Фильтр публикаций


“ በዩናይትድ እንደምቆይ አስባለሁ " ሆይሉንድ

ዴንማርካዊው የፊት መስመር ተጨዋች ራስሙስ ሆይሉንድ በቀጣይ በማንችስተር ዩናይትድ እቀጥላለሁ የሚል እምነት እንዳለው ተናግሯል።

የጣሊያን ሴርያው ክለብ ኢንተር ሚላን ራስሙስ ሆይሉንድን ለማስፈረም ጥረት በማድረግ ላይ መሆናቸው ሲዘገብ ነበር።

በሌላ በኩልጰማንችስተር ዩናይትድ በቀጣይ ከሚሸጣቸው ተጨዋቾች መካከል ራስሙስ ሆይሉንድ አንዱ ነው መባሉ ይታወሳል።

ስለወደፊት ቆይታው የተጠየቀው ራስሙስ ሆይሉንድ “ እስከ 2030 ኮንትራት አለኝ ስለዚህ በማንችስተር ዩናይትድ እንደምጫወት እጠብቃለሁ " ብሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


ቼልሲ የዝውውር ጥያቄ አቀረበ !

የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ የኤሲ ሚላኑን ግብ ጠባቂ ማይክ ሚግናን ለማስፈረም የዝውውር ጥያቄ ማቅረባቸው ተገልጿል።

ሰማያዊዎቹ ለግብ ጠባቂው ዝውውር 15 ሚልዮን ዩሮ የዝውውር ሒሳብ ማቅረባቸውን ጣልያናዊው ጋዜጠኛ ፋብሪዝዮ ሮማኖ ዘግቧል።

ፈረንሳዊው ግብ ጠባቂ ማይክ ሚግናን ቼልሲን መቀላቀል እንደሚፈልግ ከዚህ በፊት ሲነገር ነበር።

አሁን ላይ የዝውውር ሁኔታው በኤሲ ሚላን እጅ መሆኑ ሲገለፅ ቼልሲ የአለም ክለቦች ዋንጫ ዝውውር መስኮት ማክሰኞ ከመዘጋቱ በፊት ምላሽ እንደሚፈልጉ ተጠቁሟል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


" አርሰናል ቀጣይ ሊጉን ያሸንፋል " ጋሪ ኔቭል

የቀድሞ የማንችስተር ዩናይትድ ተጨዋች ጋሪ ኔቭል አርሰናል ቀጣዩን የፕርሚየር ሊግ ጨዋታ እንደሚያሸንፍ ተናግሯል።

" ቀጣይ አመት በድጋሜ አርሰናልን እደግፋለሁ " ያለው ጋሪ ኔቭል ቀጣዩን የሊግ ዋንጫ አርሰናል ያሸንፈዋል በማለት አስተያየቱን ሰጥቷል።

አርሰናሎች ባለፉት ሶስት አመታት ሁለተኛ መጨረሳቸውን ያነሳው ጋሪ ኔቭል “ ቀጣይ ይሳካላቸዋል "ብሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


ሬንደርስ ዛሬ የህክምና ምርመራውን ያደርጋል !

ኔዘርላንዳዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ሬንደርስ ወደ ማንችስተር ሲቲ የሚያደርገውን ዝውውር ለማጠናቀ ዛሬ የህክምና ምርመራውን እንደሚያደርግ አረጋግጧል።

ተጨዋቹ በሰጠው አስተያየት " ዛሬ ጠዋት ወደ ማንችስተር ሲቲ አምርቼ አመሻሹን እመለሳለሁ “ በማለት ተናግሯል።

ሬንደርስ በአሁኑ ሰዓት ለብሔራዊ ቡድኑ ግልጋሎት እየሰጠ የሚገኝ ሲሆን ኔዘርላንድ ማክሰኞ ከማልታ ጋር የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዋን ታደርጋለች።

ማንችስተር ሲቲ ተጫዋቹን 70 ሚልዮን ዩሮ በሚደርስ ሒሳብ ለማስፈረም ከኤሲ ሚላን ጋር መስማማታቸው አይዘነጋም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


Репост из: Betika Ethiopia Official Channel
ቀመረኛው!!
ዛሬም የሚያሸንፉባቸው የእለቱ የውርርድ ጥቆማዎች እነሆ!
አሁን ነው ማሸነፍ እድሜ ለቀመረኛው!!
ቀመረኛው - በቤቲካ ብቻ!


Ps5 Pro disk version + 1 jestic

Ps5 Pro digital +1 jestic

Ps5 Slim disk version + 1 jestic =95,000

Ps5 Slim digital + 1 jestic =85,000

Ps5 Fat disk version + 1 jestic =85,000

Ps4 Pro + 2 jestic=49,000

Ps4 Slim + 2 jestic=45,000

PlayStation 5 jestic=12,000

Available on Shop

CAN TV
Television ከኛ ጋር በፈለጉት አይነት በቅናሽ እኛ ዘንድ ያገኛሉ

ባሎት ማንኛውም እቃ መቀያየር ይቻላል
ብዛት አቅርበናል
ለክፍለ ሀገር እናቀርባለን ይደውሉ

🤝Tanks for choices

አድራሻ፡፦
ቁጥር 1  መገናኛ
ቁጥር 2  ቦሌ

ስልክ፦ 0910529770 ወይም                  0977349492
0914646972  ይደውሉ

ለአዳዲስ መረጃ Telegram channel join ይበሉ ፦
https://t.me/CanPlaystation

                       👍Update Your Life

    Can PlayStation እና Tv Market


በዝግ እንዲካሄድ ተወስኗል!

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በነገው ዕለት በወላይታ ድቻ እና ሲዳማ ቡና መካከል የሚደረገው የኢትዮጵያ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ "ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት በዝግ እንዲካሄድ ተወስኗል" ሲል ከደቂቃዎች በፊት አስታውቋል።

ፌዴሬሽኑ፥ "ጨዋታው በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (ETV) በቀጥታ ይተላለፋል" ሲል ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ጠቅሷል።

የሁለቱ ክለቦች የዋንጫ ጨዋታ በነገው ዕለት ከቀኑ 9:00 ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚካሄድ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


" ስፔን እንዴት እንደምትሸነፍ አላውቅም " ሮናልዶ

የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን አምበል ክርስቲያኖ ሮናልዶ “ ነገ ቀኑ ታሪክ የመስሪያ ነው “ ሲል በዛሬው የቡድኑ ልምምድ ላይ ተናግሯል።

“ ስፔንን እንዴት ማሸነፍ ይቻላል ተብሎ የተጠየቀው ሮናልዶ “ እንዴት ማሸነፍ እንደሚቻል አላውቅም “ ሲል ምላሽ ሰጥቷል።

“ ስፔን ብዙ ነገር የሰጠችኝ ሀገር ነች ለበርካታ አመታት በዛ ኖርያለሁ ቤተሰቦቼ እና ጓደኞቼ ስፔናዊ ናቸው ነገርግን ነገ ፖርቹጋል እንደምታሸንፍ ተስፋ አደርጋለሁ። “ ሮናልዶ

የስፔን እና ፖርቹጋል የኔሽንስ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታ ነገ ምሽት 4:00 ሰዓት አሊያንዝ አሬና ስታዲየም ላይ ይደረጋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


ቪክቶር ኦሲሜን ወደ አል ሂላል ያመራ ይሆን ?

ናይጄሪያዊው የፊት መስመር ተጨዋች ቪክቶር ኦሲሜን ወደ ሳውዲ አረቢያው ክለብ አል ሂላል ለማምራት መቃረቡ ተገልጿል።

አል ሂላል ተጫዋቹን በ 75 ሚልዮን ዩሮ ለማስፈረም ከናፖሊ ጋር ከስምምነት መድረሳቸውን የጣሊያን መገናኛ በዙሀን ዘግበዋል።

አሁን ላይ አል ሂላል ዝውውሩን ለማጠናቀቅ የቪክቶር ኦሲሜንን ይሁንታ በመጠባበቅ ላይ መሆናቸው ተገልጿል።

አሰልጣኝ ሲሞን ኢንዛጊን የሾመው አል ሂላል ቪክቶር ኦሲሜንን ወደ አለም ክለቦች ዋንጫ ይዞ ለመሄድ ከፍተኛ ጥረት ላይ መሆኑ ተገልጿል።

አል ሂላል ለቪክቶር ኦሲሜን በአመት 40 ሚልዮን ዩሮ ክፍያ እንዳቀረቡለት ተዘግቧል።

የቱርኩ ክለብ ጋላታሳራይ በበኩሉ ቪክቶር ኦሲሜንን በቋሚነት ለማቆየት በጥረት ላይ መሆናቸው ሲገለፅ ሌሎች ክለቦችም ጥያቄ አቅርበዋል ተብሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


አርሰናል ኬፓን እንዴት ለማስፈረም አሰበ ?

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የአሰልጣኝ ቡድን አባላት የኬፓ አሪዛባላጋ የረጅም ጊዜ አድናቂዎች እንደነበሩ ተገልጿል።

መድፈኞቹ ኬፓ አሪዛባላጋን ለማስፈረም የምልመላ ቡድናቸው ንግግር ሲያደርግ የአሁኑ የመጀመሪያው እንዳልሆነ ተነግሯል።

ኬፓ አሪዛባላጋ በውሉ ያለው አነስተኛ የኮንትራት ማፍረሻ ክፍያ ምክንያት የተለያዩ አማራጮች እንደሚቀርቡለት ተጠብቆ ነበር።

በአርሰናል ቤት የቡድኑን ቁጥር አንድ ግብ ጠባቂ ዴቪድ ራያን ሊያስቀምጥ እንደማይችል እንደሚረዳ የተገለጸው ኬፓ ይሁን እንጂ ለቦታው መፋለም እንደሚፈልግ ተነግሯል።

መድፈኞቹ ኬፓ በሪያል ማድሪድ እና ቼልሲ ቆይታው የቡድኑን ቁጥር 1️⃣ ግብ ጠባቂ የመርዳት አቅም እንዳለው አሳይቷል ብለው እንደሚያምኑ ተነግሯል።

ኬፓ አሪዛባላጋ ከዚህ በፊት በሁለቱ ክለቦች ኤድዋርድ ሜንዲ እና አንድሬ ሉኒንን እየተካ ሲያገለግል እንደነበር የሚታወስ ነው።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


ቼልሲ የፊት መስመር ተጨዋች ሊያስፈርም ነው !

የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ የቦርስያ ዶርትመንዱን የፊት መስመር ተጨዋች ጄሚ ጊቴንስ ለማስፈረም በመስራት ላይ መሆናቸው ተገልጿል።

ሰማያዊዎቹ ተጨዋቹን ለማስፈረም ለቦርስያ ዶርትመንድ የ 35 ሚልዮን ዩሮ የዝውውር ጥያቄ ማቅረባቸው ተነግሯል።

ቼልሲ እንግሊዛዊውን ተጨዋች ጄሚ ጊቴንስ የሰባት አመት ኮንትራት ለማስፈረም በግል ከስምምነት መድረሳቸው ተዘግቧል።

ከአምስት አመታት በፊት ከማንችስተር ሲቲ አካዳሚ ዶርትመንድን የተቀላቀለው ጄሚ ጊቴንስ ለዋናው ቡድን 106 ጨዋታዎች ማድረግ ችሏል።

የ 20ዓመቱ ጄሚ ጊቴንስ በተጠናቀቀው የውድድር አመት ጥሩ ጊዜ ሲያሳልፍ ለዶርትመንድ የሻምፒየንስ ሊግ አራት ግቦችን ጨምሮ 12 ጎሎች አስቆጥሯል።

በግራ የፊት መስመር መጫወት የሚቀናው ጄሚ ጊቴንስ በተጨማሪም የአጥቂ አማካይ ቦታ ተሰልፎ የመጫወት የተለየ ክህሎት እንዳለው ይነገራል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


ቶተንሀም የሴት ቡድኑን አሰልጣኝ አሰናበተ !

የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶተንሀም የሴቶች ቡድን አሰልጣኝ ሮበርት ቪላሀምን ከአሰልጣኝነት መሰናበታቸው ተገልጿል።

የክለቡ ሊቀመንበር ዳንኤል ሌቪ አሰልጣኝ አንሄ ፖስቴኮግሉን ባሰናበቱ በማግስቱ የሴት ቡድኑን አሰልጣኝ ከስራው አባረዋል።

አሰልጣኙ ባለፈው አመት ቡድኑን ተረክበው ስድስተኛ ደረጃን በመያዝ ሲያጠናቅቁ የኤፌ ካፕ ፍፃሜም መድረስ ችለዋል።

ቡድኑ በዘንድሮው የውድድር አመት ከወራጅ ቀጠናው በአንድ ደረጃ ከፍ ብሎ መጨረሱን ተከትሎ አሰልጣኙ ሊሰናበቱ እንደቻሉ ተነግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


አርሰናል ኬፓን ለማስፈረም ተቃርቧል !

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የቼልሲውን ግብ ጠባቂ ኬፓ አሪዛባላጋን ዝውውር ለማጠናቀቅ ከጫፍ መድረሳቸው ተገልጿል።

መድፈኞቹ ኬፓ አሪዛባላጋን የቡድኑ ቁጥር ሁለት ግብ ጠባቂ አድርገው ለማስፈረም እየሰሩ መሆኑ ተዘግቦ እንደነበር ይታወሳል።

አርሰናል አሁን ላይ የ 30ዓመቱ ኬፓ አሪዛባላጋ በቼልሲ ያለውን ኮንትራት ማፍረሻ 5 ሚልዮን ፓውንድ በመክፈል ለማስፈረም ተቃርበዋል።

ስፔናዊው ግብ ጠባቂ ኬፓ አሪዛባላጋ በአርሰናል ቤት የተሻለ የጨዋታ ሰዓት ለማግኘት ለመፎካከር ፍቃደኛ መሆኑ ተገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


አሌሀንድሮ ጋርናቾ ከዩናይትድ ጋር ሊለያይ ነው !

ማንችስተር ዩናይትድ ከአርጀንቲናዊው የፊት መስመር ተጨዋች አሌሀንድሮ ጋርናቾ ጋር እንደሚለያዩ ተገልጿል።

አሌሀንድሮ ጋርናቾ ማንችስተር ዩናይትድን እንደሚለቅ መረጋገጡ ተነግሯል።

አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም በቅርቡ አሌሀንድሮ ጋርናቾ ክለብ እንዲፈልግ እንዳሳወቁት ተዘግቦ እንደነበር አይዘነጋም።

በቀጣይ ጋርናቾን ለማስፈረም ሶስት የፕርሚየር ሊግ ክለቦች እንዲሁም የጣልያን ክለቦች ጥረት እያደረጉ መሆኑ ተጠቁሟል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


“ ፒኤስጂን በመልቀቄ አልፀፀትም “ ምባፔ

ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ ፒኤስጂ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ በማሸነፉ ደስተኛ መሆኑን ገልጿል።

ኪሊያን ምባፔ አክሎም ፒኤስጂ እሱ በለቀቀ ከአመት ባነሰ ጊዜ ሻምፒየንስ ሊግ ማሸነፉ በመልቀቅ ውሳኔው እንዲፀፀት እንደማያደርገው ተናግሯል።

" ከፒኤስጂ ጋር የነበረኝ ታሪክ ተፈፅሟል " ያለው ኪሊያን ምባፔ ምንም ቁጭት የለብኝም እጣፈንታ ነው ሲል ተደምጧል።

ሻምፒየንስ ሊግ ለማሳካት " ሁሉንም ነገር ያለመታከት ሞክሪያለሁ " የሚለው ተጨዋቹ ያለእኔ መሆን ነበረበት ፒኤስጂ ዋንጫው ይገባዋል ብሏል።

ኪሊያን ምባፔ በፒኤስጂ ባሳለፋቸው 7️⃣ አመታት 6️⃣ የፈረንሳይ ሊግ ዋንጫዎችን ቢያሳካም የሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ሳያሸንፍ ወደ ሪያል ማድሪድ አቅንቷል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


“ ማክቶሚናይ ዩናይትድ መሳሳቱን ሊያሳይ ፈልጎ ነበር “ ሮበርትሰን

ስኮትላንዳዊው የሊቨርፑል የመስመር ተጨዋች ሮበርትሰን ስኮት ማክቶሚናይ ያለውን አቅም ማሳየት ፈልጎ እንደነበር ገልጿል።

ባለፈው አመት ማንችስተር ዩናይትድን በመልቀቅ ናፖሊን የተቀላቀለው ስኮት ማክቶሚናይ የሴርያው የአመቱ ምርጥ ተጨዋች ሽልማት ማሸነፉ ይታወሳል።

" ማክቶሚናይ በናፖሊ ራሱን ማሳየት ፈልጎ ነበር " ያለው ሮበርትሰን በተጨማሪም ማንችስተር ዩናይትድ መሳሳቱን ማሳየት ፈልጎ ነበር ብሏል።

ሮበርትሰን አክሎም እሱ በርካታ ሰዎች ስለእሱ መሳሳታቸውን ማሳየት ፈልጎ ነበር ተሳክቶለታል ሲል ተናግሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


" ሊዮኔል ሜሲን እወደዋለሁ “ ሮናልዶ

ፖርቹጋላዊው ተጨዋች ክርስቲያኖ ሮናልዶ የምንጊዜም ባላንጣው ሊዮኔል ሚሲ ለእኔ አክብሮት አለው እኔም እወደዋለሁ በማለት ተናግሯል።

ከጋዜጠኞች ስለ ሊዮኔል ሜሲ ጥያቄ የቀረበለት ሮናልዶ “ እኛ በጋራ ለአስራ አምስት አመታት በትልቁ መድረክ ነበርን “ ሲል ተደምጧል።

" ሊዮኔል ሜሲን እወደዋለሁ " የሚለው ሮናልዶ አንድ ጊዜ ባሎን ዶር ቦታ ቋንቋ እንደተረጎምኩለት አስታውሳለሁ።ብሏል።

አክሎም " ሊዮኔል ሜሲ ሁልጊዜም በጥሩ ሁኔታ ነው የሚያናግረኝ እሱ በጣም ያከብረኛል " ሲል ሮናልዶ ተናግሯል።

ጫማውን መቼ እንደሚሰቅል የተጠየቀው ሮናልዶ " ነገ ጠዋት ተነስቼ ከዚህ በኋላ መጫወት አልፈልግም ልል እችላለሁ ነገርግን አሁን ላይ ደስተኛ ነኝ " ብሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


Репост из: WANAW SPORT WEAR
#Wanawsportswear ✔️

⭐️|🇱🇷
የላይቤሪያ የሴቶች ብሔራዊ ቡድን – በዋናው የስፖርት ትጥቅ
💪

እንኳን ደስ አለን በአፍሪካ የስፖርት መድረክ ኩራት ሆነዋል!
በሠላም ዘራይ አሰልጣኝነት የሚመራው የላይቤሪያ የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ማውሪታኒያ በተዘጋጀው የ2025 WAFU Women’s Cup በ3ተኛ ደረጃነት አጠናቀዋል።

👏🏽የዋናው ስፖርት ብራንድ አምባሳደር እና የላይቤሪያ የሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሠልጣኝ በሆነችው ሠላም ዘረዓይ ስኬት ታላቅ ኩርት እና ክብር ይሰማዋል!

ዋናው የስፖርት አልባሳት ብራንድ የላይቤሪያ የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ይፋዊ የስፖርት ትጥቅ አቅራቢ ስለሆነ ታላቅ ኩራት ይሰማዋል። ዋናው አፍሪካዊ ጀግናዎችን ማልበሱን ይቀጥላል። 🌍

ለበለጠ መረጃ
8️⃣2️⃣8️⃣9️⃣

🔗 ማህበራዊ ገጾቻችን🔗
Instagram|Facebook |TikTok |X|Youtube
🇪🇹በኢትዮጵያ የተመረተ | ⭐️ ይሄ ነው ዋናው !!!


ሮናልዶ በአለም ክለቦች ዋንጫ አይሳተፍም !

ክርስቲያኖ ሮናልዶ በቀጣዩ የአለም ክለቦች ዋንጫ ውድድር እንደማይሳተፍ በይፋ አስታውቋል።

ሮናልዶ በቀጣይ የአለም ክለቦች ዋንጫ ውድድር ላይ የሚሳተፍ ክለብ ሊቀላቀል ይችላል የሚሉ ዘገባዎች ሲወጡ እንደነበር ይታወሳል።

" በውድድሩ እንድሳተፍ ጥያቄዎች ቀርበውልኝ ነበር “ ያለው ሮናልዶ ነገርግን ውሳኔው ተወስኗል በውድድሩ አልሳተፍም ሲል አረጋግጧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


" ነገ ዋንጫውን እንወስደዋለን " ሮናልዶ

" ያማል እንዲያድግ ፍቀዱለት "

የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን አምበል ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከነገው የኔሽንስ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታ በፊት ከጋዜጠኞች ጋር ቆይታ አድርጓል።

ክርስቲያኖ ሮናልዶ ምን አለ ?

- "ነገሮች በጥሩ ሁኔታ እንደሚሄዱ እና ፖርቹጋል ዋንጫውን ይዛ እንደምትወጣ እርግጠኛ ነኝ።

- አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ በብሔራዊ ቡድኑ ጥሩ የሚባል ስራ እየሰሩ ነው የሚል እምነት አለኝ።

- ጨዋታው ከባድ እንደሚሆን እናውቃለን ፤ ስፔን በራስ መተማመን አላቸው ነገርግን እኛም ጥሩ ተጨዋቾች አሉን በጥሩ አስተሳሰብ ወደ ሜዳ እንገባለን።

- ላሚን ያማል ጥሩ ስራ እየሰራ ነው አቅሙን በጥሩ ሁኔታ ይጠቀማል።

-  እሱ ላይ ብዙ ጫና አታድርጉበት በጤናማ መንገድ እንዲያድግ እንፍቀድለት እሱ የችሎታ እጥረት የለበትም።

- የባሎን ዶር አሸናፊ መሆን ያለበት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ያሸነፈው ተጨዋች ነው።" ሲል ተደምጧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe

Показано 20 последних публикаций.