መሰማት ይፈልጋል
ብዙ ጊዜ በጌታ ፊት ተንበርክከን ስንፀልይ አንደ ልጅ ጌታን ብዙ ነገሮችን እንጠይቀዋለን፤ አባ ይሄን ነገር አድርግልኝ ፣ ካንተ ይሄን እጠብቃለው እንለዋለን፤ ነገር ግን ብዙዎቻችን እኛ ጌታን እንደ አባት የሚያስፈልገንን እንደምንጠይቀው ሁሉ የሚሰማንም አባት እኛ ልጆቹ እንድንኖርለት የሚፈልገው ህይወት እንዳለ አናስተውልም፤ አይታቹ ከሆነ የዛ የጠፋው ልጅ ትልቁ ጥፋት ንብረት መካፈሉ ላይ ሳይሆን ንብረት ከተካፈለ በኋላ አባቱን ምን አይነት ህይወት መኖር እንዳለበት አለመጠየቁ ላይ ነው፤ የተወደዳቹ የአባቴ ልጆች ፀሎታቹ የእናንተ ሀሳብ ብቻ የሚፀባረቅበት ስፍራ መሆን የለበትም፤ እኛ በፀሎት ስፍራችን ላይ ተንበርክከን አባታችን እንዲሰማን እንደምንፈልገው ሁሉ ጌታም በግሉ በልጆቹ መሰማትን ይፈልጋል፤ ይሄ አባት ምን አይነት ህይወት ልኑርልህ... እንደ ልጅ ከኔ የምትፈልገው ምንድነው እንድትሉት ይፈልጋል፤ ከጌታ ጋር የሚኖራቹ ህብረትም ፍሬያማ የሚሆነው በእናንተ ፍላጎቶችና ጥያቄዎች ላይ ብቻ ሳይሆን በእርሱም የልብ ፍቃድ ላይ የሚመሰረት ከሆነ ነው።
@thedayofpentecost
@thedayofpentecost
ብዙ ጊዜ በጌታ ፊት ተንበርክከን ስንፀልይ አንደ ልጅ ጌታን ብዙ ነገሮችን እንጠይቀዋለን፤ አባ ይሄን ነገር አድርግልኝ ፣ ካንተ ይሄን እጠብቃለው እንለዋለን፤ ነገር ግን ብዙዎቻችን እኛ ጌታን እንደ አባት የሚያስፈልገንን እንደምንጠይቀው ሁሉ የሚሰማንም አባት እኛ ልጆቹ እንድንኖርለት የሚፈልገው ህይወት እንዳለ አናስተውልም፤ አይታቹ ከሆነ የዛ የጠፋው ልጅ ትልቁ ጥፋት ንብረት መካፈሉ ላይ ሳይሆን ንብረት ከተካፈለ በኋላ አባቱን ምን አይነት ህይወት መኖር እንዳለበት አለመጠየቁ ላይ ነው፤ የተወደዳቹ የአባቴ ልጆች ፀሎታቹ የእናንተ ሀሳብ ብቻ የሚፀባረቅበት ስፍራ መሆን የለበትም፤ እኛ በፀሎት ስፍራችን ላይ ተንበርክከን አባታችን እንዲሰማን እንደምንፈልገው ሁሉ ጌታም በግሉ በልጆቹ መሰማትን ይፈልጋል፤ ይሄ አባት ምን አይነት ህይወት ልኑርልህ... እንደ ልጅ ከኔ የምትፈልገው ምንድነው እንድትሉት ይፈልጋል፤ ከጌታ ጋር የሚኖራቹ ህብረትም ፍሬያማ የሚሆነው በእናንተ ፍላጎቶችና ጥያቄዎች ላይ ብቻ ሳይሆን በእርሱም የልብ ፍቃድ ላይ የሚመሰረት ከሆነ ነው።
@thedayofpentecost
@thedayofpentecost