ክፍል ፮ሰላም ውድ የ
አሐቲ ቤተክርስቲያን ቻናል ቤተሰቦቻችን ! ዛሬ ደግሞ በቤተክርስቲያን ውስጥ የሚገኙትን ንዋያተ ቅድሳት፣ የአቀማመጣቸውንና የአጠቃቀማቸውን ሥርዓት እንመለከታለን ::
በቤተክርስቲያን ውስጥ የሚገኙትን ንዋያተ ቅድሳት፣ የአቀማመጣቸውንና የአጠቃቀማቸውን ሥርዓት እንመለከታለን። ንዋያተ ቅድሳት በቤተክርስቲያን ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጣቸው ሲሆን፣ እያንዳንዱም የራሱ የሆነ ምሳሌያዊ ትርጉም አለው።
ታቦት ወይም ጽላት • ታቦት ከብሉይ ኪዳንና ከእስራኤል የነፃነት ሕይወት ጋር የተያያዘ ታሪክ አለው። የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ማደሪያ፣ መገለጫ ነው።
• ጽላት እግዚአብሔር ለሙሴ አስቀድሞ በአሥርቱ ትዕዛዛት የጻፋቸው ቃላት የሚገኙበት ነው። (ዘጸ 31:18)
• በሐዲስ ኪዳን ጽላትም ታቦትም የሚባለው ያው አንዱ መሥዋዕት ነው።
• ጽላት የሚከተሉት ባህሪያት አሉት ፦
* ከቦታ ወደ ቦታ ለማዛወር እንዲቻል ተደርጎ ይሠራል።
* በፊቱ "አልፋ ወ ኦሜጋ" የሚል ጽሑፍ ይጻፋል።
* ከላይ ሥዕለ ሥላሴ፣ ቀጥሎ ምስለ ፍቁር ወልዳ ፣ ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእ እንዲሁም መቅደሱ የተሠራለት ጻድቅ ሆነ ሰማዕት መልአክም ሆነ ሐዋርያ ስዕሉ ይቀረፃል ከዛም ስም ይጻፋል።
• ይህ ከተጻፈ በኋላ በኤጲስ ቆጶስ ተባርኮና ሜሮን ተቀብቶ በበሩ ይቀመጣል። ጽላተ ኪዳን ማኅደረ እግዚአብሔር ነው፤ ያለ ታቦትም መሥዋዕት አይሠዋም።
መስቀል • መስቀል የክርስትና ምልክት ነው።
• ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስዋዕት የሆነበት ነው።
• የክርስቶስ ደም የፈሰሰበት ነው።
• የድኅነት ኃይላችን መገለጫ ነው።
• መስቀል ሰውና እግዚአብሔር የታረቁበት ታላቅ አደባባይ ነው።
• መስቀል የቤተክርስቲያን ምሥጢራትን ለመፈጸም ትልቅ ቦታ አለው።
የመስቀል ዓይነቶች •
ሀ. የመፆር መስቀል፦ በቅዳሴ ጊዜ በማዕጠንት ጊዜ ሠራዒ ዲያቆን የሚይዘው ነው።
•
ለ. የእጅ መስቀል፦ ሊቃነ ጳጳሳት፣ ኤጲስ ቆጶሳትና ካህናት የሚይዙት ምእመናንን የሚባርኩበት ነው።
•
ሐ. የአንገት መስቀል፦ ምእመናን ከአንገታቸው አስረው ጌታችንን የሚገልጹበት ነው።
•
መ. የዕርፈ መስቀል፦ ካህናት ለምእመናን የሚሰጡት ነው።
• ከእንጨት፣ ከብር፣ ከዳብ፣ ከብረትና ከወርቅ ይሠራሉ። እያንዳንዱም የየራሱ ምሳሌያዊ ትርጉም አለው።
*
የእንጨት መስቀል - ጌታችን ዕፀ መስቀልን ለመሸከሙ ምሳሌ ነው።
*
የብረት መስቀል - በብረት (አምስት ቅንዋት) የተወጋበትን ያመለክታል።
*
የብር መስቀል - ይሁዳ ሠላሳ ብር አሳልፎ እንደሰጠው ያሳያል።
*
የወርቅ መስቀል - ንጹሐ ባሕርይ አምላክ መሆኑን ያሳያል።
*
የመዳብ መስቀል - መዳብ ቀይ በመሆኑ የጌታችንን ደም ያመለክታል።
መንበረ ታቦት • መንበር የታቦት መቀመጫ ነው።
• በኦሪት የነበረውን መሰዊያ የሚተካ ነው።
• ከታቦቱ ጋር መሥዋዕት የሚቀርብበት ቦታ ነው።
ፃሕል • ቅዱስ ሥጋው የሚቀመጥበት ዕቃ ነው።
• ከወርቅ፣ ከብር ወይም ከናስ ይሠራል።
• የክርስቶስ መወለድና መቃብሩ ምሳሌ ነው።
ጽዋዕ • የክርስቶስ ክቡር ደም የሚቀርብበት ንዋየ ቅዱስ ነው።
• ከወርቅ፣ ከብር፣ ከዳብ፣ ከናስ ወይም ከብረት ይሠራል።
• ጌታችን "ይህ ደሜ ነው" ብሎ የሰጠበትን ጽዋ ያስታውሳል።
ዕርፈ መስቀል • ይህም የጌታችንን ክቡር ደም ለማቀበል የሚያገለግል ንዋየ ቅዱስ ነው።
• የሱራፌል ክንፍ ምሳሌ አለው።
• የመለኮት እሳታዊ ኃይልን ይይዛል።
0ውድ• በድርገት ጊዜ ጻህል የሚቀመጡበት ሰፋ ያለ ጻህል ነው። ሥጋው እንዳይነጥብ(እንዳይወድቅ) ሰፋ ጎላ እንዲሁም ከበር ብሎ እንዲታይ ለማለት የተደረገ ነው
• ከብረት፣ ከነሐስ ወይም ከእንጨት ይሠራል።
• ጌታችን የተፈረደበት የጲላጦስ አደባባይ ምሳሌ ነው።
አጎበሮ • በረድ ላይ የሚደፋ አራት ማዕዘን ቅርጽ ያለው ትንሽዬ ብረት ወይም እንጨት ነው።
• ሥጋ ወደ ደሙ በሚለወጥበት ጊዜ ስቡ እንዳይነካው ከፍ አድርጎ የሚይዝ ነው።
ጽንሐሕ • የዕጣን ማሳረጊያ ነው።
• ከወርቅ፣ ከብር ወይም ከብረት ይሰራል።
• የእመቤታችን የድንግል ማርያም ምሳሌ ነው።
መሶበ ወርቅ፦
• ኅብስትና ወይን የሚቀርብበት ነው።
• ከወርቅ፣ ከብርና ከሌሎች ማዕድናት የሚሠራ ነው።
• የድንግል ማርያም ምሳሌ ነው።
አልባሳት (የካህናትና የዲያቆናት ልብሶች)፦
የቀሳውስት ልብስ * ቀሚስ
* ካባ ላንቃ
* ሞጣይት
* ቆብ ወይም ቀፀላ
የዲያቆናት ልብስ * ለምድ ላንቃ
* ቀሚስ
* እጀ ጠባብ ወይም ሶባ
* አክሊል ወይም ቆብ
ማኅፈዳት፦
• አምስት መሸፈኛዎች ናቸው። አብዛኛውን ጊዜ ከጥጥ ወይም ከሐር ይሠራሉ።
* አንደኛው በጽላት ላይ ይነጠፋል።
* ሁለተኛው በጸሐሉ ላይ ይነጠፋል።
* ሦስተኛው የመሥዋዕቱ ልብስ ሆኖ ከሰሜን ወደ ደቡብ ይሰበሰባል።
* አራተኛው ከመሥዋዕቱ በስተ ምዕራብ ይሰበሰባል።
* አምስተኛው ከሰሜን ምዕራብ፣ ከምሥራቃዊ ወገን ወደ ደቡባዊ ምዕራብ ይሰበሰባል።
• ክርስቶስ በግርግም ሲተኛ በጨርቅ መጠቅለሉን የሚያስታውስ ነው።
መጋረጃዎች • በመቅደስ በር ላይ የሚታጠቁ መጋረጃዎች ናቸው።
• ለመቅደሱ ክብርን ይሰጣሉ። የሚከፈቱበትና የሚዘጉበት ጊዜ አለው።
ታቦት መጎናጸፊያ • ይህ ታቦቱ በክብር የሚለብሰው ልብስ ነው።
• በቅዳሴ ጊዜና በዓላት ላይ ታቦቱን ያጌጣል።
የማሕሌት መገልገያ መሣሪያዎች * መቋሚያ
* ከበሮ
* ጓናጽል
ማጠቃለያ:
ንዋያተ ቅድሳት በቤተክርስቲያን ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጣቸው ሲሆን፣ እያንዳንዱም የራሱ የሆነ ምሳሌያዊ ትርጉም አለው። እነዚህን ንዋያተ ቅድሳት በአግባቡ መጠቀምና መንከባከብ የሁላችንም ኃላፊነት ነው።
ይህን መልዕክት ለሌሎችም በማጋራት ያወቅንውን እንድናሳውቅና ና በረከትን እንድናገኝ እንጋብዛችኋለን እንዲሁም ማንኛውም አይነት ጥያቄ ካላችሁ ግሩፑ ላይ አሳውቁን እንመልሳለን
በቀጣይ ወደ ቤተ መቅደስ በጸሎት ለመቅረብ እንዴት መዘጋጀት ይቻላል?.....
|| @AHATI_BETKERSTYAN