በ6 ወሩ የፎረንሲክ ምርመራ ከተካሄደባቸው ሰነዶች ውስጥ 73 በመቶው ሀሰተኛ ናቸው ተባለ።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በ2017 በጀት ዓመት ስድስት ወራት ከቀረቡለት 191 የወንጀል ጉዳዮች እና 167 ከፍታብሔር ጋር የተያያዙ የምርመራ ጥያቄዎችን ከፖሊስና ከፍርድ ቤት ተቀብሎ በፎረንሲክ ምርመራ ማጣራቱን ገልጿል።
በዚህም የፎረንሲክ ምርመራ ከተካሄደባቸው 358 ሰነዶችን ውስጥ 73 በመቶ የሚሆኑት ሀሰተኛ መሆናቸውን አረጋግጫለሁ ሲል አስታውቋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባደራጀው የምርመራ ላብራቶሪ በሰነዶች ላይ የሚፈፀሙ ፊርማዎችን፣ በቲተሮችና በማህተሞች፣ በባንክ ቼኮች፣ በፖስፖርቶች፣ በተለያዩ ሀገር ገንዘቦች ላይ የተፈፀሙ ድልዝና ስርዞችን፣ በፅሁፎች እና በቁጥሮችን ይመረምራል።
በተጨማሪም ከውርስ ጋር የተያያዙ ሰነዶችን እና ከቦታ ካርታ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በመመርመር ትክክለኛ እና ሀሰተኛ መሆናቸውን የማረጋገጥ ሥራም ይሰራል።
በሀገራችን የፀረ-ሙስና አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 23 ሥር መንግሥታዊ እንዲሁም ሕዝባዊ ድርጅት ሰነዶችን በማስመሰል በሙሉ ወይም በከፊል የለወጠ፤ ያሻሻለ፤ የቀነሰ፤ የጨመረ ወይም በማጥፋት ወደ ሀሰተኛነት የለወጠ እንደ ወንጀሉ ክብደት እስከ እድሜ ልክ ጽኑ እስራት ያስቀጣል።
ኅብረተሰቡም ማንኛውም ዓይነት ውሎችን ሲዋዋል፣ Online ግብይቶች ሲያደርግና ሲፈርም በአጠቃላይ ከሰነድ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በሚገባ ማየትና ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
@tikvahethmagazine
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በ2017 በጀት ዓመት ስድስት ወራት ከቀረቡለት 191 የወንጀል ጉዳዮች እና 167 ከፍታብሔር ጋር የተያያዙ የምርመራ ጥያቄዎችን ከፖሊስና ከፍርድ ቤት ተቀብሎ በፎረንሲክ ምርመራ ማጣራቱን ገልጿል።
በዚህም የፎረንሲክ ምርመራ ከተካሄደባቸው 358 ሰነዶችን ውስጥ 73 በመቶ የሚሆኑት ሀሰተኛ መሆናቸውን አረጋግጫለሁ ሲል አስታውቋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባደራጀው የምርመራ ላብራቶሪ በሰነዶች ላይ የሚፈፀሙ ፊርማዎችን፣ በቲተሮችና በማህተሞች፣ በባንክ ቼኮች፣ በፖስፖርቶች፣ በተለያዩ ሀገር ገንዘቦች ላይ የተፈፀሙ ድልዝና ስርዞችን፣ በፅሁፎች እና በቁጥሮችን ይመረምራል።
በተጨማሪም ከውርስ ጋር የተያያዙ ሰነዶችን እና ከቦታ ካርታ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በመመርመር ትክክለኛ እና ሀሰተኛ መሆናቸውን የማረጋገጥ ሥራም ይሰራል።
በሀገራችን የፀረ-ሙስና አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 23 ሥር መንግሥታዊ እንዲሁም ሕዝባዊ ድርጅት ሰነዶችን በማስመሰል በሙሉ ወይም በከፊል የለወጠ፤ ያሻሻለ፤ የቀነሰ፤ የጨመረ ወይም በማጥፋት ወደ ሀሰተኛነት የለወጠ እንደ ወንጀሉ ክብደት እስከ እድሜ ልክ ጽኑ እስራት ያስቀጣል።
ኅብረተሰቡም ማንኛውም ዓይነት ውሎችን ሲዋዋል፣ Online ግብይቶች ሲያደርግና ሲፈርም በአጠቃላይ ከሰነድ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በሚገባ ማየትና ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
@tikvahethmagazine