"ክህሎት ስለ ኢትዮጵያ " የተሰኘ የፎቶ ግራፍ አውደ ርዕይ ተከፈተ
በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት "ክህሎት ስለኢትዮጵያ" በሚል ርዕስ የተዘጋጀው የፎቶግራፍ አውደ ርዕይ እና ፓናል ውይይት በሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል ተከፍቷል።
የፎቶ ግራፍ አውደ ርዕዩ በአዲስ አበባ የተከፈተ ሲሆን በዚህም ጥንታዊ የክህሎት አጀማመር መሠረቶች፣ በሰመር ካምፕ እና በስታርት አፕ የተሰሩ ሥራዎች፣ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት ተማሪዎች የተሰሩ ማሽኖች እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ የተገኙ ውጤቶች ለእይታ ቀርበዋል።
በመክፈቻው የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚልን ጨምሮ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ተሻለ በሬቻ፣ አቶ ዳንኤል ተሬሳ፣ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፀዳለ ተክሉ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት (ኢፕድ) በምዕራፍ አንድ ስለኢትዮጵያ መድረኩ በ14 የተለያዩ ከተሞች በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይትና ምክክር ማካሄዱ ይታወሳል።
ሁለተኛው ምዕራፍ ደግሞ በቡታጅራና በሐረር ተካሄዷል። ይህ በአዲስ አበባ የሚካሄደው መድረክ የሁለተኛው ምዕራፍ ሶስተኛ ዙር ነው። በድምሩ "ስለኢትዮጵያ" የተሰኘው መድረክ የዛሬውን ጨምሮ ለ17ተኛ ጊዜ ተካሄዷል።
የኢፕድ ስለኢትዮጵያ የፎቶግራፍ አውደ ርዕይና የፓናል ውይይት የሁለተኛ ምዕራፍ የፎቶግራፍ አውደ ርዕዩና የፓናል ውይይቱ በቀጣይም በተለያዩ ከተሞች እንደሚካሄድ ይጠበቃል።
#ዳጉ_ጆርናል
በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት "ክህሎት ስለኢትዮጵያ" በሚል ርዕስ የተዘጋጀው የፎቶግራፍ አውደ ርዕይ እና ፓናል ውይይት በሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል ተከፍቷል።
የፎቶ ግራፍ አውደ ርዕዩ በአዲስ አበባ የተከፈተ ሲሆን በዚህም ጥንታዊ የክህሎት አጀማመር መሠረቶች፣ በሰመር ካምፕ እና በስታርት አፕ የተሰሩ ሥራዎች፣ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት ተማሪዎች የተሰሩ ማሽኖች እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ የተገኙ ውጤቶች ለእይታ ቀርበዋል።
በመክፈቻው የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚልን ጨምሮ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ተሻለ በሬቻ፣ አቶ ዳንኤል ተሬሳ፣ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፀዳለ ተክሉ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት (ኢፕድ) በምዕራፍ አንድ ስለኢትዮጵያ መድረኩ በ14 የተለያዩ ከተሞች በዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይትና ምክክር ማካሄዱ ይታወሳል።
ሁለተኛው ምዕራፍ ደግሞ በቡታጅራና በሐረር ተካሄዷል። ይህ በአዲስ አበባ የሚካሄደው መድረክ የሁለተኛው ምዕራፍ ሶስተኛ ዙር ነው። በድምሩ "ስለኢትዮጵያ" የተሰኘው መድረክ የዛሬውን ጨምሮ ለ17ተኛ ጊዜ ተካሄዷል።
የኢፕድ ስለኢትዮጵያ የፎቶግራፍ አውደ ርዕይና የፓናል ውይይት የሁለተኛ ምዕራፍ የፎቶግራፍ አውደ ርዕዩና የፓናል ውይይቱ በቀጣይም በተለያዩ ከተሞች እንደሚካሄድ ይጠበቃል።
#ዳጉ_ጆርናል