#የህዝብድምፅ ከህዝብ በጥቆማ መልክ ደርሰውን ትክክኝነታቸው የተረጋገጡ 5 መረጃዎች
1. የሲዳማ ክልል አስተዳደር በያዝነው ሳምንት የአፈር ማዳበሪያ ዋጋ ላይ ከ100 ፐርሰንት በላይ ጭማሪ አድርጓል፣ ይህም አርሶ አደሩን ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ከቷል። ዳፕ ማዳበሪያ ከዚህ በፊት በኩንታል 3,980 ብር ሲሸጥ የነበረ ሲሆን ከነበረበት ባሳለፍነው ማክሰኞ በተወሰነው መሰረት ዋጋው እስ 8,047 ብር እንዲሆን ተደርጓል። "ምንም አይነት ገቢ የሌለው አርሶ አደር ለማዳበሪያ 8,074 ብር ከየት ያመጣል? ቢገዛ እንኳ ከምርቱ ምንን ሊያተርፍ ይችላል? የሚለው በጣም አሳሳቢ ጉዳይ እንደሆነባቸው ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።
2. የኢሚግሬሽን ባህር ዳር ቅርንጫፍ በርካታ ሰዎችን ለአሻራ እየቀጠረ ተስተናጋጆች ሲሄዱ "አዲስ አሰራር ስለመጣ ተቃጥሏል፣ ከእንደገና ለአዲስ 5,000 ብር እና የሚያስቸኩል ጉዳይ ካላችሁ ደግሞ 20,000 ብር ከፍላችሁ መመዝገብ ትችላላችሁ" እየተባሉ መሆኑን ለሚድያችን ጠቁመዋል። የከፈሉት ገንዘብ እና ያቃጠሉት ግዜን በተመለከተ ሲጠይቁም ምላሽ እንዳላገኙ ተናግረዋል።
3. በኦሮሚያ ክልል "ሚዛን ጀምረናል" በሚል ምክንያት ከ12 ሜትር ኪዩብ በላይ የሆኑ እንደ ሲኖ ያሉ መኪናዎች መንቀሳቀስ እንዳልቻሉ ታውቋል፣ ይህም የኮንስትራክሽን ግብዐት የሆኑት እንደ ጠጠር እና አሸዋ ዋጋቸው በእጅጉ እንደጨመረ መሠረት ሚድያ ሰምቷል። ይህ የሰሞኑ "ሚዛን" የተባለ አሰራር የተወሰኑ የአሸዋ እና ጠጠር አምራቾችን ለመጥቀም እንደሆነ የተናገሩት ምንጮች ከዚህም በተጨማሪ በየቦታው የኬላ ክፍያ እንዳሰለቻቸው ጠቁመዋል።
4. በሀዋሳ ከተማ የሚስተዋለው የቤንዚን እጥረት ተባብሶ መቀጠሉ ታውቋል። ማደያዎች አሁንም ቤንዚን መሸጥ ያቆሙ ቢሆንም አሽከርካሪዎች እስከ 300 ብር ከጥቁር ገበያ ከመግዛት እየተገደዱ መሆኑን ያስረዳሉ። "ብዙ ማደያ አለ፣ ነገር ግን ቤንዝን የለም። የሆነ ቀን አንዱጋ አለ ከተባለ አዳር ተሠልፈን ሳናገኝ እንበተናለን። በየመንገዱ ከየት እንደሚያመጡ የማይታወቁ አንድ ሊትር 300 ብር እየሸጡልን ነው" ብለው ነዋሪዎች ጠቁመዋል።
5. በመጨረሻም፣ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ለበዓል የወጡ በርካታ ወጣቶች የፋኖን ስም ጠርታችሁ ጨፍራችኋል ተብለው እየታደኑ በመታሰር ላይ እንደሚገኙ ታውቋል። ወጣቶቹ አሁን ላይ የታሰሩበት ቦታ እንደማይታወቅ የጠቆሙት ምንጮቻችን ቁጥራቸው በርካታ በመሆኑ ፖሊስ ጣብያ ስለማይችለው ምናልባት ወደ ወታደራዊ ካምፕ ተወስደው ሊሆን እንደሚችል ጠቁመዋል። "ሚካኤል ታቦቱ ወደ ማደሪያ ሲመለስ ጨፍራችሀል የተባሉት ወጣቶች እስከዛሬ ቀን ድረስ ታፍሰው የት እንደታሰሩም አይታወቅም፣ በየፖሊስ ጣቢያውም የሉም፣ በቁጥር በጣም ብዙ ናቸው" ያሉን በስፍራው ያሉ ምንጮቻችን ናቸው።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
1. የሲዳማ ክልል አስተዳደር በያዝነው ሳምንት የአፈር ማዳበሪያ ዋጋ ላይ ከ100 ፐርሰንት በላይ ጭማሪ አድርጓል፣ ይህም አርሶ አደሩን ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ከቷል። ዳፕ ማዳበሪያ ከዚህ በፊት በኩንታል 3,980 ብር ሲሸጥ የነበረ ሲሆን ከነበረበት ባሳለፍነው ማክሰኞ በተወሰነው መሰረት ዋጋው እስ 8,047 ብር እንዲሆን ተደርጓል። "ምንም አይነት ገቢ የሌለው አርሶ አደር ለማዳበሪያ 8,074 ብር ከየት ያመጣል? ቢገዛ እንኳ ከምርቱ ምንን ሊያተርፍ ይችላል? የሚለው በጣም አሳሳቢ ጉዳይ እንደሆነባቸው ለመሠረት ሚድያ ተናግረዋል።
2. የኢሚግሬሽን ባህር ዳር ቅርንጫፍ በርካታ ሰዎችን ለአሻራ እየቀጠረ ተስተናጋጆች ሲሄዱ "አዲስ አሰራር ስለመጣ ተቃጥሏል፣ ከእንደገና ለአዲስ 5,000 ብር እና የሚያስቸኩል ጉዳይ ካላችሁ ደግሞ 20,000 ብር ከፍላችሁ መመዝገብ ትችላላችሁ" እየተባሉ መሆኑን ለሚድያችን ጠቁመዋል። የከፈሉት ገንዘብ እና ያቃጠሉት ግዜን በተመለከተ ሲጠይቁም ምላሽ እንዳላገኙ ተናግረዋል።
3. በኦሮሚያ ክልል "ሚዛን ጀምረናል" በሚል ምክንያት ከ12 ሜትር ኪዩብ በላይ የሆኑ እንደ ሲኖ ያሉ መኪናዎች መንቀሳቀስ እንዳልቻሉ ታውቋል፣ ይህም የኮንስትራክሽን ግብዐት የሆኑት እንደ ጠጠር እና አሸዋ ዋጋቸው በእጅጉ እንደጨመረ መሠረት ሚድያ ሰምቷል። ይህ የሰሞኑ "ሚዛን" የተባለ አሰራር የተወሰኑ የአሸዋ እና ጠጠር አምራቾችን ለመጥቀም እንደሆነ የተናገሩት ምንጮች ከዚህም በተጨማሪ በየቦታው የኬላ ክፍያ እንዳሰለቻቸው ጠቁመዋል።
4. በሀዋሳ ከተማ የሚስተዋለው የቤንዚን እጥረት ተባብሶ መቀጠሉ ታውቋል። ማደያዎች አሁንም ቤንዚን መሸጥ ያቆሙ ቢሆንም አሽከርካሪዎች እስከ 300 ብር ከጥቁር ገበያ ከመግዛት እየተገደዱ መሆኑን ያስረዳሉ። "ብዙ ማደያ አለ፣ ነገር ግን ቤንዝን የለም። የሆነ ቀን አንዱጋ አለ ከተባለ አዳር ተሠልፈን ሳናገኝ እንበተናለን። በየመንገዱ ከየት እንደሚያመጡ የማይታወቁ አንድ ሊትር 300 ብር እየሸጡልን ነው" ብለው ነዋሪዎች ጠቁመዋል።
5. በመጨረሻም፣ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ለበዓል የወጡ በርካታ ወጣቶች የፋኖን ስም ጠርታችሁ ጨፍራችኋል ተብለው እየታደኑ በመታሰር ላይ እንደሚገኙ ታውቋል። ወጣቶቹ አሁን ላይ የታሰሩበት ቦታ እንደማይታወቅ የጠቆሙት ምንጮቻችን ቁጥራቸው በርካታ በመሆኑ ፖሊስ ጣብያ ስለማይችለው ምናልባት ወደ ወታደራዊ ካምፕ ተወስደው ሊሆን እንደሚችል ጠቁመዋል። "ሚካኤል ታቦቱ ወደ ማደሪያ ሲመለስ ጨፍራችሀል የተባሉት ወጣቶች እስከዛሬ ቀን ድረስ ታፍሰው የት እንደታሰሩም አይታወቅም፣ በየፖሊስ ጣቢያውም የሉም፣ በቁጥር በጣም ብዙ ናቸው" ያሉን በስፍራው ያሉ ምንጮቻችን ናቸው።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia