🔸🔸🔺🔺🔹🔸
ልብ አንጠልጣይ እውነተኛ ታሪክ ❤️
ፀሀፊ ✍️ ማኔ
ክፍል 2️⃣0️⃣
እኔም ተነስቼ እግሬ ወደመራኝ ተጓዝኩ ቁርስም
ስላልበላሁ ስራመድ አቅም እያነሰኝ ሲመጣ taxi ይዤ ወደናቴ መቃብርጋ ጉዞ ጀመርኩ ።
አጠገቤ የተቀመጠችው ልጅ እኔ ከጎና ስለተቀመጥኩ ክብሯን ያጣች ያህል እንደተሰማት ተመለከትኩ በአይኗ ገላምጣ ጨረሰችኝ መኪናው ትንሽ ሲንገጫገጭ ሰውነቴ ከሰውነቷ ሲነካካ እንዴት ፅይፍ እንዳለችኝ ተመለከትኩና ከtaxi ወረድኩላት ብቻዬን አይ ባህራን እውነት ግን እኔ እራሴ ነኝ መሞት በስንት ጣሙ ብዬ እያወራሁ በሌላ taxi ወደናቴጋ ሄድኩ። የእናቴ መቃብርጋ ቁጭ አልኩና አይ እማ እንደዛ ለማቀፍ ምትናፍቂው ልጅሽ ዛሬ ሰዎች ለመንካት ሚፀየፉት ሰው እንደሆነ ብታይ ግን ምን ይሰማሽ ይሆን አልኳት፡፡ ትንሽ ቁጭ ካልኩ ቡሀላ ልሄድ ስል ልእልት መጣች እንዳየችኝ አቀፈችኝ፡፡
ዝም ብዬ አየኋት።
የት ጠፍተህ ነው ግን ሌሊቱን ሙሉ ምን ሆኖ ይሆን ብዬ እያሰብኩ አይኔ እንደፈጠጠ ነው የነጋልኝ አየሁ አይኔ እንዴት እንዳበጠ አለችኝ፡፡
አሳዘነችኝ ። ግን ካፌ ምንም ቃል አላወጣሁም ዛሬ ቀኑን ሙሉ እዚህ ቁጭ ብዬ ልጠብቅህ ነበር የመጣሁት አለችኝ። ዝም ብዬ አይን አይኗን ነው ማያት ሁኔታዬ ግራ ገብቷት ምነው ባህራን ደና አደለህም እንዴ አለችኝ።
በድጋሜ መልሴ ዝምታ ብቻ ነበር።
ወደቤት ሄደን እንድናወራ ጠየቀችኝ እሺ አልኳት። ሰፈር ላይ ኮፍያህን አድርገህ ማንም ሳያይህ ግባ ከዛ ሳንኳኳ ቶሎ ክፈትልኝ የሰፈር ሰው እንዳያየን አለችኝ፡፡
እሺ ብዬ ቁልፉን ተቀብያት ወደውስጥ ገባሁ ብዙም ሳትቆይ አንኳኳች ከፍቼ ወደውስጥ አስገባኋት፡፡ ቤት ገብቼ ቁጭ አልኩ እጄን በደረት አድርጌ ጭብጥ ብዬ ቁጭ አልኩ የሆነ ሰው ቤት ለእንግድነት የሄድኩ እንጂ ተወልጄ ያደኩበት ቤት አልመስልህ አለኝ።
ልእልት ተሯሩጣ ገብታ ገዛዝታ በመጣችው ቆንጆ ቁርስ ሰራችና አብረን በላን እርቦኝ ስለነበር እንዴት እንደበላሁ እራሱ አላቅም ብቻ በልተን እንደጨረስን።
ልእልት ቡና አፈላችና ጠጣን ከሱ መልስ ቁጭ ብለን ማውራት አለብን አለችኝ ካጠገቤ መጥታ እየተቀመጠች፡፡ ዝም ብዬ ማዳመጥ ጀመርኩ።
ምን እንደተፈጠረ እዮብ ነግሮኛል ማወቅ ያለብህ እዮብ በዛን ሰአት ላንተ ባያስብ አንተን እንድትሄድ ትቶህ ወደቤቱ መመለስ ይችላልኮ አደል እሱ ላንተ ብሎ ነው አንዳንዴ መጋፈጥ ማትችለውን ነገር መጋፈጥ አደጋው የከፋ ነው አለችኝ።
ዝም አልኳት በቃ ዝም ማለት ነው የፈለኩት የማወጣው ቃላት እራሱ ጥቅሙ አልታይህ አለኝ።ልእልት ቀጥላ ደሞ አያርገውና ያቺ ሴት እቴቴ ብትሆን አሰብከው አንዳንዴ ሞት እረፍት የሚሆንበት አጋጣሚ አለኮ አለችኝ።
ያቺ ቃል ከጭንቅላቴ አልጠፋ አለች ሌላ ወሬ እያወራች ደጋግማ ምታቃጭልብኝ ቃል ግን ሞት እረፍት ሚሆንበት ያለቻት ቃላት ናት፡፡
አሰብኩት በዛች ሴትዮ ቦታ እማ ብትሆን ሚለውን ነገር አሰብኩና ሰውነቴን ነዘረኝ እንደዛ ከምትሆንማ እንኳን በሰላም አረፈች እኝኳኝ በክብር ተቀበረች አልኩኝ። ልእልት ብዙ ነገር ነግራኝ ስትጨርስ በቃ ገላህን ታጥበህ እረፍት አድርግ ትንሽ ተኛና ማወራህ ትልቅ ጉዳይ አለ አለችኝ፡፡
ተነስቼ ሻወር ቤት ገባሁና ገላዬን ታጠብቁ ከቁም ሳጥን ቱታዬን አውጥታ ሰጠችኝና ለባበስኩ ።ወደመኝታ ቤት ገብቼ አልጋዬ ላይ ቁጭ አልኩ ልእልት መጣችና ለባብሰህ ተኛ ሞቅ ሲልህ ቶሎ ነው እንቅልፍ ሚወስድህ ለጭንቅላትህም እረፍት ስጠው እንጂ ብላ አለባበሰችኝ እኔ ጋደም ስል እሷ ለመውጣት ተዘጋጀች ፡፡
እንዴት ካፌ እንዳመለጠኝ አላቅም ግን አንቺስ ሌሊቱን አልተኛሁም ብለሽ የለ ለምን አተኝም ነይ አብረን እንተኛ አልኳት። ፊቷ ፍክትክት እያለ እሺ ብላ ከጀርባዬ ጥቅልል ብላ ተኛች።አውነት ለመናገር ከዛ ክፍል ትታኝ ስትወጣ ቤቱ
ሚበላኝም መስሎኝ ነበር።
ጠዋት አካባቢ ተኝተን ከሰአት ነው የነቃነው ስነቃ ልእልት በሁለት እጄ ጥብቅ አድርጌ አቅፊያት እሷ ደሞ ደረቴ ውስጥ ገብታ ውሽቅ ብላ እጇን ከወገቤ ላይ ጣል አድርጋ የለበስኩትን ቲሸርት ጥብቅ አድርጋ ይዛው ነበር፡፡
በሰአቱ በጣም ደንግጫለሁ ሂጂ ከዚህ ተነሽ ብዬ ላባርራትም ፈልጊያለሁ ግን እንዴት እንደሆነ አላቅም ግን እንደዛ ሆኜ መቆየትም ፈልጌ ስለነበር አውቄ እንቅልፍ እንደወሰደው ሰው መልሼ አይኔን ጨፈንኩ
ግን መቆየት አልቻልኩም ምራቄን እራሱ ለመዋጥ አቃተኝ ደሞ ጠረኗ ደስ ይላል።
አስራ ምናምን ደቂቃዎችን ታገልኩና እጆቼን ከላይዋ ላይ አንስቼ ፊቴን ላዞር ስል በማርያም ትንሽ ደቂቃ ብቻ እቀፈኝ በእቴቴ ይዤሀለሁ አለችኝ።አልተኛሽም እንዴ አልኳት።ተኝቼ ነበር ግን ስነሳ እዚህ ሁኔታ ውስጥ እራሴን ሳገኘው መተኛትን መረጥኩ አለችኝ።ስለዚህ አንቺም እኔም እያስመሰልን ነበር አልኳት። አዎ ለደቂቃዎች ከራስጋ ስትታገል እያየሁ ነበር እኔ ደሞ አቅፈኸኝ ትንሽ ደቂቃ እንድትቆይ እየፀለይኩ ነበር አለችኝ።
ይሄን ዋጋ አለው እንዴ እኔ አንቺን ማቀፌ ብዬ ጠየኳት፡፡ ምናልባትም አንተ ከምታስበው በላይ ለኔ ዋጋ አለው እኔ ደሞ በተፈጥሮዬ መታቀፍን ምወድ ሰው ነው የሆነ ሰው ሲያቅፈኝ ሰላሜን እየሰጠኝ ይመስለኛል።
በምወደው ሰው መታቀፍ ደሞ ለኔ ህልም ነው አለችኝ፡፡ ዝም ብያት ተነሳሁና ቆምኩ ትገርማለህ በእቴቴ
ይዤሀለሁ እያልኩህ ለማንኛውም እሺ ብላ ፊቷን አዙራ ተኛች።
ስታኮርፍ በራሱ ሌላ ውበት አላት ከፊት ለፊቷ ቆምኩና እሺ ነይ ተነሽ አቅፌ ሳሎን ልውሰድሽ አልኳት ዘለለች መጥታ ተጠመጠመችብኝ ደረቴ ላይ እንደህፃን ልጅ ልጥፍ ብላ አንገቴ ስር ውሽቅ አለች። በሁኔታዋ ፈገግ እያልኩ ወደሳሎን አቅፌ ወሰድኳት ሶፋ ላይ ውረጂ ብላት አሎርድም አለች በእጇ አጥብቃ ከመያዟ የተነሳ አንገቴን ህመም ተሰምቶኝ ነበር።
አረ ደከመኝ ብዬ እንድትወርድልኝ አደረኩና እኔ ቁጭ ከልኩ። እሷ ወደስልኳ ሄደች በስማም ስንቴ እንደተደወለ መጣሁ ቆይ እናቴን ላውራት ብላ ወደውጭ ወጣች።
ብዙም ሳትቆይ እዮብን ይዛው ወደውስጥ ገባች፡፡ እንዳየኝ መጣና ሰላም አለኝ።
እኔ ፊቴን እንደጣልኩት ዝም ብዬ ቁጭ አልኩ ልእልት አውሩ በሉ እኔ ምግብ ልስራ አለችና ወደውስጥ ገባች፡፡
እዮብ ሁሉንም ነገር አስረዳኝ ገና ጎዳና ላይ ብዙ አመት ስትቆይ ምትለምደው ብዙ ነገር አለ።ፊት ለፊትህ ሰው ሲታረድ እያየህ ባላየ ልታልፍ ትችላለህ ምንም የማያውቁ ህፃናት የሰቆቃ ድምፃቸውን እያሰሙ እየለመኗቸው ያለምንም ርህራሄ ሚደፍሩ ብዙ የጎዳና ልጆች አሉ አለኝ፡፡ ትንሽ ተረጋጋሁ እዮብ መረጋጋቴን ሲመለከት ዞር ዞር እያለ ቤታችንን ማደናነቅ ጀመረ፡፡
ቀጠል አድርጎ ወደ ልእልትጋ ገባና አብረው እየተሳሳቁ ምግም መስራት ጀመሩ እኔ ላጨስ ወጣሁ ውጭ ላይ ቁጭ ብዬ ሳብ ሳብ አደረኩና ሲጋራውን ጣልኩት፡፡ ትንሽ ቆይታ ልእልት መጣችና አስደነገጥከኝኮ ና ምሳ ደርሷል አለችኝ ተከትያት ገባሁ ከምሳ ቡሀላ ልእልት ልታወራኝ ምትፈልገው ጉዳይ እንዳለ ነገረችኝ።
ምን እንደሆነ ጠየኳት።
ምን እንደሆነ ጠየኳት። አሁን የእቴቴ ሙት አመት እየደረሰ ነው እና ዘመዶቻችሁ እሱ እየደገሱላት ነው።
ልክ ሙት አመት ፕሮግራሙ እንዳለፈ ግን ይዠየዚህን ቤት ጉዳይ ወደፍርድ ቤት ሊወስዱት አስበዋል። አንተ ቤት ውስጥ ስለማትኖርና አልፈልግም ብለህ ሀገር ጥለኽ ስለጠፋህ ቤቱ ተዘግቶ ከሚኖር እነሱ ቢጠቀሙበት እንደሚሻል አውርተው ጨርሰዋል።
❤️ የፍቅር ጥግ ❤️
ልብ አንጠልጣይ እውነተኛ ታሪክ ❤️
ፀሀፊ ✍️ ማኔ
ክፍል 2️⃣0️⃣
እኔም ተነስቼ እግሬ ወደመራኝ ተጓዝኩ ቁርስም
ስላልበላሁ ስራመድ አቅም እያነሰኝ ሲመጣ taxi ይዤ ወደናቴ መቃብርጋ ጉዞ ጀመርኩ ።
አጠገቤ የተቀመጠችው ልጅ እኔ ከጎና ስለተቀመጥኩ ክብሯን ያጣች ያህል እንደተሰማት ተመለከትኩ በአይኗ ገላምጣ ጨረሰችኝ መኪናው ትንሽ ሲንገጫገጭ ሰውነቴ ከሰውነቷ ሲነካካ እንዴት ፅይፍ እንዳለችኝ ተመለከትኩና ከtaxi ወረድኩላት ብቻዬን አይ ባህራን እውነት ግን እኔ እራሴ ነኝ መሞት በስንት ጣሙ ብዬ እያወራሁ በሌላ taxi ወደናቴጋ ሄድኩ። የእናቴ መቃብርጋ ቁጭ አልኩና አይ እማ እንደዛ ለማቀፍ ምትናፍቂው ልጅሽ ዛሬ ሰዎች ለመንካት ሚፀየፉት ሰው እንደሆነ ብታይ ግን ምን ይሰማሽ ይሆን አልኳት፡፡ ትንሽ ቁጭ ካልኩ ቡሀላ ልሄድ ስል ልእልት መጣች እንዳየችኝ አቀፈችኝ፡፡
ዝም ብዬ አየኋት።
የት ጠፍተህ ነው ግን ሌሊቱን ሙሉ ምን ሆኖ ይሆን ብዬ እያሰብኩ አይኔ እንደፈጠጠ ነው የነጋልኝ አየሁ አይኔ እንዴት እንዳበጠ አለችኝ፡፡
አሳዘነችኝ ። ግን ካፌ ምንም ቃል አላወጣሁም ዛሬ ቀኑን ሙሉ እዚህ ቁጭ ብዬ ልጠብቅህ ነበር የመጣሁት አለችኝ። ዝም ብዬ አይን አይኗን ነው ማያት ሁኔታዬ ግራ ገብቷት ምነው ባህራን ደና አደለህም እንዴ አለችኝ።
በድጋሜ መልሴ ዝምታ ብቻ ነበር።
ወደቤት ሄደን እንድናወራ ጠየቀችኝ እሺ አልኳት። ሰፈር ላይ ኮፍያህን አድርገህ ማንም ሳያይህ ግባ ከዛ ሳንኳኳ ቶሎ ክፈትልኝ የሰፈር ሰው እንዳያየን አለችኝ፡፡
እሺ ብዬ ቁልፉን ተቀብያት ወደውስጥ ገባሁ ብዙም ሳትቆይ አንኳኳች ከፍቼ ወደውስጥ አስገባኋት፡፡ ቤት ገብቼ ቁጭ አልኩ እጄን በደረት አድርጌ ጭብጥ ብዬ ቁጭ አልኩ የሆነ ሰው ቤት ለእንግድነት የሄድኩ እንጂ ተወልጄ ያደኩበት ቤት አልመስልህ አለኝ።
ልእልት ተሯሩጣ ገብታ ገዛዝታ በመጣችው ቆንጆ ቁርስ ሰራችና አብረን በላን እርቦኝ ስለነበር እንዴት እንደበላሁ እራሱ አላቅም ብቻ በልተን እንደጨረስን።
ልእልት ቡና አፈላችና ጠጣን ከሱ መልስ ቁጭ ብለን ማውራት አለብን አለችኝ ካጠገቤ መጥታ እየተቀመጠች፡፡ ዝም ብዬ ማዳመጥ ጀመርኩ።
ምን እንደተፈጠረ እዮብ ነግሮኛል ማወቅ ያለብህ እዮብ በዛን ሰአት ላንተ ባያስብ አንተን እንድትሄድ ትቶህ ወደቤቱ መመለስ ይችላልኮ አደል እሱ ላንተ ብሎ ነው አንዳንዴ መጋፈጥ ማትችለውን ነገር መጋፈጥ አደጋው የከፋ ነው አለችኝ።
ዝም አልኳት በቃ ዝም ማለት ነው የፈለኩት የማወጣው ቃላት እራሱ ጥቅሙ አልታይህ አለኝ።ልእልት ቀጥላ ደሞ አያርገውና ያቺ ሴት እቴቴ ብትሆን አሰብከው አንዳንዴ ሞት እረፍት የሚሆንበት አጋጣሚ አለኮ አለችኝ።
ያቺ ቃል ከጭንቅላቴ አልጠፋ አለች ሌላ ወሬ እያወራች ደጋግማ ምታቃጭልብኝ ቃል ግን ሞት እረፍት ሚሆንበት ያለቻት ቃላት ናት፡፡
አሰብኩት በዛች ሴትዮ ቦታ እማ ብትሆን ሚለውን ነገር አሰብኩና ሰውነቴን ነዘረኝ እንደዛ ከምትሆንማ እንኳን በሰላም አረፈች እኝኳኝ በክብር ተቀበረች አልኩኝ። ልእልት ብዙ ነገር ነግራኝ ስትጨርስ በቃ ገላህን ታጥበህ እረፍት አድርግ ትንሽ ተኛና ማወራህ ትልቅ ጉዳይ አለ አለችኝ፡፡
ተነስቼ ሻወር ቤት ገባሁና ገላዬን ታጠብቁ ከቁም ሳጥን ቱታዬን አውጥታ ሰጠችኝና ለባበስኩ ።ወደመኝታ ቤት ገብቼ አልጋዬ ላይ ቁጭ አልኩ ልእልት መጣችና ለባብሰህ ተኛ ሞቅ ሲልህ ቶሎ ነው እንቅልፍ ሚወስድህ ለጭንቅላትህም እረፍት ስጠው እንጂ ብላ አለባበሰችኝ እኔ ጋደም ስል እሷ ለመውጣት ተዘጋጀች ፡፡
እንዴት ካፌ እንዳመለጠኝ አላቅም ግን አንቺስ ሌሊቱን አልተኛሁም ብለሽ የለ ለምን አተኝም ነይ አብረን እንተኛ አልኳት። ፊቷ ፍክትክት እያለ እሺ ብላ ከጀርባዬ ጥቅልል ብላ ተኛች።አውነት ለመናገር ከዛ ክፍል ትታኝ ስትወጣ ቤቱ
ሚበላኝም መስሎኝ ነበር።
ጠዋት አካባቢ ተኝተን ከሰአት ነው የነቃነው ስነቃ ልእልት በሁለት እጄ ጥብቅ አድርጌ አቅፊያት እሷ ደሞ ደረቴ ውስጥ ገብታ ውሽቅ ብላ እጇን ከወገቤ ላይ ጣል አድርጋ የለበስኩትን ቲሸርት ጥብቅ አድርጋ ይዛው ነበር፡፡
በሰአቱ በጣም ደንግጫለሁ ሂጂ ከዚህ ተነሽ ብዬ ላባርራትም ፈልጊያለሁ ግን እንዴት እንደሆነ አላቅም ግን እንደዛ ሆኜ መቆየትም ፈልጌ ስለነበር አውቄ እንቅልፍ እንደወሰደው ሰው መልሼ አይኔን ጨፈንኩ
ግን መቆየት አልቻልኩም ምራቄን እራሱ ለመዋጥ አቃተኝ ደሞ ጠረኗ ደስ ይላል።
አስራ ምናምን ደቂቃዎችን ታገልኩና እጆቼን ከላይዋ ላይ አንስቼ ፊቴን ላዞር ስል በማርያም ትንሽ ደቂቃ ብቻ እቀፈኝ በእቴቴ ይዤሀለሁ አለችኝ።አልተኛሽም እንዴ አልኳት።ተኝቼ ነበር ግን ስነሳ እዚህ ሁኔታ ውስጥ እራሴን ሳገኘው መተኛትን መረጥኩ አለችኝ።ስለዚህ አንቺም እኔም እያስመሰልን ነበር አልኳት። አዎ ለደቂቃዎች ከራስጋ ስትታገል እያየሁ ነበር እኔ ደሞ አቅፈኸኝ ትንሽ ደቂቃ እንድትቆይ እየፀለይኩ ነበር አለችኝ።
ይሄን ዋጋ አለው እንዴ እኔ አንቺን ማቀፌ ብዬ ጠየኳት፡፡ ምናልባትም አንተ ከምታስበው በላይ ለኔ ዋጋ አለው እኔ ደሞ በተፈጥሮዬ መታቀፍን ምወድ ሰው ነው የሆነ ሰው ሲያቅፈኝ ሰላሜን እየሰጠኝ ይመስለኛል።
በምወደው ሰው መታቀፍ ደሞ ለኔ ህልም ነው አለችኝ፡፡ ዝም ብያት ተነሳሁና ቆምኩ ትገርማለህ በእቴቴ
ይዤሀለሁ እያልኩህ ለማንኛውም እሺ ብላ ፊቷን አዙራ ተኛች።
ስታኮርፍ በራሱ ሌላ ውበት አላት ከፊት ለፊቷ ቆምኩና እሺ ነይ ተነሽ አቅፌ ሳሎን ልውሰድሽ አልኳት ዘለለች መጥታ ተጠመጠመችብኝ ደረቴ ላይ እንደህፃን ልጅ ልጥፍ ብላ አንገቴ ስር ውሽቅ አለች። በሁኔታዋ ፈገግ እያልኩ ወደሳሎን አቅፌ ወሰድኳት ሶፋ ላይ ውረጂ ብላት አሎርድም አለች በእጇ አጥብቃ ከመያዟ የተነሳ አንገቴን ህመም ተሰምቶኝ ነበር።
አረ ደከመኝ ብዬ እንድትወርድልኝ አደረኩና እኔ ቁጭ ከልኩ። እሷ ወደስልኳ ሄደች በስማም ስንቴ እንደተደወለ መጣሁ ቆይ እናቴን ላውራት ብላ ወደውጭ ወጣች።
ብዙም ሳትቆይ እዮብን ይዛው ወደውስጥ ገባች፡፡ እንዳየኝ መጣና ሰላም አለኝ።
እኔ ፊቴን እንደጣልኩት ዝም ብዬ ቁጭ አልኩ ልእልት አውሩ በሉ እኔ ምግብ ልስራ አለችና ወደውስጥ ገባች፡፡
እዮብ ሁሉንም ነገር አስረዳኝ ገና ጎዳና ላይ ብዙ አመት ስትቆይ ምትለምደው ብዙ ነገር አለ።ፊት ለፊትህ ሰው ሲታረድ እያየህ ባላየ ልታልፍ ትችላለህ ምንም የማያውቁ ህፃናት የሰቆቃ ድምፃቸውን እያሰሙ እየለመኗቸው ያለምንም ርህራሄ ሚደፍሩ ብዙ የጎዳና ልጆች አሉ አለኝ፡፡ ትንሽ ተረጋጋሁ እዮብ መረጋጋቴን ሲመለከት ዞር ዞር እያለ ቤታችንን ማደናነቅ ጀመረ፡፡
ቀጠል አድርጎ ወደ ልእልትጋ ገባና አብረው እየተሳሳቁ ምግም መስራት ጀመሩ እኔ ላጨስ ወጣሁ ውጭ ላይ ቁጭ ብዬ ሳብ ሳብ አደረኩና ሲጋራውን ጣልኩት፡፡ ትንሽ ቆይታ ልእልት መጣችና አስደነገጥከኝኮ ና ምሳ ደርሷል አለችኝ ተከትያት ገባሁ ከምሳ ቡሀላ ልእልት ልታወራኝ ምትፈልገው ጉዳይ እንዳለ ነገረችኝ።
ምን እንደሆነ ጠየኳት።
ምን እንደሆነ ጠየኳት። አሁን የእቴቴ ሙት አመት እየደረሰ ነው እና ዘመዶቻችሁ እሱ እየደገሱላት ነው።
ልክ ሙት አመት ፕሮግራሙ እንዳለፈ ግን ይዠየዚህን ቤት ጉዳይ ወደፍርድ ቤት ሊወስዱት አስበዋል። አንተ ቤት ውስጥ ስለማትኖርና አልፈልግም ብለህ ሀገር ጥለኽ ስለጠፋህ ቤቱ ተዘግቶ ከሚኖር እነሱ ቢጠቀሙበት እንደሚሻል አውርተው ጨርሰዋል።