ሚያዝያ ቀን/14/08/2017, እውን ለማድረግ ወሰኑ

ሸይኻችን ደርሳቸውን ኢያሰጡ ኢያቀሩ እኛም መስጂድ ላይ ሁነን ሙጧለዓ ኢያደረግን ኢየተቃራን ባለነበት በድንገት ግቢው በኢኻዋኖችና አስከትለው በመጣቸው ፌደራሎች ግቢው ተጥለቅልቋል የመጅሊሱ መሪ ተብዬዎች ወደ መስጂድ ገብተው ማይኩን ነቅለው በመላኢካ ወታደር ታጅበው የመጡ መስሏቸው ነው መሰለኝ ትንኮሳ ትንኮሳ ብሏቸው ሲቃራ የነበረውን ደረሳ በግልምጫ ተነስ ውጣ ኢያሉ አስደንግጠው አስወጡዋቸው.! ሸይኻችንን ሄደው ደርስ አቋረጧቸው.!

ደረሳዎችን በሙሉ መታወቂያ ካርዳቸውን በመቀበል በሰልፍ ሰበሰቧቸውና ምክኒያቱን ሳይነግሯቸው ልብሳችሁን ሰብስቡ አሏቸው ደረሶችም ሰበሰቡ,
ወደ የሆነ ጥላ ስር ወስደው ሰብስበውን ወታደሮች በግዴታ መድረሳውን ለቀን እንድኖጣ ነገሩን እነሱም ኢኽዋኖች በጠረጠሯቸው መልኩ እንዲሆኑ አምነው ነው መሰለኝ ከዚህ በኋላ ተመልሶ የሚመጣ ካለ ብሎ የግድያ ዛቻውን መዛት ጀመረ.¡¡ ከዛም በመቀጠል ደረሶች በሁለት ሲኖትራክና በሶስት አባዱላ ተጫኑ ሸይኻችንና ከፊል የሀራ ሰለፊያ ወጣቶችንም ጫኗቸውና ሙስሊም ኢያዘነ ካፊር ጉድ ኢያለ ወደ ዞን ጉዞ ተጀመረ የሀራ ሰለፊዮችንና ሸይኻችንን ዞን አሳሰሯቸው እኛን ደሞ በሁለት ቅጥቅጥና በሶስት አባዱላ አስጭነው ወልዲያን አስለቅቀው አስወጡን ከዛም መርሳ ሀይቅ ደሴ ኮምቦልቻ ተከፋፍለን ተቀመጥን...
ይህ ሁላ የኢኽዋኖች ጥረት ለምንድነው..¡?
የነቢያችንን ﷺ መንገድ ከምድረ ገፅ ለማጥፋት ነው አሁንም ልታውቁት የሚገባው ነገር እንኳን ለስልጣንና ለቦርጫችሁ ምትሯሯጡት እናንተ ይቅርና የአለም ሕዝብ ቢነሳ እንኳ አይሞክሩትም የኛም ወኔያችን ይጨምር እንጂ በጭራሽ አይቀንስም ኢንሻአሏህ


📝 ሐፊዱ ሙሐመድ ነኝ

የቴሌግራም ቻናላችንን ጆይን ይበሉ፦
               ◊◊◊◊➖◊◊◊◊
╔══════ ❁❁ ═══════╗
https://t.me/abu_hessan ↩️
╚══════ ❁❁ ═══════╝

Показано 20 последних публикаций.