የእሷ ጥንካሬ ለሌሎችም የሚጋባ ዓይነት ነው፤ ጽናቷ ሌሎችን የሚያበረታ ነው። ለመንፈሳዊ ጉዳዮች ትኩረት ስለምትሰጥም ትምህርቷም ሌሎችን ወደ ከፍታው የሚያሻግር፤ ምክሯ ከስህተታቸው የሚመልስ ነው። ደጋግሞ በመሞከር የምታምን ትዕግሥትን የተላበሰች፣ ባልተሳካው ጉዳይ ፀፀትና ቁጭት የምታዘወትር በመሆኗም በማኅበራዊ ሕይወቷም ሆነ በሌሎች ተግባራቶቿ ብዙዎችን ታስቀናለች። በዙሪያዋ ያሉ ሁሉ ለማደግ እንዲንጠራሩ ታደርጋለች።
ሰዎች ማንነታቸውን ከተቀበሉ ድከመታቸውን ማረም እንደሚችሉ፤ ጥንካሬያቸውን ለሰው ሁሉ እንደሚያሳዩ፤ ለሌሎች ሰዎች መብራት እንደሚሆኑና ራሳቸውን ከጨለማው ወደ ብርሃኑ ማውጣት እንደማይሳናቸው ታስባለች። በዚህ ውስጥ ደግሞ እርሷ ለሌሎች የነገ መውጫቸው መሰላል እንደሆነችም ትገነዘባለች።
ያብስራ ትናንትን በብዙ እያማረረች ብትቆይም ዛሬ ላይ ግን ማንንም ሳትወቅስ ወደፊት ትራመዳለች። እንደውም አሁን ላይ ቆም ብላ ስታስበው ‹‹በእኔ እንዲህ መሆን ማንም ተወቃሽ የለም›› ትላለች። ‹‹ፈጣሪ በዚህ ደረጃ የፈጠረኝ መጥፎ ስለሆነ ወይም ቤተሰቦቼ ኃጢአት ስለሠሩ አይደለም። እኔን ስለሚወደኝና ቤተሰቦቼም የበለጠ ጠንካራ እንደሆኑ ስላሰበ ነው። ሌሎች በእኔ ውስጥ ተምረው ደስተኛ ኑሮን እንዲኖሩ ስለፈለገ ነው። እኔም ደስታዬ በሌሎች ለውጥ ውስጥ እንዲሆን ስለፈለገኝ ነው እንጂ ፈጣሪ በፍጥረቱ የሚሳሳት ሆኖ አይደለም።» በማለትም በእርሷ አካል ጉዳተኝነት ዙሪያ ተወቃሽ የሚባል ነገር እንደሌለ ትናገራለች።
ፈጣሪ ለእርሷ የሰጣት ልዩ ጸጋ እንዳለ የምታምነው ያብስራ፤ በዛሬዋ ውስጥ ማንም ሰው እርሷን ካገኘ የተፈጠረበትን ዓላማ እንዲረዳ የማድረግ አቅም እንዳላት አውቃለች። በዚህ ደግሞ ፈጣሪዋን ታመሰግናለች፤ ለዚህ ያበቋትን ቤተሰቦቿንና ጓደኞቿን አመስግና አትጠግብም።
ምሳሌ ፋውንዴሽን
ያብስራ ማንም ሰው በሕይወቱ ስኬታማ ለመሆን ስንፍናንና አልችልም ባይነትን ማስወገድ ነው የሚል አቋም አላት። በተለይም ራስን ማሸነፍና ራስን መቀበል ከምንም በላይ ለሕይወት ጉዞ አስፈላጊ እንደሆነም ታምናለች። በዚህ አቋሟም ላይ ሆና በመንቀሳቀሷ ከፍታዋን እንደገነባች ታስባለች። ምክንያቱም ዛሬ ላይ ያብስራ የተለዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ ትገኛለች። አንዱ ከራሷ አልፋ በጎ አድራጎት ድርጅት ከፍታ ለሌሎች መድረስ ችላለች።
ድርጅቱ ምሳሌ ፋውንዴሽን ይባላል። ዋና ተግባሩ በየዓመቱ በበዓላት እና በትምህርት ማስጀመሪያ ወቅት በኢኮኖሚያቸው ዝቅ ያሉ የማኅበረሰብ ክፍሎችን ማገዝና የማዕድ ማጋራት ሥራ ማከናወን ነው።
ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁሶችን ማቅረብ፤ አቅመ ደካማን ከእነ ቤተሰባቸው በዓልን በደስታ እንዲያሳልፉ ማገዝ ሲሆን፤ ትኩረት የሚሰጣቸው የማኅበረሰብ ክፍሎቹም የአዕምሮ እድገት ውስንነት፤ ሴተኛ አዳሪዎች፤ ጎዳና ላይ ኑሯቸውን ያደረጉ ሰዎችና ጧሪና ቀባሪ ያጡ አዛውንቶች ናቸው። እናም በሁለቱ ወቅት ቢያንስ 700 ቢበዛ ደግሞ 1000 ሰዎችን እንዲታገዙ ለማድረግ በሀዋሳ ከተማ አካባቢ ያሉ አጋሮቿ ጋር በመተባበር ተግባሩን ትከውናለች።
ያብስራ በድርጅቷ በኩል ብቻ አይደለም ሰዎችን የምታግዘው። ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተከታይ ቲክቶከር በመሆኗ የራሷን ገቢ ለማሳደግ የተለያዩ ማስታወቂያቸውን ከመሥራት ጎን ለጎን ወጣቶችን በተለያየ አግባብ ታስተምራለች። በርካቶችን ታነቃቃለች፤ ለተሻለ ሥራም እንዲነሱ ታበረታታለች። ከዚያ ወጣ በማለትም በግሏም ሆነ በቡድን ለወጣቶች ማይንድ ሴትአፕ ላይ የተለያዩ ሥልጠናዎችን ትሰጣለች። ተቀጥራ በምትሠራበት መሥሪያ ቤት በኩልም አርሶ አደሩ የበለጠ ተጠቃሚ እንዲሆንም ትተጋለች።
መልዕክት ያብሰራ
የሰዎች ታላቅነት የሚመዘነው ባላቸው አቅምና እድል ተጠቅመው ለሌሎች መትረፍ ሲችሉ እንደሆነ የምታምነው ያብስራ፤ አካል ጉዳተኞችን መደገፍ የአንድ አካል ብቻ እንዳልሆነ አበክራ ትናገራለች። ቤተሰብ ግዴታው ቢሆንም ማኅበረሰቡ ካልደገፈው ውጤታማ መሆን አይችልም ባይ ነች። ደከመኝ ሳይሉ፤ ለነገ የሚሆናቸውን ነገር ሳይሰስቱ ሊሰጧቸው እንደሚገባ ታነሳለች።
አካል ጉዳት ተፈልጎ የሚመጣ ባለመሆኑ በሁሉም በኩል ትኩረት ሊሰጠው ይገባል። ከመንግሥት እስከ ቤተሰብ ድረስ ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እንክብካቤ ሊያደርግላቸው ያስፈልጋል። በሁኔታዎች ሁሉ ያልተገደበ ድጋፉን ማድረግ ይገባል። ማኅበረሰቡም ቢሆን ከማሸማቀቅ ይልቅ ብርታት ሊሆነው ያስፈልጋል ትላለች።
ማንነትን አለመቀበል ለነገሮች ውስብስብነት ያጋልጣል፤ ወቃሽነትን ያመጣል፤ ተስፋ መቁረጥንና አለመሥራትን ከፍ ያደርጋል። ይህ ደግሞ በሰው ጫንቃ ላይ እንድናርፍ ያስገድደናል። ሕይወትንም ጨለማ ያደርጋል። ስለሆነም አካል ጉዳተኞች ጉዳታቸውን ተቀብለው መጓዝና ለጥያቄዎቻቸው በራሳቸው መፍትሔ ማምጣት ነው በማለት ትመክራለች።
ራሳችንን ለመለወጥ የምንሠራው ሥራ፤ ስለራሳችን ጠንካራ ግምት የምንሰጥ ከሆነና ከውስጣችን የምናወጣቸው ቃላቶች ሳይቀሩ ይገነቡናል። እናም ለዓላማ የተፈጠርን እንደሆንን ለማወቅ ለራሳችን የምንነግረውን ነገር እንምረጥ ትላለች። እስትንፋስ ያላቸው ሁሉ ምንም ዓይነት አፈጣጠር ይኑራቸው ለዓላማ ተፈጥረዋልና አደርገዋለሁ ብለው ከተነሱ ተአምር መሥራት ይችላሉ። ለዚህ ደግሞ እድልም፤ ተስፋም አላቸው ባይ ነች።
የያብስራ የመጨረሻ መልዕክት ራሳችን ላይ እንሥራ የሚል ነው። ራሳችን ላይ ስንሰራ አሸናፊ እንሆናለን፤ የምንፈልገው ላይ እንደርሳለን፤ ጠንካራ ነሽ የሚሉ ሰዎችን እናበረክታለን። በአካል ጉዳታችን የሚያሸማቅቀንም ሆነ አትችሉም የሚለንን እንቀንሳለን ትላለች።
ጽጌረዳ ጫንያለው
አዲስ ዘመን መጋቢት 30 ቀን 2017
ሰዎች ማንነታቸውን ከተቀበሉ ድከመታቸውን ማረም እንደሚችሉ፤ ጥንካሬያቸውን ለሰው ሁሉ እንደሚያሳዩ፤ ለሌሎች ሰዎች መብራት እንደሚሆኑና ራሳቸውን ከጨለማው ወደ ብርሃኑ ማውጣት እንደማይሳናቸው ታስባለች። በዚህ ውስጥ ደግሞ እርሷ ለሌሎች የነገ መውጫቸው መሰላል እንደሆነችም ትገነዘባለች።
ያብስራ ትናንትን በብዙ እያማረረች ብትቆይም ዛሬ ላይ ግን ማንንም ሳትወቅስ ወደፊት ትራመዳለች። እንደውም አሁን ላይ ቆም ብላ ስታስበው ‹‹በእኔ እንዲህ መሆን ማንም ተወቃሽ የለም›› ትላለች። ‹‹ፈጣሪ በዚህ ደረጃ የፈጠረኝ መጥፎ ስለሆነ ወይም ቤተሰቦቼ ኃጢአት ስለሠሩ አይደለም። እኔን ስለሚወደኝና ቤተሰቦቼም የበለጠ ጠንካራ እንደሆኑ ስላሰበ ነው። ሌሎች በእኔ ውስጥ ተምረው ደስተኛ ኑሮን እንዲኖሩ ስለፈለገ ነው። እኔም ደስታዬ በሌሎች ለውጥ ውስጥ እንዲሆን ስለፈለገኝ ነው እንጂ ፈጣሪ በፍጥረቱ የሚሳሳት ሆኖ አይደለም።» በማለትም በእርሷ አካል ጉዳተኝነት ዙሪያ ተወቃሽ የሚባል ነገር እንደሌለ ትናገራለች።
ፈጣሪ ለእርሷ የሰጣት ልዩ ጸጋ እንዳለ የምታምነው ያብስራ፤ በዛሬዋ ውስጥ ማንም ሰው እርሷን ካገኘ የተፈጠረበትን ዓላማ እንዲረዳ የማድረግ አቅም እንዳላት አውቃለች። በዚህ ደግሞ ፈጣሪዋን ታመሰግናለች፤ ለዚህ ያበቋትን ቤተሰቦቿንና ጓደኞቿን አመስግና አትጠግብም።
ምሳሌ ፋውንዴሽን
ያብስራ ማንም ሰው በሕይወቱ ስኬታማ ለመሆን ስንፍናንና አልችልም ባይነትን ማስወገድ ነው የሚል አቋም አላት። በተለይም ራስን ማሸነፍና ራስን መቀበል ከምንም በላይ ለሕይወት ጉዞ አስፈላጊ እንደሆነም ታምናለች። በዚህ አቋሟም ላይ ሆና በመንቀሳቀሷ ከፍታዋን እንደገነባች ታስባለች። ምክንያቱም ዛሬ ላይ ያብስራ የተለዩ ተግባራትን በማከናወን ላይ ትገኛለች። አንዱ ከራሷ አልፋ በጎ አድራጎት ድርጅት ከፍታ ለሌሎች መድረስ ችላለች።
ድርጅቱ ምሳሌ ፋውንዴሽን ይባላል። ዋና ተግባሩ በየዓመቱ በበዓላት እና በትምህርት ማስጀመሪያ ወቅት በኢኮኖሚያቸው ዝቅ ያሉ የማኅበረሰብ ክፍሎችን ማገዝና የማዕድ ማጋራት ሥራ ማከናወን ነው።
ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁሶችን ማቅረብ፤ አቅመ ደካማን ከእነ ቤተሰባቸው በዓልን በደስታ እንዲያሳልፉ ማገዝ ሲሆን፤ ትኩረት የሚሰጣቸው የማኅበረሰብ ክፍሎቹም የአዕምሮ እድገት ውስንነት፤ ሴተኛ አዳሪዎች፤ ጎዳና ላይ ኑሯቸውን ያደረጉ ሰዎችና ጧሪና ቀባሪ ያጡ አዛውንቶች ናቸው። እናም በሁለቱ ወቅት ቢያንስ 700 ቢበዛ ደግሞ 1000 ሰዎችን እንዲታገዙ ለማድረግ በሀዋሳ ከተማ አካባቢ ያሉ አጋሮቿ ጋር በመተባበር ተግባሩን ትከውናለች።
ያብስራ በድርጅቷ በኩል ብቻ አይደለም ሰዎችን የምታግዘው። ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተከታይ ቲክቶከር በመሆኗ የራሷን ገቢ ለማሳደግ የተለያዩ ማስታወቂያቸውን ከመሥራት ጎን ለጎን ወጣቶችን በተለያየ አግባብ ታስተምራለች። በርካቶችን ታነቃቃለች፤ ለተሻለ ሥራም እንዲነሱ ታበረታታለች። ከዚያ ወጣ በማለትም በግሏም ሆነ በቡድን ለወጣቶች ማይንድ ሴትአፕ ላይ የተለያዩ ሥልጠናዎችን ትሰጣለች። ተቀጥራ በምትሠራበት መሥሪያ ቤት በኩልም አርሶ አደሩ የበለጠ ተጠቃሚ እንዲሆንም ትተጋለች።
መልዕክት ያብሰራ
የሰዎች ታላቅነት የሚመዘነው ባላቸው አቅምና እድል ተጠቅመው ለሌሎች መትረፍ ሲችሉ እንደሆነ የምታምነው ያብስራ፤ አካል ጉዳተኞችን መደገፍ የአንድ አካል ብቻ እንዳልሆነ አበክራ ትናገራለች። ቤተሰብ ግዴታው ቢሆንም ማኅበረሰቡ ካልደገፈው ውጤታማ መሆን አይችልም ባይ ነች። ደከመኝ ሳይሉ፤ ለነገ የሚሆናቸውን ነገር ሳይሰስቱ ሊሰጧቸው እንደሚገባ ታነሳለች።
አካል ጉዳት ተፈልጎ የሚመጣ ባለመሆኑ በሁሉም በኩል ትኩረት ሊሰጠው ይገባል። ከመንግሥት እስከ ቤተሰብ ድረስ ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እንክብካቤ ሊያደርግላቸው ያስፈልጋል። በሁኔታዎች ሁሉ ያልተገደበ ድጋፉን ማድረግ ይገባል። ማኅበረሰቡም ቢሆን ከማሸማቀቅ ይልቅ ብርታት ሊሆነው ያስፈልጋል ትላለች።
ማንነትን አለመቀበል ለነገሮች ውስብስብነት ያጋልጣል፤ ወቃሽነትን ያመጣል፤ ተስፋ መቁረጥንና አለመሥራትን ከፍ ያደርጋል። ይህ ደግሞ በሰው ጫንቃ ላይ እንድናርፍ ያስገድደናል። ሕይወትንም ጨለማ ያደርጋል። ስለሆነም አካል ጉዳተኞች ጉዳታቸውን ተቀብለው መጓዝና ለጥያቄዎቻቸው በራሳቸው መፍትሔ ማምጣት ነው በማለት ትመክራለች።
ራሳችንን ለመለወጥ የምንሠራው ሥራ፤ ስለራሳችን ጠንካራ ግምት የምንሰጥ ከሆነና ከውስጣችን የምናወጣቸው ቃላቶች ሳይቀሩ ይገነቡናል። እናም ለዓላማ የተፈጠርን እንደሆንን ለማወቅ ለራሳችን የምንነግረውን ነገር እንምረጥ ትላለች። እስትንፋስ ያላቸው ሁሉ ምንም ዓይነት አፈጣጠር ይኑራቸው ለዓላማ ተፈጥረዋልና አደርገዋለሁ ብለው ከተነሱ ተአምር መሥራት ይችላሉ። ለዚህ ደግሞ እድልም፤ ተስፋም አላቸው ባይ ነች።
የያብስራ የመጨረሻ መልዕክት ራሳችን ላይ እንሥራ የሚል ነው። ራሳችን ላይ ስንሰራ አሸናፊ እንሆናለን፤ የምንፈልገው ላይ እንደርሳለን፤ ጠንካራ ነሽ የሚሉ ሰዎችን እናበረክታለን። በአካል ጉዳታችን የሚያሸማቅቀንም ሆነ አትችሉም የሚለንን እንቀንሳለን ትላለች።
ጽጌረዳ ጫንያለው
አዲስ ዘመን መጋቢት 30 ቀን 2017