🇪🇹ዘወልድ ምክረ-ሕግ🇪🇹‼️


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


ቻናሉ ሕጎችንና የፍ/ቤት ዉሳኔዎችን ያጋራል። አጫጭር የሕግ ማብራሪያዎችንና የምክር አገልግሎቶችን ይሰጣል።

ጠበቃ ካሊድ ከበደ እና ጠበቃ አማረ እሸቱ
በማንኛዉም የፌዴራል እና የክልል ፍ/ቤት ጠባቃና የሕግ አማካሪ
ስልክ- 0935439820
ኢሜይል- khalidbinkebe@gmail.com

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


Репост из: ስለ ህግ
Information !


Репост из: Minda Girma Law Office ምንዳ ግርማ ህግ ቢሮ
243135.pdf
859.1Кб
የሰ/መ/ቁ 243135 (ያልታተመ)

    “በሌላ ወንጀል ተከስሶ በሌላ ማረሚያ ቤት ታስሮ የሚገኝን ተከሳሽ ለመቅረብ ፍቃደኛ አልሆነም ወይም የመከላከል መብቱን በፍቃዱ ትቶታል በሚል ጉዳዩን በሌለበት ተመልክቶ መወሰን የሕገ-መንግስቱን አንቀጽ 20(4)፤ አንቀጽ 9(4) እና 13 እንዲሁም የወ/መ/ሕ/ሥ/ሥ/ቁ 161 እና ተከታዮችን ድንጋጌዎች ያገናዘበ ነዉ ሊባል አይችልም፡፡”




Репост из: Ethiopian all level law student & lawyers group
#ይዞታውን ለጠጠር ማውጫነት ለማዋል ባለይዞታው በአንድ በኩል መንገዱን የሚሰራው ወይም የሚያሰራው የመንግስት አካላት ወይም የግል ድርጅቶች በሌላ በኩል ሆነው የገቡትን ውል መሰረት በማድረግ #በውሉ መሰረት #ካሳ እንዲከፈል የሚቀርብ ክስ ለሕዝብ ጥቅም ሲባል የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበት፣ካሣ የሚከፈልበትና ተነሺዎች መልሰው የሚቋቋሙበትን ሁኔታ ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 1161/2011 አግባብ የሚጠየቅ ካሳ ባለመሆኑ መደበኛ ፍርድ ቤት ጉዳዩን ለመዳኘት ስልጣን አለው፣
ሰ/መ/ቁጥር 218653 ጥቅምት 2ቀን 2015 ዓ/ም


Репост из: Click Ethiopian Laws:- by Mastewal
የገጠር ባዶ መሬት ሽያጭ ዉል ህገ ወጥ ድርጊት በመሆኑ በመርህ ደረጃ ዉሉን ተከትሎ የተሰሩ ስራዎች ምንም አይነት ህጋዊ ውጤት ባይኖራቸውም ነገር ግን መሬቱን የገዛው ሰው በመሬቱ ላይ ያለማቸው አትክልቶች ለሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም የሚሰጡ እንደ ቡና፣ ጫት፣ አቡካዶ፣ ፓፓየ፣ ማንጎ፣ ብርቱካን፣ አፕል፣ ዘይቱና፣ እንሰት፣ ግሽጣና ሙዝ የመሳሰሉ ተክሎች ከሆኑ ተቆርጠውም ጥቅም የማይሰጡ ስለሆኑ በልዩ ሁኔታ ገዢው አትክልቶቹን ለማልማት ያወጣቸውን ልዩ ልዩ ወጪዎቺ ባለመሬቱ እንዲተካ ማድረግ የሚገባ እንጂ ቆርጦ እንዲያነሳ ሊወሰን የማይገባ ስለመሆኑ፣ በመሬቱ ላይ የተሰራው ቤት ከሆነ ግን ገዢ የሰራውን ቤት አፍርሶ መሬቱን ሊያስረክብ የሚገባ ስለመሆኑ የተሰጠ ውሳኔ


Репост из: Dereje Tariku Law Office
220782.pdf
903.7Кб
ተጠሪ #ያለፈቃድ በተውት ጉዳይ በፍትሐ ብሔር ሥነ ሥርዓት ሕጉ ቁጥር 279(1) መሠረት #ሌላ ክስ ማቅረብ አይችሉም

ክስ እንድቋረጥ መፍቀድ ለፍርድ ቤት የተሰጠ #ፍቅድ ሥልጣን (discretion of the court) በመሆኑ ፍርድ ቤት የክስ አቀራረብ ሥርዓት ጉድለት መኖሩን ሲረዳ በራሱ ጊዜ አልያም ከሳሹ ክሱን ሙሉ በሙሉ ወይንም በከፊል ለማቋረጥ የሚያስችል በቂ ምክያት ኖሮት አቤቱታ ለፍርድ ቤት ባቀረበ ጊዜ ፈቃዱ ሊሰጥ ይችላል፡፡ ክስ ለማቋረጥ የሚያስችል ፈቃድ የማግኘት ውጤቱ አስቀድሞ በጉዳዩ ላይ ምንም ክስ እንዳልቀረበ ተወስዶ ለከሳሹ አዲስ ክስ የማቅረብ ነፃነት ስለሚሰጠው ከዚህ አንፃር በተከሳሽ ሊቀርብ የሚችለውን መቃወሚያ ያስቀርለታል፡፡


Репост из: Lawyer_Henok ⚖️Ethio Law🥇ኢትዮ ሕግ
ክርክር ተደርጎ ዉሳኔ ከተሰጠ በኋላ በፍ/ብ/ስ/ስ ህግ ቁጥር 358 መሰረት ያቀረበችዉ መቃወሚያ ክርክር መኖሩን አታዉቅም ነበር ለማለት ጣልቃ ገብታ መከራከር ስትችል ከቅን ልቦና ዉጪ ዉጤቱን ጠብቃ ያቀረበችዉ አቤቱታ ነዉ የሚለዉን ለመወሰን በእርግጥም የመቃወም አመልካች ቀደም ሲል ክርክር ሲደረግ የነበረ መሆኑን ክርክሩም የእሷን መብት የሚመለከት መሆኑን ታዉቅ እንደነበር መረጋገጥ ያለበት ፍሬነገር ጉዳይ ነዉ።
በክርክሩ ተካፋይ ያልሆነ ወገን ባልተሳተፈበት ክርክር ተድርጎ መብቱን የሚነካ ፍርድ መሰጠቱን ባወቀ ጊዜ ፍርዱን በመቃወም መብቱን ማስከበር እንደሚችል በፍ/ብ/ስ/ስ/ህግ 358 ላይ ተደንግጓል፡፡
ይሁንና ይህንን መብት በመጠቀም ረገድ ክርክሩ መኖሩን እያወቀ በቸልተኝነቱ ወይም በእሱ ጉድለት የክርክሩ ተካፋይ ሳይሆን የቀረ ወገን ከቅን ልቦና ዉጪ ጉዳዩን ለማጓተት የሚያቀርበዉ መቃወሚያ ተቀባይነት ሊኖረዉ እንዳማይገባ ሰበር ችሎቱ ገዥ ዉሳኔ የሰጠበት መሆኑ ይታወቃል(ሰበር መ/ቁ/56795፣40229፣93987 እና ሌሎች መሰል መዝገቦችን ይመለከታል)፡፡
ተከሳሽ ባልና ሚስት ሆነዉ አይነጋገሩም ወይም ክርክሩን አያዉቁም ተብሎ አይገመትም የሚል (መነሻ) ያለማስረጃ ሊገመት አይገባም።
👇👇👇👇👇
https://t.me/ethiolawtips


Репост из: ስለ ህግ
መ/ቁጥር 236316
መጋቢት 28 ቀን 2015 ዓ.ም                       
ዳግም ዳኝነት - ይግባኝ ሊቀርብ ስለሚችልበት አግባብ
  ___///____
                                                                                                                                         
ዳግም ዳኝነት ተጠይቆ አቤቱታው የቀረበለት ፍርድ ቤት ወደ ፍሬ ጉዳይ ክርክሩ ከመግባቱ በፊት ዳኝነቱ እንደገና ሊታይ ይገባዋል ወይም አይገባውም በሚለው ነጥብ ላይ አስቀድሞ ውሳኔ መስጠት የሚገባው ስለመሆኑ ከፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 6/4 አነጋገር መገንዘብ ይቻላል፡፡በዚህ መሰረት ዳኝነቱ እንደገና ሊታይ ይገባዋል ወይም አይገባዉም ሲል አዲስ ተገኘ የተባለዉን ማስረጃ ከፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 6(1 እና 2) መመዘኛዎችን የሚያሟላ መሆን አለመሆኑን አስመልክቶ ፍርድ ቤቱ በሚሰጠዉ ዉሳኔ ላይ ይግባኝ ለማቅረብ እንደማይቻል በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 6/4 ስር ተደንግጓል፡፡በዚህ አግባብ የተሰጠ ዉሳኔ ይግባኝ ሊባልበት የማይችል እንደመሆኑ እንደመጨረሻ ዉሳኔ ተቆጥሮ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ከሆነ ለሚመለከተዉ ሰበር ሰሚ ችሎት ቀርቦ ሊታይ የሚችል ነዉ፡፡ 
በሌላ በኩል የቀረበዉን የዳግም ዳኝነት አቤቱታ ከፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 6(1 እና 2) መስፈርቶች አንጻር አይቶ ዳኝነቱ እንደገና ሊታይ ይገባዋል በሚል ፍርድ ቤቱ ዉሳኔ ወይም ትእዛዝ ከሰጠ በኋላ ዋናዉን ጉዳይ በተመለከተ የቀረበ ክርክር አዲስ ተገኘ ከተባለዉ ማስረጃ እና አስቀድሞ የቀረቡትን ማስረጃዎች በመመርመር እና በመመዘን አስቀድሞ የሰጠዉን ዉሳኔ በማሻሻል ወይም በመለወጥ ከተወሰነ የይግባኝ ሰሚዉ ፍርድ ቤት ሥልጣን የሚሆነዉ ዳግም ዳኝነት ጥያቄ ለማቅረብ መሟላት ስላለባቸዉ ቅድመ ሁኔታዎች መመርመር ሳይሆን በዋናዉ ጉዳይ ላይ የተሰጠዉን ዉሳኔ ተገቢነት እና/ወይም ሕጋዊነት መመርመር ላይ የተወሰነ ስለሚሆን ከዚህ አኳያ የተሰጠ ዉሳኔ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 6/4 ስር በተደነገገዉ መሰረት ይግባኝ የማይባልበት ነዉ ሊባል የሚችል አይደለም፡፡ከዚህ ጋር በተያያዘ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ/መ/ቁጥር 42871 ፣75243 እና በሌሎች መዛግብት ላይ አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ተሰጥቷል


Репост из: Lawyer_Henok ⚖️Ethio Law🥇ኢትዮ ሕግ
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎትም በሰ.መ.ቁ 156783 በሰጠው ውሳኔ አስቀድሞ #በውርስ የተገኘ ቤት #ፈርሶ በምትኩ አዲስ የተሰራው ቤት የአንደኛው ወገን የግል ሐብት ነው ሊባል የሚችለው በክልሉ የቤተሰብ ሕግ አዋጅ ቁጥር 69/1995 እና 83/1996 አንቀጽ 74 (2) ስር በተመለከተው መሰረት በምትክ የተሰራው ቤት #የተገለለ ከሆነ ብቻ ነው በሚል በየትኛውም እርከን ላይ ለሚገኙ ፍርድ ቤቶች አስገዳጅ የሆነ የሕግ ትርጉም ሰጥቶበታል፡፡የሰ.መ.ቁ246525 ጥቅምት 08 ቀን 2017 ዓ.ም👇👇
https://t.me/ethiolawtips

Показано 9 последних публикаций.