ሩሲያ ባለፈው ሳምንት ግዙፍ የሰው አልባ አውሮፕላኖች እና የሚሳኤል ጥቃቶች ፈፅማብኛለች ስትል ዩክሬን አስታወቀች
ዩክሬን ሩሲያ በአንድ ጀምበር 119 አጥቂ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን በበርካታ ክልሎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ፈፅማብኛለት በማለት ባሳለፍነው ሳምንት የተለያዩ መሳሪያዎችን በመጠቀም በመቶዎች የሚቆጠሩ ጥቃቶችን ሞስኮ መሰንዘሯን ተናግራለች። የዩክሬን አየር ሃይል እንደዘገበው 73 የሻሄድ አይነት ሰው አልባ አውሮፕላኖች እና ሌሎች ዩኤቪዎች በተለያዩ ክልሎች ጥቃት እንዳያዱርሱ ተመትተው ሲጣሉ 37 የጠላት አታላይ አውሮፕላኖች ከክትትል ራዳር ጠፍተዋል ነገርግን ምንም አይነት ጉዳት አላደረሱም ብሏል።
ጥቃቶች በዶኔትስክ፣ ካርኪቭ፣ ፖልታቫ፣ ቼርካሲ፣ ሱሚ እና ዛፖሪዝሂያ አካባቢዎች ላይ ጉዳት አድርሰዋል ሲሉ ባለስልጣናቱ ገልጸዋል። ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ባለፈው ሳምንት ሩሲያ “1,200 የሚጠጉ የአየር ላይ ቦምቦችን፣ 870 የሚጠጉ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን እና ከ80 የሚበልጡ ሚሳኤሎችን” በመጠቀም በዩክሬን ላይ “በመቶዎች የሚቆጠሩ ጥቃቶችን” ባለፈው ሳምንት ውስጥ ብቻ እንደከፈተች ተናግረዋል። “እያንዳንዱ ሻሄድ ሰው አልባ አውሮፕላን እና ሩሲያ የምትጠቀመው እያንዳንዱ የአየር ላይ ቦምብ ማዕቀብን በመጣስ የተፈፀሙ ጥቃቶች ናቸዋ። ይህ መሳሪያ ከ 82,000 በላይ የውጭ አገር ሰራሽ ክፍሎችን ይዟል ሲል ዘሌንስኪ በቴሌግራም ጽፏል።
ዩክሬን ከአጋሮቿ ጋር በየቀኑ ተጨማሪ የአየር መከላከያ ዘዴዎችን ፣በአገር ውስጥ መከላከያ ምርት ላይ ኢንቨስት ለማድረግ እና በሩሲያ ላይ ጠንካራ ማዕቀቦች እንዲጤል እየሰራች መሆኑን አፅንዖት ሰጥታለች። "ፍትሃዊ ሰላም ለማምጣት እና አስተማማኝ የደህንነት ዋስትናዎችን ለማረጋገጥ ስራችንን እንቀጥላለን" ብለዋል። ዩክሬን ምዕራባውያን አጋሮች ወደ ሩሲያ በሚላኩ የቴክኖሎጂ ምርቶች ላይ ገደቦችን እንዲያጠናክሩ ደጋግማ በመጠየቅ፣ ማዕቀቡ ቢጣልባትም ከውጭ የተሰሩ ወሳኝ የጦር መሳሪያ አካላትን ሩሲያ ማግኘቷን ቀጥላለች ስትል ኬየቭ አስታውቃለች።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
ዩክሬን ሩሲያ በአንድ ጀምበር 119 አጥቂ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን በበርካታ ክልሎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ፈፅማብኛለት በማለት ባሳለፍነው ሳምንት የተለያዩ መሳሪያዎችን በመጠቀም በመቶዎች የሚቆጠሩ ጥቃቶችን ሞስኮ መሰንዘሯን ተናግራለች። የዩክሬን አየር ሃይል እንደዘገበው 73 የሻሄድ አይነት ሰው አልባ አውሮፕላኖች እና ሌሎች ዩኤቪዎች በተለያዩ ክልሎች ጥቃት እንዳያዱርሱ ተመትተው ሲጣሉ 37 የጠላት አታላይ አውሮፕላኖች ከክትትል ራዳር ጠፍተዋል ነገርግን ምንም አይነት ጉዳት አላደረሱም ብሏል።
ጥቃቶች በዶኔትስክ፣ ካርኪቭ፣ ፖልታቫ፣ ቼርካሲ፣ ሱሚ እና ዛፖሪዝሂያ አካባቢዎች ላይ ጉዳት አድርሰዋል ሲሉ ባለስልጣናቱ ገልጸዋል። ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ባለፈው ሳምንት ሩሲያ “1,200 የሚጠጉ የአየር ላይ ቦምቦችን፣ 870 የሚጠጉ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን እና ከ80 የሚበልጡ ሚሳኤሎችን” በመጠቀም በዩክሬን ላይ “በመቶዎች የሚቆጠሩ ጥቃቶችን” ባለፈው ሳምንት ውስጥ ብቻ እንደከፈተች ተናግረዋል። “እያንዳንዱ ሻሄድ ሰው አልባ አውሮፕላን እና ሩሲያ የምትጠቀመው እያንዳንዱ የአየር ላይ ቦምብ ማዕቀብን በመጣስ የተፈፀሙ ጥቃቶች ናቸዋ። ይህ መሳሪያ ከ 82,000 በላይ የውጭ አገር ሰራሽ ክፍሎችን ይዟል ሲል ዘሌንስኪ በቴሌግራም ጽፏል።
ዩክሬን ከአጋሮቿ ጋር በየቀኑ ተጨማሪ የአየር መከላከያ ዘዴዎችን ፣በአገር ውስጥ መከላከያ ምርት ላይ ኢንቨስት ለማድረግ እና በሩሲያ ላይ ጠንካራ ማዕቀቦች እንዲጤል እየሰራች መሆኑን አፅንዖት ሰጥታለች። "ፍትሃዊ ሰላም ለማምጣት እና አስተማማኝ የደህንነት ዋስትናዎችን ለማረጋገጥ ስራችንን እንቀጥላለን" ብለዋል። ዩክሬን ምዕራባውያን አጋሮች ወደ ሩሲያ በሚላኩ የቴክኖሎጂ ምርቶች ላይ ገደቦችን እንዲያጠናክሩ ደጋግማ በመጠየቅ፣ ማዕቀቡ ቢጣልባትም ከውጭ የተሰሩ ወሳኝ የጦር መሳሪያ አካላትን ሩሲያ ማግኘቷን ቀጥላለች ስትል ኬየቭ አስታውቃለች።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል