" ዜለንስኪ ጥሩ የነበረበት ብቸኛው ነገር ባይደንን ማታለል ብቻ ነበር " - ፕሬዜዳንት ትራምፕ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሊድሚር ዘለንስኪን " ትሁትና ውጤታማ ኮሜዲያን ነው " ሲሉ ወረፏቸው።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትሩዝ በተባለው የማህበራዊ ትስስር ገጻቸው የዩክሬኑን ፕሬዝዳንት ቮሊድሚር ዘለንስኪን " ያለ ምርጫ የተቀመጠ አምባገነን ነው " ብለዋል።
ትራምፕ ዩክሬን ከአሜሪካ ያገኘችውን ድጋፍ በውድ ማዕድናት እንድትከፍል እንደሚፈልጉ ተናገሩ
ትራምፕ " ትሁቱና ውጤታማ ኮሜዲያን ዘለንስኪ አሜሪካን 350 ቢሊየን ዶላር በማስውጣት መጀመር ያልነበረባቸው እና የማያሸንፉት ጦርነት ውስጥ ገብተዋል " ብለዋል።
" ዩክሬን ጦርነቱን ያለ አሜሪካ እና ትራምፕ በፍፁም መቋቋም አትችልም " ሲሉም ገልጸዋል።
ዜለንስኪ ከላክንለት ገንዘብ ግማሹ " የጠፋ " መሆኑን አምኗል ያሉት ትራምፕ " ምርጫ ለማድረግ ፈቃደኛ አይደለም፣ በዩክሬን የሕዝብ ዘንድ ያለው ተቀባይነት በጣም ዝቅተኛ ነው " ብለዋል።
" ዜለንስኪ ጥሩ የነበረበት ብቸኛው ነገር ባይደንን ማታለል ብቻ ነበር " ሲሉም ገልጸዋል።
" ያለ ምርጫ የተቀመጠ አምባገነን ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ በፍጥነት መንቀሳቀስ ይኖርበታል፤ ካልሆነ ግን የሚያተርፈው ሀገር አይኖርም " ብለዋል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አክውም " ዩክሬንን እወዳለሁ፣ ነገር ግን ዘለንስኪ አስከፊ ስራ ሰርቷል፣ ሚሊዮኖችም ያለምክንያት ሞተዋል እየሞቱም ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሊድሚር ዘለንስኪ " ዶናልድ ትራምፕ የሀሰት መረጃ ውስጥ እየኖሩ ወይንም በሀሰት መረጃ እየተነዱ ነው " ብለዋል።
ዩክሬን ከሩስያ ጋር ጦርነቱ ውስጥ እንዳለች ይታወቃል።
መረጃው የአል አይን ኒውስ ነው።
@tikvahethiopia
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሊድሚር ዘለንስኪን " ትሁትና ውጤታማ ኮሜዲያን ነው " ሲሉ ወረፏቸው።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትሩዝ በተባለው የማህበራዊ ትስስር ገጻቸው የዩክሬኑን ፕሬዝዳንት ቮሊድሚር ዘለንስኪን " ያለ ምርጫ የተቀመጠ አምባገነን ነው " ብለዋል።
ትራምፕ ዩክሬን ከአሜሪካ ያገኘችውን ድጋፍ በውድ ማዕድናት እንድትከፍል እንደሚፈልጉ ተናገሩ
ትራምፕ " ትሁቱና ውጤታማ ኮሜዲያን ዘለንስኪ አሜሪካን 350 ቢሊየን ዶላር በማስውጣት መጀመር ያልነበረባቸው እና የማያሸንፉት ጦርነት ውስጥ ገብተዋል " ብለዋል።
" ዩክሬን ጦርነቱን ያለ አሜሪካ እና ትራምፕ በፍፁም መቋቋም አትችልም " ሲሉም ገልጸዋል።
ዜለንስኪ ከላክንለት ገንዘብ ግማሹ " የጠፋ " መሆኑን አምኗል ያሉት ትራምፕ " ምርጫ ለማድረግ ፈቃደኛ አይደለም፣ በዩክሬን የሕዝብ ዘንድ ያለው ተቀባይነት በጣም ዝቅተኛ ነው " ብለዋል።
" ዜለንስኪ ጥሩ የነበረበት ብቸኛው ነገር ባይደንን ማታለል ብቻ ነበር " ሲሉም ገልጸዋል።
" ያለ ምርጫ የተቀመጠ አምባገነን ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ በፍጥነት መንቀሳቀስ ይኖርበታል፤ ካልሆነ ግን የሚያተርፈው ሀገር አይኖርም " ብለዋል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አክውም " ዩክሬንን እወዳለሁ፣ ነገር ግን ዘለንስኪ አስከፊ ስራ ሰርቷል፣ ሚሊዮኖችም ያለምክንያት ሞተዋል እየሞቱም ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሊድሚር ዘለንስኪ " ዶናልድ ትራምፕ የሀሰት መረጃ ውስጥ እየኖሩ ወይንም በሀሰት መረጃ እየተነዱ ነው " ብለዋል።
ዩክሬን ከሩስያ ጋር ጦርነቱ ውስጥ እንዳለች ይታወቃል።
መረጃው የአል አይን ኒውስ ነው።
@tikvahethiopia