Фильтр публикаций


ሊቨርፑል ለፍፃሜ ደርሰዋል !

በእንግሊዝ ካራባኦ ካፕ ግማሽ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ ሊቨርፑል ከቶተንሀም ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 4ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።

የሊቨርፑልን የማሸነፊያ ግቦች ጋክፖ ፣ መሐመድ ሳላህ ፣ ስቦዝላይ እና ቫን ዳይክ አስቆጥረዋል።

ሊቨርፑል ቶተንሀምን በድምር ውጤት 4ለ1 በማሸነፍ ለካራባኦ ካፕ ፍፃሜ መድረሳቸውን አረጋግጠዋል።

በፍፃሜው ሊቨርፑል ከኒውካስል ዩናይትድ ጋር የካራባኦ ካፕ ፍፃሜ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ይሆናል።

የፍፃሜ ጨዋታው መጋቢት 7/2017 ዓ.ም በዌምብሌይ ስታዲየም የሚካሄድ ይሆናል።

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe

5.5k 0 3 25 135

80 '

ሊቨርፑል 4 - 0 ቶተንሀም

⚽ ጋክፖ
⚽ ሳላህ
⚽ ስቦዛላይ
⚽ ቫን ዳይክ

ድምር ውጤት :- 4-1

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


76 '

ሊቨርፑል 3 - 0 ቶተንሀም

⚽ ጋክፖ
⚽ ሳላህ
⚽ ስቦዛላይ

ድምር ውጤት :- 3-1

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


ኢንተር ሚላን ሽንፈት ገጠመው !

በጣልያን ሴርያ ተስተካካይ መርሐግብር ኢንተር ሚላን ከፊዮሬንቲና ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 3ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።

የፊዮሬንቲናን የማሸነፊያ ግቦች ሞይስ ኪን 2x እና ራኔሪ አስቆጥረዋል።

በአሰልጣኝ ሲሞን ኢንዛጊ የሚመራው ኢንተር ሚላን  ከአስራ ሰባት የሊግ ጨዋታዎች በኋላ ተሸንፏል።

በሊጉ ደረጃ ሰንጠረዥ ስንተኛ ናቸው ?

2️⃣ ኢንተር ሚላን :- 51 ነጥብ
4️⃣ ፊዮሬንቲና :- 42 ነጥብ

ቀጣይ መርሐግብር ?

ሰኞ -  ኢንተር ሚላን ከ ፊዮሬንቲና

@Tikvahethsport          @kidusyoftahe


60 '

ሊቨርፑል 2 - 0 ቶተንሀም

⚽ ጋክፖ
⚽ ሳላህ

ድምር ውጤት :- 2-1

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


52 '

ሊቨርፑል 2 - 0 ቶተንሀም

⚽ ጋክፖ
⚽ ሳላህ

ድምር ውጤት :- 2-1

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


  እረፍት

ሊቨርፑል 1 - 0 ቶተንሀም

⚽ ጋክፖ

ድምር ውጤት :- 1-1

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe

10k 0 0 17 57

35  '

ሊቨርፑል 1 - 0 ቶተንሀም

⚽ ጋክፖ

ድምር ውጤት :- 1-1

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


27 '

ሊቨርፑል 0 - 0 ቶተንሀም

ድምር ውጤት :- 0-1

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


15 '

ሊቨርፑል 0 - 0 ቶተንሀም

ድምር ውጤት :- 0-1

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


3 '

ሊቨርፑል 0 - 0 ቶተንሀም

ድምር ውጤት :- 0-1

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


አሊሰን ለምን ከጨዋታ ውጪ ሆነ ?

ብራዚላዊው የሊቨርፑል ግብ ጠባቂ አሊሰን ቤከር በምሽቱ የቶተንሀም ካራባኦ ካፕ ግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ አይሳተፍም።

አሊሰን ቤከር ከጨዋታው ውጪ የሆነው እረፍት ተሰጥቶት እንጂ ብቁ ካለመሆን ጋር የተገናኘ እንዳልሆነ ተገልጿል።

የሊቨርፑል እና ቶተንሀም ጨዋታ በአንፊልድ ምሽት 5:00 ሰዓት ይጀመራል።

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


የጨዋታ አሰላለፍ !

5:00 ሊቨርፑል ከ ቶተንሀም

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


“ የተለየ ድጋፍ ያስፈልገናል “ አርኔ ስሎት

የሊቨርፑሉ ዋና አሰልጣኝ አርኔ ስሎት የክለቡ ደጋፊዎች በምሽቱ የካራባኦ ካፕ ጨዋታ ደማቅ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

" ዛሬ የደጋፊዎች ድጋፍ ያስፈልገናል " ያሉት አርኔ ስሎት እንደዚህ አይነት ወሳኝ ጨዋታዎች ሲኖሩ ድጋፉ ልዩ እንደሆነ ተነግሮኛል ዛሬ እንጠብቃለን ብለዋል።

ቨርጅል ቫን ዳይክ በበኩሉ ለፍፃሜ ለመድረስ መጓጓታቸውን ገልፆ  " በአንፊልድ የማይረሳ ምሽት ማድረግ እንፈልጋለን " ብሏል።

ሊቨርፑል የመጀመሪያውን የካራባኦ ካፕ ግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ በቶተንሀም 1ለ0 መሸነፉ ይታወሳል።

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


አሸናፊ ግርማ የዋናው ብራንድ አምባሳደር ሆኖ ተሾመ !

የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ውጤታማ ተጨዋች አሸናፊ ግርማ የዋናው ስፖርት አልባሳት ብራንድ አምባሳደር በመሆን ተሹሟል።

በኢትዮጵያ የስፖርት ኢንደስትሪ ውስጥ በተቀላቀለ ጥቂት አመታት ውስጥ ተቀባይነት እያገኘ የመጣው ዋናው ስፖርት አሸናፊ ግርማን የሰሜን አሜሪካ ብራንድ አምባሳደር አድርጎ ሾሟል።

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በተደጋጋሚ የአመቱ ኮከብ ተጨዋች በመሆን አኩሪ ታሪክ የፃፈው አሸናፊ ግርማ በአሁን ሰዓት ኢትዮጵያን የሚያኮሩ የነገ ኮከቦችን ለማፍራት በታዳጊዎች ላይ እየሰራ ይገኛል።

በአሁኑ ሰዓት በካናዳ በአሰልጣኝንት ሙያ ላይ የሚገኘዉ አሸናፊ ግርማ በስምምነቱ ደስተኛ መሆኑን ገልፆ “ ይህ ስምምነት በኢትዮጵያ እና በካናዳ በእግር ኳስ ልማት ዙሪያ የምሰራቸዉን ስራዎች እንደሚያጠናክርልኝ እምነቴ ነዉ" ብሏል።

የዋናው ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀ/ስላሴ ገ/ክርስቶስ በበኩላቸው “ በኢትዮጵያ እግርኳስ ጉልህ አሻራቸዉን ካስቀመጡ ተጨዋቾች አንዱ አሸናፊ ግርማ ጋር በጋራ ለመስራት መስማማታችን አስደስቶኛል። ስምምነቱ ነገ ሀገራቸዉን የሚያኮሩ እግር ኳስ ተጨዋቾችን ለማፍራት የሚደረጉ ተግባራትን በጉልህ ያግዛል።" ብለዋል።

ዋናው ስፖርት በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ለተለያዩ ከለቦች እንዲሁም ለኢትዮጵያ ከ17ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የስፖርት ትጥቅ አቅራቢ መሆን ችሏል።

ዋናው ከሀገር ውጪ በመውጣትም የላይቤሪያ ዋናው ብሄራዊ ቡድን ይፋዊ የስፖርት ትጥቆች አቅራቢ ነዉ።

ይህም ኢትዮጵያዊውን የስፖርት አልባሳት ብራንድ "ዋናው ስፖርት'ን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች ላይ የታየ የመጀመሪያዉ ብራንድ ያደርገዋል።

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe


“ ፔሬዝ ፍላጎቱ ቢሮው በጉልበታችን እንድንበረከክ ነው “ - ዣቪየር ቴባስ

የስፔን ላሊጋው ፕሬዝዳንት ዣቪየር ቴባስ ሪያል ማድሪድ ዳኞቹን መውቀሱ ተገቢ አይደለም በማለት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ሪያል ማድሪድ ከቀናት በፊት በእስፓኞል በተሸነፈበት ጨዋታ ላይ የዳኝነት በደል እንደተፈፀመበት ባወጣው መግለጫ ገልፆ ነበር።

ክለቡ የስፔን እግርኳስ ፌዴሬሽን በጨዋታው የነበረውን የቫር ድምጽ ቅጂ እንዲሰጠው ጠይቋል።

“ ማድሪድ ዳኝነቱን ብቻ ሳይሆን ውድድሩንም መጉዳት ይፈልጋል “ ያሉት የላሊጋው ፕሬዝዳንት ዣቪየር ቴባስ ደብዳቤውን ፈርሞ ያወጣውን ስው መክሰስ ከቻልን እንመለከታለን ብለዋል።

ፕሬዚዳንቱ አክለውም “ ፍሎረንቲኖ ፔሬዝ ሁልጊዜ ትክክል መሆን ይፈልጋል እኛ ደግሞ ቢሮው በጉልበታችን እንድንበረከክ ነው ፍላጎቱ “ ሲሉ ተደምጠዋል።

የስፔን ላሊጋ ፣ እግርኳስ ፌዴሬሽኑ እና አብዛኞቹ ክለቦች ሪያል ማድሪድ ዳኞችን በመወንጀሉ እና ጫና በማሳደሩ እንዲቀጣ እንደሚፈልጉ ተገልጿል።

ሪያል ማድሪድ በበኩሉ ምባፔ ላይ ጥፋት ሲሰራ የነበረው የቫር ድምፅ ቅጂ እስከ ነገ አርብ ካልተሰጣቸው ለመክሰስ ወደ ከፍተኛ ፍርድ ቤት እንደሚያመሩ ማስጠንቀቃቸው ተነግሯል።

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


የማድሪድ ደርቢን ማን ይመራዋል ?

የላሊጋው መሪ ሪያል ማድሪድ ከአትሌቲኮ ማድሪድ የሚያደርጉትን ተጠባቂ ጨዋታ የሚመሩት ዳኛ ታውቀዋል።

ቅዳሜ ምሽት 5:00 ሳንቲያጎ በርናቦ ላይ የሚደረገውን ተጠባቂ ጨዋታ ሴሳ ሶቶ ግራዶ በመሐል ዳኝነት እንደሚመሩት ይፋ ተደርጓል።

የመሐል ዳኛው በቅርቡ ሪያል ማድሪድ ከቫሌንሼያ በረበረው ጨዋታ ለቪንሰስ ጁኒየር ቀይ ካርድ መዘው ነበር።

ዳኛው ከዚህ በፊት በሁለት አጋጣሚዎች የማድሪድ ደርቢን የመሩ ሲሆን ሁለቱ ክለቦች አንድ አንድ ጊዜ ተሸናንፈዋል።

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


“ የዋህ አይደለሁም አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ነን “ አሞሪም

የማንችስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም ቡድኑን ከመረከቤ በፊት ስለሚመጣው ጫና አውቅ ነበር በማለት ተናግረዋል።

“ እኔ የዋህ ሰው አይደለሁም “ የሚሉት አሞሪም “ ብዙ ጊዜ ተናግሬያለሁ እግርኳስ በውጤት ላይ የተመሰረተ ስፖርት ነው  “ ሲሉ “ አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ነን “ ብለዋል።

አሰልጣኙ አክለውም “ የሚገጥመን አስቸጋሪ ሁኔታ እስከ ውድድር ዘመኑ መጨረሻ ይቀጥላል “ በማለት ተናግረዋል።

“ ጫናው የሚጠበቅ እና አስደሳች ነው ፤ ቡድኑን ለመረከብ ስስማማ ይህ እንደሚገጥመኝ አውቅ ነበር።“ ሩበን አሞሪም

ስለ ራሽፎርድ የተጠየቁት አሰልጣኙ “ እሱ አሁን የአስቶን ቪላ ተጨዋች ነው ይህንን ጥያቄ እነሱን መጠየቅ ትችላላችሁ " ሲሉ ለጋዜጠኞች መልሰዋል።

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


“ አርሰናል ሀሪ ኬንን መመልከት አለበት “ - ፖል ሜርሰን

እንግሊዛዊው የቀድሞ ተጨዋች ፖል ሜርሰን አርሰናል ቀጣይ ጥር ላይ ሀሪ ኬንን ስለ ማስፈረም ማሰብ እንዳለበት ተናግሯል።

እንግሊዛዊው ተጨዋች ሀሪ ኬን በሚቀጥለው ጥር ወር ውሉን በ 54 ሚልዮን ፓውንድ በማፍረስ ሌላ ክለብ መቀላቀል ይችላል።

“ አርሰናል ይህንን እድል እንዲጠቀምበት እመክራለሁ “ ያለው ፖል ሜርሰን የማይሆንበት ምክንያት የለም “ሲል ተናግሯል።

“ አርሰናል ክረምት ላይ ወይም በጥር ወር አጥቂ ማስፈረም ያስፈልገዋል “ ያለው ፖል ሜርሰን አክሎም ሶሎ ካምቤል ከዚህ በፊት አድርጎ አሳይቶናል “ ብሏል።

እንግሊዛዊው የቀድሞ ተከላካይ ሶል ካምቤል ከዚህ በፊት ከቶተንሀም በመልቀቅ ተቀናቃኛቸውን አርሰናል ተቀላቅሎ መጫወቱ የሚታወስ ነው።

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


የሴርያ የወሩ ምርጥ ተጨዋች ታውቋል !

የ 2024/25 የውድድር ዘመን የጣልያን ሴርያ የወርሀ ጥር የወሩ ምርጥ ተጨዋች ይፋ ተደርጓል።

በዚህም መሰረት የናፖሊው አማካይ አንድሬ ፍራንክ ዛምቦ አንጉይሳ የጥር ወር የሴርያው ምርጥ ተጨዋች በመባል ተመርጧል።

ካሜሮናዊው አማካይ አንጉይሳ በወሩ ባደረጋቸው የሴርያ ጨዋታዎች 2️⃣ ግቦችን አስቆጥሮ 2️⃣ አመቻችቶ አቀብሏል።

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe

Показано 20 последних публикаций.