የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት እርዳታ ማቋረጡ ኢትዮጵያ በኤች አይ ቪ ላይ የምታደርገውን ትግል አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን የመንግስታቱ ድርጅት አስታወቀ
ከሩብ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የቫይረሱ ተጠቃሚዎችን ለአደጋ ያጋልጣል ሲል አስጠንቅቋል
ከኤች አይ ቪ/ኤድስ ጋር በተያያዘ የአሜሪካ መንግስት ለኢትዮጵያ የሚሰጠው ድጋፍና እርዳታ መቋረጥ በኦሮሚያ እና ጋምቤላ ክልሎች እንዲሁም በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ ከ270 ሺ በላይ ለሚሆኑ የቫይረሱ መከላከያ መድሃኒት ተጠቃሚዎችን ህይወት ይበልጥ ከባድ ያደርገዋል ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኤች አይ ቪ/ኤድስ ፕሮግራም አስጠንቀቀ።
በርካቶች ኤች አይቪን ጨምሮ በግብረ ሥጋ ግንኙነት ወቅት የሚተላለፉ በሽታዎችን ለመከላከል የሚውል ኮንዶም ከአሁን በኋላ አይደርሳቸውም ብሏል።
በተጨማሪም የገንዘብ ድጋፍ መቋረጡ የአካባቢ ጤና አጠባበቅ አቅም ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት እንዳያደናቅፈው ስጋት እንዳለው አስታውቋል፤ የጤና ባለሙያዎች የሚሰጡት ስልጠና ላይ ተፅዕኖ በማሳደር በኢትዮጵያ የኤችአይቪ በሽታ መከላከል ሂደት ላይ እየተመዘገበ ያለውን እድገት ያዘገየዋል ሲል አመልክቷል።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1
ከሩብ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የቫይረሱ ተጠቃሚዎችን ለአደጋ ያጋልጣል ሲል አስጠንቅቋል
ከኤች አይ ቪ/ኤድስ ጋር በተያያዘ የአሜሪካ መንግስት ለኢትዮጵያ የሚሰጠው ድጋፍና እርዳታ መቋረጥ በኦሮሚያ እና ጋምቤላ ክልሎች እንዲሁም በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ ከ270 ሺ በላይ ለሚሆኑ የቫይረሱ መከላከያ መድሃኒት ተጠቃሚዎችን ህይወት ይበልጥ ከባድ ያደርገዋል ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኤች አይ ቪ/ኤድስ ፕሮግራም አስጠንቀቀ።
በርካቶች ኤች አይቪን ጨምሮ በግብረ ሥጋ ግንኙነት ወቅት የሚተላለፉ በሽታዎችን ለመከላከል የሚውል ኮንዶም ከአሁን በኋላ አይደርሳቸውም ብሏል።
በተጨማሪም የገንዘብ ድጋፍ መቋረጡ የአካባቢ ጤና አጠባበቅ አቅም ለመገንባት የሚደረገውን ጥረት እንዳያደናቅፈው ስጋት እንዳለው አስታውቋል፤ የጤና ባለሙያዎች የሚሰጡት ስልጠና ላይ ተፅዕኖ በማሳደር በኢትዮጵያ የኤችአይቪ በሽታ መከላከል ሂደት ላይ እየተመዘገበ ያለውን እድገት ያዘገየዋል ሲል አመልክቷል።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1