❗#ከተራ_ምን_ማለት_ነው?❗
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
🔴👉 ከተራ "ከበበ" ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው ውኃ መከተር፣ መገደብ ማለት ነው፡፡
🔵👉 የጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰበ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላል፡፡ የምንጮች ውኃ ደካማ በመሆኑ እንዲጠራቀም ይከተራል ጉድጓድ እየተቆፈረ ውኃው እንዳይሄድ ይገደባል፡፡
🔴👉 በየዓመቱ ጥር 10 ቀን የምእመናኑ አብዛኛው ሥራ ውኃውን መከተርና መገደብ በመሆኑ ዕለቱ ከተራ የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡
🔴👉 ውኃው የሚከተረው በማግሥቱ ጥር 11 ቀን የጥምቀት በዓል ስለሚከበር ለሕዝቡ መጠመቂያ እንዲሆን ነው፡፡ በየሰበካው ቦታ ተለይቶና ተከልሎ ታቦታቱ በዳስ ወይም በድንኳን የሚያድሩበት፣ የተለያዩ የውኃ አካላት ተጠርገው የሚከተሩበት ወይም ሰው ሠራሽ የግድብ ውኃ የሚበጅበት ስፍራ ‹‹ባሕረ ጥምቀት››፣ ‹‹የታቦት ማደርያ›› እየተባለ ይጠራል።
🔵👉 ከዚህም በተጨማሪ በቅዱስ ላልይበላ ዘመነ መንግሥት በኢትዮጵያ ምድር እየተመላለሱ በብሕትውና እና በስብከተ ወንጌል ያገለግሉ የነበሩት ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በአክሱም፣ በመቐለና በመርጡለ ማርያም እየተዘዋወሩ ባሕረ ጥምቀቱን ባርከዋል፡፡
🔵👉 በዐፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት (1260-1275 ዓ.ም) በጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት (1203-1204 ዓ.ም) አሳሳቢነት የተጀመረው ሥርዐተ በዓል ተጠናክሮ እንዲቀጥል በዐዋጅ ትእዛዝ አስተላልፈዋል፡፡
🔴👉 ታቦታቱም በሕዝብ ጥበቃና ክብካቤ ተደርጎላቸው በየጥምቀተ ባሕሩ እንዲያድሩ ወስነዋል፡፡ የበዓሉ አከባበር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋና አድማሱ ብሔራዊነትን እየያዘ መጣ፡፡
🔴👉 ከዐፄ ገብረ መስቀል ጀምሮ የአደባባይ በዓል የሆነው የጥምቀት በዓል በ15ኛው ክ/ዘመን በደገኛው ኢትዮጵያዊው ንጉሠ ነገሥት ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ (1426-1460 ዓ.ም) አማካኝነት ታቦታቱ ወደ ወንዝ ወርደው ዕለቱን እንዳይመለሱ፣ በዚያ ፈንታ በጥምቀት ዋዜማ ጥር 10 ቀን ከሰዓት በኋላ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ ወርደው እንዲያድሩ፣ አገሩን በኪደተ እግር ይባርኩም ዘንድ በሄዱበት መንገድ እንዳይመለሱ በዐዋጅ ወሰኑ፡፡
🔵👉 ይህን ታሪክ በመከተል ዐፄ ናዖድ (1486-1500) ዓ.ም) ማንኛውም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ምእመን ታቦተ ሕጉ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ በሚወርድበት እና ከባሕረ ጥምቀቱ ወደ ቤተ መቅደሱ በሚመለስበት ጊዜ አጅቦ አውርዶ፣ አጅቦ መመለስ እንዳለበት በዐዋጅ አስነግረው ነበር፡፡ ሕዝቡም ታቦታተ ሕጉን በሆታና በእልልታ ከቤተ መቅደስ አጅቦ ከአወጣ በኋላ በባሕረ ጥምቀት ከትሞ ማደር ጀመረ ።
🔵👉 ታቦታተ ሕጉ በወጡበት ቦታ የማይመለሱበት ምክንያት ብዙ ምስጢር አለው፤ ይኸውም ‹‹ወተቀደሰት ምድር በኪደተ እግሩ ምድር በኪደተ እግሩ ተቀደሰች›› እንዳለ ሊቁ ያልተባረከ መሬት እንዲባረክ ነው፤ ዳግመኛም ያላየው እያየ ያልሰማው እየሰማ ሥርዓቱን አይቶ እንዲያምን ሃይማኖት እንዲሰፋ ነው። ነቢያት በመጡበት እንዳይመለሱ ሥርዓት ነበረና የዚያም ምሳሌ ነው፡፡ ሰብአ ሰገል ጌታን ካገኙ በኋላ በመጡበት ቦታ አልተመለሱምና የዚያም ምሳሌ ነው፡፡
🔴👉 የቃል ኪዳኑን ታቦት ይዞ አክብሮ ወደ ወንዝ መውረድ በብሉይ ኪዳን የነበረ ሥርዓት ነው ኢያሱ በሙሴ ተተክቶ ሕዝበ እስራኤልን ሲመራ ታቦቱን አሸክሞ ሲሔድና ከዮርዳስ ወንዝ ሲደርስ ባሕሩ ከኹለት ይከፈልና ወራጁም ይቆም እንደነበረ ቅዱስ መጽሐፍ ይናገራል።
🔷👉 እስራኤል ወደ ምድረ ርስት ሲገቡ ታላቁን የዮርዳኖስ ወንዝ ሲሻገሩ ድንኳን ጥለው የቃል ኪዳን ታቦት ድንኳን ውስጥ አድርገው ሌዋውያኑ ዙሪያውን፣ ካህናቱ በውስጥ ሆነው እግዚአብሔርን እያመሰገኑ እንደተሻገሩ መፅሐፍ ይናገራል ዛሬም እንደ ዮርዳኖስ ከድህነት ወደ ብልጽግና፣ ከደዌ ወደ ጤና፣ ከከህደት ወደ ሃይማኖት ከድንቁርና ወደ ዕውቀት አላሻግር ያለን ባሕረ ኀጢአት በቃል ኪዳኑ አማካኝነት በጥምቀቱ በረከት ያደርቅልናል። ኢያሱ ፩ ፥ ፲፫ ፣ ኢያሱ ፫ ፥ ፰
🔴👉 በዓለ ከተራ የምን ምሳሌ ታቦታቱ ለምን ወደ ጥምቀተ ባሕር ሔደው እዛው ያድራሉ ቢባል :- ሐዋርያው ፊልጶስ ኢትዮጵያዊ ጃንደረባውን ሊያጠምቀው ወደ ጋዛ ወንዝ የመውረዱ ምሳሌ ነው። ሐዋ ሥራ ፰ ፥ ፴፬
🔷👉 ዋናው ምሥጢሩ ግን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዮሐንስን አስከትሎ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ የመሄዱና ለመጠመቅ ተራ ሲጠብቅ እዛው የማደሩ ምሳሌ ነው። ጌታችን ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ የመጣው ጥር 10 አመማቴ ፫ ፥ ፲ በዚህ መሠረት ከጥንት ጀምሮ የቃል ኪዳኑን ታቦት ይዘን ወደ ወንዝ ወርደን በዓለ ጥምቀትን የምናከብረው ከዚህ ታሪክ በመነሣት ነው።
🔴👉 ስለዚህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየዓመቱ ጥር ፲ ቀን ተቀራራቢ የሆኑትን ታቦታትን በየአቅራቢያቸው ወደሚገኘው ወንዝ በአንድነት እያወረደች ከከተራ ዕለት ጀምሮ የጥምቀትን በዓል በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ታከብራለች። ሌሊቱን ከሚያነጋው ሕዝበ ክርስቲያን ጋር በመሆን ያሬዳዊ ማሕሌትና የወንጌል ጉባኤ ተዘርግቶ በመምህራን ወቅታዊ ትምህርት ሲሰጥ ይታደራል ይዋላል።
🔵👉 በበዓለ ጥምቀት ዋዜማ የታቦታቱ ወደ ወንዝ መውረድና የባሕረ ጥምቀት መዘጋጀት የሚከተለው ሃይማኖታዊ ታሪክና ምሳሌ አለው። ታቦቱ የጌታችን፤ ታቦቱን አክብሮ /ይዞ/ የሚሄደው ካህን የቅዱስ ዮሐንስ፣ ባሕረ ጥምቀቱ የዮርዳኖስ ወንዝ፣ ታቦታቱን አጅበው የሚሄዱትና በዓሉን የሚያከብሩት ምእመናን ወደ ቅዱስ ዮሐንስ እየመጡ የንስሐ ጥምቀት ሲጠመቁ የነበሩ ሰዎች ምሳሌዎች ናቸው።
❗እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሠላም አደረሳችሁ❗
🔷👉 መልካም በዓል
#ፎሎው_ማድረግ_እንዳይረሳ
፨፨፨ #ወስብሐት_ለእግዚአብሔር ፨፨፨
።።።።። #ወለወላዲቱ_ድንግል ።።።።።
።።።።። #ወለመስቀሉ_ክቡር ።።።።።
ዲ/ን ዮናስ ዘ ሆለታ ደብረ ኤዶም
ጥር 10 /2017 ዓ.ም
ሆለታ
ፔጁን #Like_Follow_Share በማድረግ ትክክለኛ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት እንዲሁም መረጃ ያግኙ
🔴👉 በቴሌግራም | Telegram
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/joinchat_yonas_holet_debreedom
🔴👉 በዋትስአፕ | whatsapp
👇👇👇👇👇
https://whatsapp.com/channel/0029Va4Ter67T8bV5NlRGJ2w
🔴👉 1ኛ ዩትዩብ | 1st YouTube
👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@yonastube
🔴👉 2ኛ ዩትዩብ | 2nd YouTube
👇👇👇👇👇👇
https://youtube.com/@yonasmedia16
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
🔴👉 ከተራ "ከበበ" ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው ውኃ መከተር፣ መገደብ ማለት ነው፡፡
🔵👉 የጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰበ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላል፡፡ የምንጮች ውኃ ደካማ በመሆኑ እንዲጠራቀም ይከተራል ጉድጓድ እየተቆፈረ ውኃው እንዳይሄድ ይገደባል፡፡
🔴👉 በየዓመቱ ጥር 10 ቀን የምእመናኑ አብዛኛው ሥራ ውኃውን መከተርና መገደብ በመሆኑ ዕለቱ ከተራ የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡
🔴👉 ውኃው የሚከተረው በማግሥቱ ጥር 11 ቀን የጥምቀት በዓል ስለሚከበር ለሕዝቡ መጠመቂያ እንዲሆን ነው፡፡ በየሰበካው ቦታ ተለይቶና ተከልሎ ታቦታቱ በዳስ ወይም በድንኳን የሚያድሩበት፣ የተለያዩ የውኃ አካላት ተጠርገው የሚከተሩበት ወይም ሰው ሠራሽ የግድብ ውኃ የሚበጅበት ስፍራ ‹‹ባሕረ ጥምቀት››፣ ‹‹የታቦት ማደርያ›› እየተባለ ይጠራል።
🔵👉 ከዚህም በተጨማሪ በቅዱስ ላልይበላ ዘመነ መንግሥት በኢትዮጵያ ምድር እየተመላለሱ በብሕትውና እና በስብከተ ወንጌል ያገለግሉ የነበሩት ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በአክሱም፣ በመቐለና በመርጡለ ማርያም እየተዘዋወሩ ባሕረ ጥምቀቱን ባርከዋል፡፡
🔵👉 በዐፄ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት (1260-1275 ዓ.ም) በጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት (1203-1204 ዓ.ም) አሳሳቢነት የተጀመረው ሥርዐተ በዓል ተጠናክሮ እንዲቀጥል በዐዋጅ ትእዛዝ አስተላልፈዋል፡፡
🔴👉 ታቦታቱም በሕዝብ ጥበቃና ክብካቤ ተደርጎላቸው በየጥምቀተ ባሕሩ እንዲያድሩ ወስነዋል፡፡ የበዓሉ አከባበር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋና አድማሱ ብሔራዊነትን እየያዘ መጣ፡፡
🔴👉 ከዐፄ ገብረ መስቀል ጀምሮ የአደባባይ በዓል የሆነው የጥምቀት በዓል በ15ኛው ክ/ዘመን በደገኛው ኢትዮጵያዊው ንጉሠ ነገሥት ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ (1426-1460 ዓ.ም) አማካኝነት ታቦታቱ ወደ ወንዝ ወርደው ዕለቱን እንዳይመለሱ፣ በዚያ ፈንታ በጥምቀት ዋዜማ ጥር 10 ቀን ከሰዓት በኋላ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ ወርደው እንዲያድሩ፣ አገሩን በኪደተ እግር ይባርኩም ዘንድ በሄዱበት መንገድ እንዳይመለሱ በዐዋጅ ወሰኑ፡፡
🔵👉 ይህን ታሪክ በመከተል ዐፄ ናዖድ (1486-1500) ዓ.ም) ማንኛውም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ምእመን ታቦተ ሕጉ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ በሚወርድበት እና ከባሕረ ጥምቀቱ ወደ ቤተ መቅደሱ በሚመለስበት ጊዜ አጅቦ አውርዶ፣ አጅቦ መመለስ እንዳለበት በዐዋጅ አስነግረው ነበር፡፡ ሕዝቡም ታቦታተ ሕጉን በሆታና በእልልታ ከቤተ መቅደስ አጅቦ ከአወጣ በኋላ በባሕረ ጥምቀት ከትሞ ማደር ጀመረ ።
🔵👉 ታቦታተ ሕጉ በወጡበት ቦታ የማይመለሱበት ምክንያት ብዙ ምስጢር አለው፤ ይኸውም ‹‹ወተቀደሰት ምድር በኪደተ እግሩ ምድር በኪደተ እግሩ ተቀደሰች›› እንዳለ ሊቁ ያልተባረከ መሬት እንዲባረክ ነው፤ ዳግመኛም ያላየው እያየ ያልሰማው እየሰማ ሥርዓቱን አይቶ እንዲያምን ሃይማኖት እንዲሰፋ ነው። ነቢያት በመጡበት እንዳይመለሱ ሥርዓት ነበረና የዚያም ምሳሌ ነው፡፡ ሰብአ ሰገል ጌታን ካገኙ በኋላ በመጡበት ቦታ አልተመለሱምና የዚያም ምሳሌ ነው፡፡
🔴👉 የቃል ኪዳኑን ታቦት ይዞ አክብሮ ወደ ወንዝ መውረድ በብሉይ ኪዳን የነበረ ሥርዓት ነው ኢያሱ በሙሴ ተተክቶ ሕዝበ እስራኤልን ሲመራ ታቦቱን አሸክሞ ሲሔድና ከዮርዳስ ወንዝ ሲደርስ ባሕሩ ከኹለት ይከፈልና ወራጁም ይቆም እንደነበረ ቅዱስ መጽሐፍ ይናገራል።
🔷👉 እስራኤል ወደ ምድረ ርስት ሲገቡ ታላቁን የዮርዳኖስ ወንዝ ሲሻገሩ ድንኳን ጥለው የቃል ኪዳን ታቦት ድንኳን ውስጥ አድርገው ሌዋውያኑ ዙሪያውን፣ ካህናቱ በውስጥ ሆነው እግዚአብሔርን እያመሰገኑ እንደተሻገሩ መፅሐፍ ይናገራል ዛሬም እንደ ዮርዳኖስ ከድህነት ወደ ብልጽግና፣ ከደዌ ወደ ጤና፣ ከከህደት ወደ ሃይማኖት ከድንቁርና ወደ ዕውቀት አላሻግር ያለን ባሕረ ኀጢአት በቃል ኪዳኑ አማካኝነት በጥምቀቱ በረከት ያደርቅልናል። ኢያሱ ፩ ፥ ፲፫ ፣ ኢያሱ ፫ ፥ ፰
🔴👉 በዓለ ከተራ የምን ምሳሌ ታቦታቱ ለምን ወደ ጥምቀተ ባሕር ሔደው እዛው ያድራሉ ቢባል :- ሐዋርያው ፊልጶስ ኢትዮጵያዊ ጃንደረባውን ሊያጠምቀው ወደ ጋዛ ወንዝ የመውረዱ ምሳሌ ነው። ሐዋ ሥራ ፰ ፥ ፴፬
🔷👉 ዋናው ምሥጢሩ ግን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዮሐንስን አስከትሎ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ የመሄዱና ለመጠመቅ ተራ ሲጠብቅ እዛው የማደሩ ምሳሌ ነው። ጌታችን ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ የመጣው ጥር 10 አመማቴ ፫ ፥ ፲ በዚህ መሠረት ከጥንት ጀምሮ የቃል ኪዳኑን ታቦት ይዘን ወደ ወንዝ ወርደን በዓለ ጥምቀትን የምናከብረው ከዚህ ታሪክ በመነሣት ነው።
🔴👉 ስለዚህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየዓመቱ ጥር ፲ ቀን ተቀራራቢ የሆኑትን ታቦታትን በየአቅራቢያቸው ወደሚገኘው ወንዝ በአንድነት እያወረደች ከከተራ ዕለት ጀምሮ የጥምቀትን በዓል በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ታከብራለች። ሌሊቱን ከሚያነጋው ሕዝበ ክርስቲያን ጋር በመሆን ያሬዳዊ ማሕሌትና የወንጌል ጉባኤ ተዘርግቶ በመምህራን ወቅታዊ ትምህርት ሲሰጥ ይታደራል ይዋላል።
🔵👉 በበዓለ ጥምቀት ዋዜማ የታቦታቱ ወደ ወንዝ መውረድና የባሕረ ጥምቀት መዘጋጀት የሚከተለው ሃይማኖታዊ ታሪክና ምሳሌ አለው። ታቦቱ የጌታችን፤ ታቦቱን አክብሮ /ይዞ/ የሚሄደው ካህን የቅዱስ ዮሐንስ፣ ባሕረ ጥምቀቱ የዮርዳኖስ ወንዝ፣ ታቦታቱን አጅበው የሚሄዱትና በዓሉን የሚያከብሩት ምእመናን ወደ ቅዱስ ዮሐንስ እየመጡ የንስሐ ጥምቀት ሲጠመቁ የነበሩ ሰዎች ምሳሌዎች ናቸው።
❗እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሠላም አደረሳችሁ❗
🔷👉 መልካም በዓል
#ፎሎው_ማድረግ_እንዳይረሳ
፨፨፨ #ወስብሐት_ለእግዚአብሔር ፨፨፨
።።።።። #ወለወላዲቱ_ድንግል ።።።።።
።።።።። #ወለመስቀሉ_ክቡር ።።።።።
ዲ/ን ዮናስ ዘ ሆለታ ደብረ ኤዶም
ጥር 10 /2017 ዓ.ም
ሆለታ
ፔጁን #Like_Follow_Share በማድረግ ትክክለኛ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት እንዲሁም መረጃ ያግኙ
🔴👉 በቴሌግራም | Telegram
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/joinchat_yonas_holet_debreedom
🔴👉 በዋትስአፕ | whatsapp
👇👇👇👇👇
https://whatsapp.com/channel/0029Va4Ter67T8bV5NlRGJ2w
🔴👉 1ኛ ዩትዩብ | 1st YouTube
👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@yonastube
🔴👉 2ኛ ዩትዩብ | 2nd YouTube
👇👇👇👇👇👇
https://youtube.com/@yonasmedia16