235739 (3).pdf
አከራካሪዉ የገጠር መሬት ይዞታ ተጠሪ እና የአመልካች ልጅ የስር ተከሳሽ ጋብቻቸዉን ሲፈጽሙ አመልካች በጎጆ መዉጫነት በምስክሮች ፊት እንደሰጧቸዉ በሕግ ማስረጃ የመመዘን ሥልጣን የተሰጣቸዉ የወረዳ ፍርድ ቤት እና ጉዳዩን በይግባኝ የተመለከተዉ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያረጋገጡት
ፍሬ ነገር ነዉ፡፡የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት ዉሳኔ የሰጠዉም የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በማስረጃ ያረጋገጠዉን ይህንኑ ፍሬ ነገር መሰረት በማድረግ ነዉ፡፡የስጦታ ዉል በተለይም በልማድ የዳበረዉ
በየአካባቢዉ ማሕብረሰብ ለጎጆ መዉጫነትነት ተብሎ የሚሰጥ የገጠር እርሻ መሬት የተለየ ፎርም እንዲኖረዉ የሚያስገድድ ድንጋጌ በወቅቱ ተግባራዊ ሲሆን በነበረዉ በኦሮሚያ ክልል የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 130/1999 ላይ አልተመለከተም፡፡በዚህ መልኩ በሕጉ ጥብቅ ፎርማሊቲ ያልተደነገገበት ምክንያት ይህ እሴት ያለዉን ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ጠቀሜታ ከግምት በማስገባት ጥብቅ ስርዓት መከተል አስፈላጊ እንዳልሆነ በማሰብ ነዉ፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ለጎጆ መዉጫ ተብሎ የሚደረግ የገጠር መሬት ስጦታ የተለየ የዉል ፎርም እንዲኖረዉ ሕጉ የግድ የሚለዉ አለመሆኑን በሰ/መ/ቁጥር 107840፣ 197998፣206535 እና ሌሎች መሰል መዛግብት ላይ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡ ከዚህም የምንገዘበዉ ከገጠር መሬት
ይዞታ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ በተለይም የባለይዞታዉ ልጅ ወይም ሌላ የባለይዞታዉ የቤተሰብ አባል ትዳር
ሲይዝ ለመተዳደሪያ የሚሆን በተለምዶ ለጎጆ መዉጫ ተብሎ የሚደረግ የመሬት ስጦታ ጥብቅ የሆነ የአጻጻፍ ስርዓት ወይም የስጦታ ዉል ፎርም ባያሟላም በየማህበረሰቡ የዳበረዉን ልማድ እና ጠቃሚ እሴት ከግምት በማስገባት ሕጋዊ ዉጤት እንዲኖረዉ ማድረግ ተገቢነት ያለዉ ስለመሆኑ ነዉ::
ፍሬ ነገር ነዉ፡፡የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት ዉሳኔ የሰጠዉም የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በማስረጃ ያረጋገጠዉን ይህንኑ ፍሬ ነገር መሰረት በማድረግ ነዉ፡፡የስጦታ ዉል በተለይም በልማድ የዳበረዉ
በየአካባቢዉ ማሕብረሰብ ለጎጆ መዉጫነትነት ተብሎ የሚሰጥ የገጠር እርሻ መሬት የተለየ ፎርም እንዲኖረዉ የሚያስገድድ ድንጋጌ በወቅቱ ተግባራዊ ሲሆን በነበረዉ በኦሮሚያ ክልል የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 130/1999 ላይ አልተመለከተም፡፡በዚህ መልኩ በሕጉ ጥብቅ ፎርማሊቲ ያልተደነገገበት ምክንያት ይህ እሴት ያለዉን ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ጠቀሜታ ከግምት በማስገባት ጥብቅ ስርዓት መከተል አስፈላጊ እንዳልሆነ በማሰብ ነዉ፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ለጎጆ መዉጫ ተብሎ የሚደረግ የገጠር መሬት ስጦታ የተለየ የዉል ፎርም እንዲኖረዉ ሕጉ የግድ የሚለዉ አለመሆኑን በሰ/መ/ቁጥር 107840፣ 197998፣206535 እና ሌሎች መሰል መዛግብት ላይ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡ ከዚህም የምንገዘበዉ ከገጠር መሬት
ይዞታ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ በተለይም የባለይዞታዉ ልጅ ወይም ሌላ የባለይዞታዉ የቤተሰብ አባል ትዳር
ሲይዝ ለመተዳደሪያ የሚሆን በተለምዶ ለጎጆ መዉጫ ተብሎ የሚደረግ የመሬት ስጦታ ጥብቅ የሆነ የአጻጻፍ ስርዓት ወይም የስጦታ ዉል ፎርም ባያሟላም በየማህበረሰቡ የዳበረዉን ልማድ እና ጠቃሚ እሴት ከግምት በማስገባት ሕጋዊ ዉጤት እንዲኖረዉ ማድረግ ተገቢነት ያለዉ ስለመሆኑ ነዉ::