ምን አይነት ፍቅር ነው 🙆
መግደላዊት ማርያም ትባላለች ኢየሱስን በጣም ከመውደዷ የተነሳ " በቃ ጌታሽ እኮ ሞቷል " ተብላ እንኳን ሽቶ ልቀባው ነው በሚል ሰበብ የሞተ ስጋውን ለማየት ለሊቱ እስኪነጋላት አጠብቅም ፤ ባይገርማቹ ሌሎቹ ደቀ መዛሙርቶች ኢየሱስ በህይወት እያለ
" አንተ ጌታችን ነህ " ብለውት ነበር ነገር ግን ኃላ ላይ እንደ ሰው ሲሞት ሀሳብ ቀይረው ሁሉም ወደ ኋላ ተመለሱ
ይቺ ድንቅ ሴት ግን በህይወት እያለ በራሷ ላይ ብቸኛ ጌታ ያረገችውን ኢየሱስን ሞቶም እንኳን ልትቀይረው አልፈለገችም፤ ምን አይነት ፍቅር ነው 😭 ምን አይነት
መረዳት ቢኖራት ነው ኢየሱስ ሞቶም እንኳን ለእርሱ ያላት ፍቅር አልቀዘቅዝ ያለው እናንተዬ ለካስ ኢየሱስ እንዲም ይወደዳል....ትዝ ካላቹ ኢየሱስ ከሞት ከተነሳ በኋላም ለመጀመሪያ ጊዜ ራሱን የገለጠው ለዚች ድንቅ ሴት ነበር 🔥
የተወደዳቹ ትናንት ላይ ይቺን ሴት የነካት ይሄ ታላቅ ፍቅር ዛሬ ላይ ሁላችንንም እንዲነካን ፀሎቴ ነው 🔥🔥
@thedayofpentecost
@thedayofpentecost