ዩክሬን ከሩሲያ ጋር የ30 ቀን የተኩስ አቁም ስምምነትን ለመቀበል ዝግጁ መሆኗ ተሰማ
በሳውዲ አረቢያ ከአንድ ቀን የዩናይትድ ስቴትስ እና የዩክሬን ውይይት በኋላ በአሜሪካ የቀረበውን የ30 ቀን የተኩስ አቁም ስምምነት ዩክሬን ለመቀበል ዝግጁ መሆኗን ተናግራለች። የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ዋና ፀሀፊ ማርኮ ሩቢዮ ይህንኑ ሀሳብ ለሩሲያ እንደሚያቀርቡ እና " አሁን ኳሱ በእጃቸው ውስጥ ነው" ሲሉ ተደምጠዋል።የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዶሚር ዘለንስኪ እንዳሉት ሩሲያ በ"አዎንታዊ" ሀሳብ እንድትስማማ የማሳመን ድርሻ የዩናይትድ ስቴትስ ብቻ ነው ብለዋል።
የማክሰኞው የጄዳ ንግግር በዜለንስኪ እና በአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሞላላው የዋይት ሀውስ ቢሮ ውስጥ ከተፈጠረው ያልተለመደ ግጭት በኋላ በሁለቱ ሀገራት መካከል የመጀመሪያው ይፋዊ ውይይት ነው።በጋራ የሁለቱ ሀገራት ተወካዮች በሰጡት መግለጫ፣ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ የትራምፕ እና የዜለንስኪን ግጭት ተከትሎ ዋሽንግተን ያቋረጠችውን ለዩክሬን የስለላ መረጃ ልውውጥ እና የደህንነት ድጋፍ ወዲያውኑ እንደገና እንደሚጀምር ተናግራለች። የአሜሪካ እና ዩክሬን መግለጫ እንደሚያሳየው “ሁለቱም ልዑካን ቡድን ተደራዳሪ ቡድኖቻቸውን ለመሰየም መስማማታቸውን እና ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የዩክሬን ደህንነትን ለማስፈን ድርድር ይጀምራሉ” ይላል።
ሩቢዮ ማክሰኞ ማምሻውን በጄዳህ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ሩሲያ ሃሳቡን እንደምትቀበል ተስፋ አደርጋለው ብለዋል። ዩክሬን " ተኩስ ለማቆም እና ለመነጋገር ዝግጁ ነች" ሲሉ አክለዋል። ሩሲያ የተኩስ አቁም ስምምነቱን ውድቅ ካደረገች " በሚያሳዝን ሁኔታ ሰላም ለማምጣት እንቅፋት የሆነው ማን እንደሆነ እናውቃለን" ብለዋል። "ዛሬ ዩክሬናውያን የተቀበሉትን ሀሳብ አቅርበናል ይህም የተኩስ ማቆም እና አፋጣኝ ድርድር ለማድረግ ነው።"፤ "ይህንኑ ለሩሲያውያን እናቀርባለን እናም ለሰላም አዎ እንደሚሉ ተስፋ እናደርጋለን፤ ኳሱ አሁን በእነሱ ግቢ ውስጥ ነው" ሲሉ ተደምጠዋል።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1
በሳውዲ አረቢያ ከአንድ ቀን የዩናይትድ ስቴትስ እና የዩክሬን ውይይት በኋላ በአሜሪካ የቀረበውን የ30 ቀን የተኩስ አቁም ስምምነት ዩክሬን ለመቀበል ዝግጁ መሆኗን ተናግራለች። የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ዋና ፀሀፊ ማርኮ ሩቢዮ ይህንኑ ሀሳብ ለሩሲያ እንደሚያቀርቡ እና " አሁን ኳሱ በእጃቸው ውስጥ ነው" ሲሉ ተደምጠዋል።የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዶሚር ዘለንስኪ እንዳሉት ሩሲያ በ"አዎንታዊ" ሀሳብ እንድትስማማ የማሳመን ድርሻ የዩናይትድ ስቴትስ ብቻ ነው ብለዋል።
የማክሰኞው የጄዳ ንግግር በዜለንስኪ እና በአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሞላላው የዋይት ሀውስ ቢሮ ውስጥ ከተፈጠረው ያልተለመደ ግጭት በኋላ በሁለቱ ሀገራት መካከል የመጀመሪያው ይፋዊ ውይይት ነው።በጋራ የሁለቱ ሀገራት ተወካዮች በሰጡት መግለጫ፣ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ የትራምፕ እና የዜለንስኪን ግጭት ተከትሎ ዋሽንግተን ያቋረጠችውን ለዩክሬን የስለላ መረጃ ልውውጥ እና የደህንነት ድጋፍ ወዲያውኑ እንደገና እንደሚጀምር ተናግራለች። የአሜሪካ እና ዩክሬን መግለጫ እንደሚያሳየው “ሁለቱም ልዑካን ቡድን ተደራዳሪ ቡድኖቻቸውን ለመሰየም መስማማታቸውን እና ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የዩክሬን ደህንነትን ለማስፈን ድርድር ይጀምራሉ” ይላል።
ሩቢዮ ማክሰኞ ማምሻውን በጄዳህ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ሩሲያ ሃሳቡን እንደምትቀበል ተስፋ አደርጋለው ብለዋል። ዩክሬን " ተኩስ ለማቆም እና ለመነጋገር ዝግጁ ነች" ሲሉ አክለዋል። ሩሲያ የተኩስ አቁም ስምምነቱን ውድቅ ካደረገች " በሚያሳዝን ሁኔታ ሰላም ለማምጣት እንቅፋት የሆነው ማን እንደሆነ እናውቃለን" ብለዋል። "ዛሬ ዩክሬናውያን የተቀበሉትን ሀሳብ አቅርበናል ይህም የተኩስ ማቆም እና አፋጣኝ ድርድር ለማድረግ ነው።"፤ "ይህንኑ ለሩሲያውያን እናቀርባለን እናም ለሰላም አዎ እንደሚሉ ተስፋ እናደርጋለን፤ ኳሱ አሁን በእነሱ ግቢ ውስጥ ነው" ሲሉ ተደምጠዋል።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1