“ነፍሳችንን ቢያስከፍለን እንኳን ጋዛን አንለቅም”- የጋዛ ነዋሪዎች
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋዛን የመቆጣጠር እቅድ እንዳላቸው መግለጻቸውን ተከትሎ በርካታ ፍልስጤማውያን ተቃውሟቸውን እየገለጹ ነው።
በትራምፕ ውሳኔ የተገረሙ እና የተደናገጡ የጋዛ ነዋሪ ፍሊጤየማውያን “ጋዛን ለቀን አንወጣም” ሲሉ ተቃውሞዋቸውን አሰምተዋል።
በዴይር አል ባላህ በድንኳን መጠለያ ውስጥ የሚገኙ የጋዛ ነዋሪዎች ከቢቢሲ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የጋዛ ነዋሪዎችን በቋሚነት ወደ ሌላ ስፍራ ለማስፈር የተያዘው እቅድ እንዳስደነገጣቸው በመግለጽ እቅዱ ተቀባይነት የለውም ሲሉ እምቢተኝነታቸውን አመላክተዋል።
“ነፍሳችንን ቢያስከፍለን እንኳን ጋዛን አንለቅም” ያሉት ነዋሪዎቹ፤ “የትራምፕን ውሳኔ እንቃወማለን፣ ጦርቱን አስቁሟል፤ ነገር ግን እኛን ማፈናቀል ህይወታችን እንዲያበቃለት ያደርጋል” ብለዋል።
"በአሜሪካ የተሰራችው እስራኤል በጋዛ የሚገኘውን ቤቶቻችንን ካፈረሰች በኋላ ከፍርስራሽ መውጣት እንዳለብን እየተነገረን ነው፤ በልጆቻችን ውስጥ አንድ የደም ጠብታ እንኳ ቢቀር ጋዛን አንለቅም፣ ተስፋም አንቆርጥም” ብለዋል ነዋሪዎቹ።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ወደ ዋይትሃውስ እንደገቡ የጋዛ ፍርስራሽ እስኪጸዳ ድረስ ፍልስጤማውያን እንደ ግብጽ እና ዮርዳኖስ ባሉ ሀገራት እንዲጠለሉ ሃሳብ ማቅረባቸው ይታወሳል።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋዛን የመቆጣጠር እቅድ እንዳላቸው መግለጻቸውን ተከትሎ በርካታ ፍልስጤማውያን ተቃውሟቸውን እየገለጹ ነው።
በትራምፕ ውሳኔ የተገረሙ እና የተደናገጡ የጋዛ ነዋሪ ፍሊጤየማውያን “ጋዛን ለቀን አንወጣም” ሲሉ ተቃውሞዋቸውን አሰምተዋል።
በዴይር አል ባላህ በድንኳን መጠለያ ውስጥ የሚገኙ የጋዛ ነዋሪዎች ከቢቢሲ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የጋዛ ነዋሪዎችን በቋሚነት ወደ ሌላ ስፍራ ለማስፈር የተያዘው እቅድ እንዳስደነገጣቸው በመግለጽ እቅዱ ተቀባይነት የለውም ሲሉ እምቢተኝነታቸውን አመላክተዋል።
“ነፍሳችንን ቢያስከፍለን እንኳን ጋዛን አንለቅም” ያሉት ነዋሪዎቹ፤ “የትራምፕን ውሳኔ እንቃወማለን፣ ጦርቱን አስቁሟል፤ ነገር ግን እኛን ማፈናቀል ህይወታችን እንዲያበቃለት ያደርጋል” ብለዋል።
"በአሜሪካ የተሰራችው እስራኤል በጋዛ የሚገኘውን ቤቶቻችንን ካፈረሰች በኋላ ከፍርስራሽ መውጣት እንዳለብን እየተነገረን ነው፤ በልጆቻችን ውስጥ አንድ የደም ጠብታ እንኳ ቢቀር ጋዛን አንለቅም፣ ተስፋም አንቆርጥም” ብለዋል ነዋሪዎቹ።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ወደ ዋይትሃውስ እንደገቡ የጋዛ ፍርስራሽ እስኪጸዳ ድረስ ፍልስጤማውያን እንደ ግብጽ እና ዮርዳኖስ ባሉ ሀገራት እንዲጠለሉ ሃሳብ ማቅረባቸው ይታወሳል።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1