🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹🔹
ልብ አንጠልጣይ የ ፍቅር ታሪክ በመልካም ልቦች የ ቴሌግራም ቻናል ተዘጋጅቶ የቀረበ💟
⭐️ክፍል 🟰4️⃣
ብቻ የዛን ቀን ውጤቱን ሲያይ አይሞቀው አይበርደው በቃ የጠበቀው ነገር እንዳገኘ ግልፅ ነው።
ማታ ቤት እንደገባሁ ግሩፓችን ውስጥ ገብቼ የሱን ስም ፈለኩና እራሴ ፃፍኩለት ለካ እንደዚህ ጎበዝ ነህ በቃ ታስጠናኛለህ አልኩት ለመቀለድ መሞከሬ ነበር በኔ ቤት።
አረ ባክሽ አስጠናሀለሁ ለማለት ፈልገሽ ነው አለኝ።
አንተኮ ነህ የበለጥከኝ ??
እኔ እንደበለጥኩሽ በምን አወቅሽ የኔን ውጤት ስትከታተይ ነበር ማለት ነው አለኝ።
አረ አደለም እንዲሁ ከፊት ለፊት ስለምትቀመጥ አጋጣሚ ነው እንጂ አልኩት።
እሺ አለኝ።
እሺ ሲለኝ እልህ ነገር ያዘኝ ይሁን ወይ እኔጃ ብቻ ግን ንዴት በሚመስል መልኩ ማውራት አልፈለክም እንዴ አልኩት።
ማውራት ባልፈልግኮ እንደባለፈው እንዳንቺ የተፃፃፍነውን አጠፋው ነበር አለኝ።
ኦኦ በሱ ተናደህ ነው እንዴ ይቅርታ በቃ አልኩት።
ችግር የለውም አልፏል በቃ አለኝ።
አሺ አልኩት።
ግን በድጋሜ ልንገርሽ በጣም ተናድጄብሽ ነበር አለኝ።
አረ በቃ እርሳው ጭቅጭቅ አስመሰልነውኮ ወሬያችንን አልኩት ነገሮችን ለማብረድ አስቤ።
ደስ የሚለው እሱም ቀለል አደረገውና በዛው አንድ አንድ እያልን ማውራት ጀመርን ።
ምንም ሳላጠና እራት ተጠርቼ ወጣሁ ወደክፍሌ እስክገባም ቸኩዬ ነበር ብቻ ካባቴጋ የተወሰነ ካወራን ቡሀላ ያልጨረስኩት ጥናት እንዳለኝ ነግሬው ቶሎ ወደክፍሌ ገባሁና ማውራት ጀመርን።
ምን እንዳወራን ሁላ አላውቅም ግን ዴቭ ሁላ ምነው እስካሁን እንዴት ቆየሽ ብሎ እስኪረመብኝ ድረስ እያወራን ነበር።
የሆነ ሰአት ላይ ከonline ወጥቶ ቆየ እኔም እንቅልፍ ወሰደኝ።
ጠዋት እንደተነሳሁ መጀመሪያ የሱን text ቼክ አደረኩኝ ምንም አላከልኝም።
ተነስቼ ወደክላሴ ሄድኩ አሁን ግን ስንገናኝ በአካል እናወራ ይሆን እንዴ ወይስ እንደሌላ ጊዜው ዝም ነው ምንባባለው እያልኩ ከራሴጋ እያወራሁ ነበር።
ክላስ ስገባ እሱ አልመጣም ገብቼ ቁጭ እንዳልኩ አስተማሪ ገባ ከኋላዋ ተከትሏት ስላረፈደ ይቅርታ ጠይቆ ገባ።
ቀኑን ሙሉ ምንም እንዳላወራ እንደማይተዋወቅ ሰው ሆነን ዋልን።
ቴሌግራም ላይ ግን ማውራታችንን ተያያዝነው ።
እስከሳምንቱ መጨረሻ ድረስ ክላስ ውስጥ ምንም እንደማይተዋወቅ ሰው እየሆንን እቤት እቤት ስንሆን ደሞ ከኛ በላይ ጓደኛ ያለ እስከማይመስለን እያወራን ቆየን።
እያሱ መልክና ጭንቅላት ብቻ ሳይሆን የሚገርም ፀባይም አለው ።
ስናወራ ይሄ እረጅም አመት አብሮ እንደቆየ እንደሚተዋወቅ ሰው ነበር ወሬያችን።
ከወሬያችን ውስጥ ግን ቀልቤን የሳበው አንድ ነገር ነበር።
እያወራን ሳናስበው ሰአቱ ይሄዳል አምስት ሰአት አካባቢ በቃ ደና ደሪ 11 ሰአት ስለምነሳ አሁን ቶሎ መተኛት አለብኝ ይለኛል።
ለምን ስለው??
እናቴን ማገዝ አለብኝ 11 ሰአት ተነስቼ እሷን በስራ አግዤ ነው ወደትምህርት ቤት የምመጣው ይለኛል።
እናትህ ስራዋ ምንድነው በሌሊት እንድትነሳ የሚያደርግህ ልለው አስብና አጉል ድፍረት መስሎኝ ዝም እላለሁ።
ብቻ ሳምንቱ አልቆ እሁድ ቀን ላይ ዴቭ እንደለመደው ቤት መጣና አብረን እንውጣ ምሳ ልጋብዝሽ አለኝ ።
አረ እኔ አልወጣም አባቴ ይገለኛል እንደዚህ ስትል ቢሰማህ እራሱ መባረርህ ነው አልኩት ማስጠንቀቂያ በሚመስል መልኩ።
አረ ኤልዱ አባትሽ እራሱ ነው ወጣ አድርጌ እንዳዝናናሽ የነገረኝ እንጂ በምን ድፍረት መጥቼ እጠይቅሻለሁ አለኝ።
ተአምር ሆነብኝ አባቴ ቤት ስላልነበር ደውዬ ጠየኩት።
አው የኔ ልጅ ወጣ ብለሽ ተዝናኚ እኔ ቤት ስለሌሁ እንዳይደብርሽ ብዬ ነው ፈቅጄልሻለሁ አለኝ።
እንዴት እንደተናደድኩ እኔና ፈጣሪ እናውቃለን ብቻ አልወጣም ሂድ አይባል ነገር ሆኖብኝ ልብሴን እንደነገር እንደነገሩ ለብሼ ወጣሁ እናቴ በጣም ደብሯት ነበር የሆነ ደስ ያላለኝ ነገር አለ ከዛሬ ጀምሮ አባትሽን አወራውና ከቤት መውጣት የለም የምን ቅዳሜን እሁድን እየጠበቁ መገባበዝ ነው አለችኝ ለብቻዬ ጠርታ..........
🔻ክፍል አምስት ነገ ማታ3️⃣🟰3️⃣0️⃣ ይቀጥላል... ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like💝 ማድረግ አይርሱ።
🔺🔺🔺🔺🔺😀😀😀😀😀
ይ 🀄️ላ🀄️ሉን! 😀
💔 @MELKAM_LBOCH13 💔
💔 @MELKAM_LBOCH13 💔
➖የዩቲዩ ገፃችን➖
https://www.youtu@Kezerareaction33' rel='nofollow'>be.com/@Kezerareaction333
@Kezerareaction33' rel='nofollow'>https://www.youtube.com/@Kezerareaction33
💗 ኤልዳና 💗
ልብ አንጠልጣይ የ ፍቅር ታሪክ በመልካም ልቦች የ ቴሌግራም ቻናል ተዘጋጅቶ የቀረበ💟
⭐️ክፍል 🟰4️⃣
ብቻ የዛን ቀን ውጤቱን ሲያይ አይሞቀው አይበርደው በቃ የጠበቀው ነገር እንዳገኘ ግልፅ ነው።
ማታ ቤት እንደገባሁ ግሩፓችን ውስጥ ገብቼ የሱን ስም ፈለኩና እራሴ ፃፍኩለት ለካ እንደዚህ ጎበዝ ነህ በቃ ታስጠናኛለህ አልኩት ለመቀለድ መሞከሬ ነበር በኔ ቤት።
አረ ባክሽ አስጠናሀለሁ ለማለት ፈልገሽ ነው አለኝ።
አንተኮ ነህ የበለጥከኝ ??
እኔ እንደበለጥኩሽ በምን አወቅሽ የኔን ውጤት ስትከታተይ ነበር ማለት ነው አለኝ።
አረ አደለም እንዲሁ ከፊት ለፊት ስለምትቀመጥ አጋጣሚ ነው እንጂ አልኩት።
እሺ አለኝ።
እሺ ሲለኝ እልህ ነገር ያዘኝ ይሁን ወይ እኔጃ ብቻ ግን ንዴት በሚመስል መልኩ ማውራት አልፈለክም እንዴ አልኩት።
ማውራት ባልፈልግኮ እንደባለፈው እንዳንቺ የተፃፃፍነውን አጠፋው ነበር አለኝ።
ኦኦ በሱ ተናደህ ነው እንዴ ይቅርታ በቃ አልኩት።
ችግር የለውም አልፏል በቃ አለኝ።
አሺ አልኩት።
ግን በድጋሜ ልንገርሽ በጣም ተናድጄብሽ ነበር አለኝ።
አረ በቃ እርሳው ጭቅጭቅ አስመሰልነውኮ ወሬያችንን አልኩት ነገሮችን ለማብረድ አስቤ።
ደስ የሚለው እሱም ቀለል አደረገውና በዛው አንድ አንድ እያልን ማውራት ጀመርን ።
ምንም ሳላጠና እራት ተጠርቼ ወጣሁ ወደክፍሌ እስክገባም ቸኩዬ ነበር ብቻ ካባቴጋ የተወሰነ ካወራን ቡሀላ ያልጨረስኩት ጥናት እንዳለኝ ነግሬው ቶሎ ወደክፍሌ ገባሁና ማውራት ጀመርን።
ምን እንዳወራን ሁላ አላውቅም ግን ዴቭ ሁላ ምነው እስካሁን እንዴት ቆየሽ ብሎ እስኪረመብኝ ድረስ እያወራን ነበር።
የሆነ ሰአት ላይ ከonline ወጥቶ ቆየ እኔም እንቅልፍ ወሰደኝ።
ጠዋት እንደተነሳሁ መጀመሪያ የሱን text ቼክ አደረኩኝ ምንም አላከልኝም።
ተነስቼ ወደክላሴ ሄድኩ አሁን ግን ስንገናኝ በአካል እናወራ ይሆን እንዴ ወይስ እንደሌላ ጊዜው ዝም ነው ምንባባለው እያልኩ ከራሴጋ እያወራሁ ነበር።
ክላስ ስገባ እሱ አልመጣም ገብቼ ቁጭ እንዳልኩ አስተማሪ ገባ ከኋላዋ ተከትሏት ስላረፈደ ይቅርታ ጠይቆ ገባ።
ቀኑን ሙሉ ምንም እንዳላወራ እንደማይተዋወቅ ሰው ሆነን ዋልን።
ቴሌግራም ላይ ግን ማውራታችንን ተያያዝነው ።
እስከሳምንቱ መጨረሻ ድረስ ክላስ ውስጥ ምንም እንደማይተዋወቅ ሰው እየሆንን እቤት እቤት ስንሆን ደሞ ከኛ በላይ ጓደኛ ያለ እስከማይመስለን እያወራን ቆየን።
እያሱ መልክና ጭንቅላት ብቻ ሳይሆን የሚገርም ፀባይም አለው ።
ስናወራ ይሄ እረጅም አመት አብሮ እንደቆየ እንደሚተዋወቅ ሰው ነበር ወሬያችን።
ከወሬያችን ውስጥ ግን ቀልቤን የሳበው አንድ ነገር ነበር።
እያወራን ሳናስበው ሰአቱ ይሄዳል አምስት ሰአት አካባቢ በቃ ደና ደሪ 11 ሰአት ስለምነሳ አሁን ቶሎ መተኛት አለብኝ ይለኛል።
ለምን ስለው??
እናቴን ማገዝ አለብኝ 11 ሰአት ተነስቼ እሷን በስራ አግዤ ነው ወደትምህርት ቤት የምመጣው ይለኛል።
እናትህ ስራዋ ምንድነው በሌሊት እንድትነሳ የሚያደርግህ ልለው አስብና አጉል ድፍረት መስሎኝ ዝም እላለሁ።
ብቻ ሳምንቱ አልቆ እሁድ ቀን ላይ ዴቭ እንደለመደው ቤት መጣና አብረን እንውጣ ምሳ ልጋብዝሽ አለኝ ።
አረ እኔ አልወጣም አባቴ ይገለኛል እንደዚህ ስትል ቢሰማህ እራሱ መባረርህ ነው አልኩት ማስጠንቀቂያ በሚመስል መልኩ።
አረ ኤልዱ አባትሽ እራሱ ነው ወጣ አድርጌ እንዳዝናናሽ የነገረኝ እንጂ በምን ድፍረት መጥቼ እጠይቅሻለሁ አለኝ።
ተአምር ሆነብኝ አባቴ ቤት ስላልነበር ደውዬ ጠየኩት።
አው የኔ ልጅ ወጣ ብለሽ ተዝናኚ እኔ ቤት ስለሌሁ እንዳይደብርሽ ብዬ ነው ፈቅጄልሻለሁ አለኝ።
እንዴት እንደተናደድኩ እኔና ፈጣሪ እናውቃለን ብቻ አልወጣም ሂድ አይባል ነገር ሆኖብኝ ልብሴን እንደነገር እንደነገሩ ለብሼ ወጣሁ እናቴ በጣም ደብሯት ነበር የሆነ ደስ ያላለኝ ነገር አለ ከዛሬ ጀምሮ አባትሽን አወራውና ከቤት መውጣት የለም የምን ቅዳሜን እሁድን እየጠበቁ መገባበዝ ነው አለችኝ ለብቻዬ ጠርታ..........
🔻ክፍል አምስት ነገ ማታ3️⃣🟰3️⃣0️⃣ ይቀጥላል... ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like💝 ማድረግ አይርሱ።
🔺🔺🔺🔺🔺😀😀😀😀😀
ይ 🀄️ላ🀄️ሉን! 😀
💔 @MELKAM_LBOCH13 💔
💔 @MELKAM_LBOCH13 💔
➖የዩቲዩ ገፃችን➖
https://www.youtu@Kezerareaction33' rel='nofollow'>be.com/@Kezerareaction333
@Kezerareaction33' rel='nofollow'>https://www.youtube.com/@Kezerareaction33