ክፍል ፭
ሰላም ውድ የ አሐቲ ቤተክርስቲያን ቻናል ቤተሰቦቻችን ! ዛሬ ደግሞ የቤተ ክርስቲያን አተካከልና አሠራር እንመለከታለን።
ቤተ ክርስቲያን ስንል ሕንፃ ቤተ ክርስቲያንን ጨምሮ ብዙ ትርጓሜዎች እንዳሉት ይታወቃል። በዚህ ጽሑፍ ላይ፣ የቤተ ክርስቲያን ሕንፃ አሠራርንና ሥርዓትን እንመለከታለን። እግዚአብሔር በሁሉም ቦታ ቢኖርም፣ እኛ ውሱን ፍጥረታት በሆነ ቦታ ላይ ተሰብስበን እንድናመልከው አዟል። ይህ ቦታ ለእኛ መሰባሰቢያ ብቻ ሳይሆን እርሱም ከእኛ እንደማይለይ ማረጋገጫ ነው።
፩ . በብሉይ ኪዳን የነበረው ቤተ መቅደስ
እግዚአብሔር እስራኤላውያን በመካከላቸው እንዲኖር መቅደስ እንዲሠሩ አዟቸዋል (ዘጸ 25፥8)። ሰዎችም ምሕረት፣ ይቅርታና በረከት ለማግኘት ወደዚህ ቦታ ይሄዱ ነበር (ዘጸ 33፥7)። ስለዚህም ቤቱ "ቤተ እግዚአብሔር" ተባለ (2 ዜና 36፥18)።
• ደብተራ ኦሪት (ድንኳን):
• ይህ የመጀመሪያው የአምልኮ ቦታ ሲሆን በሲና ተራራ ላይ ለሙሴ ተገልጦለታል።
• ለአምልኮ አገልግሎት የሚውሉ ሁለት ክፍሎች ነበሩት፦ ቅድስተ ቅዱሳን እና ቅድስት።
• እግዚአብሔር ለሙሴ "እንደማሳይህ ሁሉ እንደ ማደሪያው ምሳሌ እንዲሁ ሥሩት" (ዘጸ 25፥9) ብሎታል። ይህም የቤተ መቅደስ ሥራ ያለ ሥርዓት እንደማይሠራ ያሳያል።
. መቅደሰ ሰሎሞን:
• ንጉሥ ሰሎሞን የሠራው ቤተ መቅደስ ሦስት ክፍሎች ነበሩት፦ ኤላም (ዙሪያ)፣ ሃይከል (አዳራሽ) እና ዳቤር (ቅድስተ ቅዱሳን)።
• እነዚህ ቦታዎች ለአዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያን መሠረት ናቸው።
፪. በሐዲስ ኪዳን የነበረው ቤተ ክርስቲያን
የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች የራሳቸው የጸሎት ቤት በተወሰነ ቦታ አላደረጉም የተለያየም ሕንፃ አልሰሩም ነበር፡፡ ነገር ግን ወደ አይሁድ ቤተ መቅደስ በመሄድ ከአይሁድ ጋር የጸልዩ ነበር፡፡
• እንዲሁም በግል የክርስቲያን ቤቶች እየተገኙ በተለያዩ ክፍሎች እየተሰበሰቡ ይጸልዩ ፣ማእድንም ይባርኩ ፣ቅዱስ ቁርባንም ያዘጋጁ ነበር፡፡ ይህን የመሳሰሉትንአገልግሎቶች ይፈጽሙባቸው የነበሩትን ምኩራቦች የጸሎት መሰብሰቢያዎች እያሉ ይጠሩአቸው ነበር፡፡
• እየዋለ እያደረ ግን አማኒው እየበዛ ስለሄደ በእነዚህ ጠባብ ክፍልና ጠባብም ግቢ አምልኮት እግዚአብሔርን ለመፈጸም አልተቻለም፡፡ ስለዚህ ክርስቲያኖች ታላላቅ ሕንፃዎችን እያሳነፁ ቤተክርስቲያን መሥራት በዚያም መሰብሰብ አምልኮተ እግዚአብሔርንም መፈጸም ጀመሩ፡፡
• በአፍሪካ የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን በ60 ዓ.ም በእስክንድሪያ የተመሠረተችው በሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ ነው።
• ይህችም ቤተክተርስቲያን ሐዋርያት ለስብከተ ወንጌል ወደዓለም ከተሰማሩ በኋላ ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ በእስክንድሪያ በጰራቅሊጦስ ስም አሠረቶ ሰኔ 5 ቀን በ61ዓ.ም የቅዳሴ ቤተክርስቲያን በዓል አክብሯል።
• በቤተ ክርስቲያን ዙሪያ የሚሠሩ ቤቶች
ቤተ ክርስቲያን ሲሠራ አንድ ሕንፃ ብቻ ሳይሆን ከቤተ ክርስቲያኑ ጋር አብረው አገልግሎት የሚሰጡ ቤቶችም ያስፈልጋሉ። እነዚህ ቤቶች በሁለት ይከፈላሉ፦
• ግድ ከቤተ ክርስቲያኑ ሳይለዩ አብረው የሚሠሩ አስፈላጊ ቤቶች
• እንደ ቤተ ክርስቲያኑ አቅም ሊሠሩ የሚገባቸው ቤቶች
. የግድ ከቤተ ክርስቲያኑ ሳይለዩ አብረው የሚሠሩ አስፈላጊ ቤቶች የሚከተሉት ናቸው
ቤተልሔም
• በቤተ ክርስቲያኑ በምሥራቅ በኩል የሚሠራ ቤት ነው።
• ዲያቆናቱ ለመሥዋዕት የሚሆነውን ኅብስትና ወይን የሚያዘጋጁበት ነው።
• ስያሜው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደበት በቤተ ልሔም ዘይሁዳ ምሳሌ ነው።
• ምሥጢሩ ዲያቆናት ሕብስቱን በቤተልሔም አዘጋጅተው ወደ ቤተ ክርስቲያን መሥዋዕት መምጣታቸው በቤተልሔም የተወለደው በጎልጎታ ለመሥዋዕት የቀረበው ክርስቶስ ይህ ነው ለማለት ነው። መቅደስ የጎልጎታ ምሳሌ ነው።
የግብር ቤት
• ለመሥዋዕት የሚሆነው ስንዴ የሚሰየምበት/የሚደቅቅበት/የሚፈጭበት በቤተ ክርስቲያኑ ቅጽረ ግቢ የሚሠራ ቤት ነው።
• ስንዴው መገበሪያ ተብሏል፤ መፍጨቱ ደግሞ መሰየም ይባላል። ይህም የመሥዋዕቱ አቀራረብ ቋንቋ ነው።
ዕቃ ቤት
• የቤተ ክርስቲያን ንዋየ ቅድሳት የሚቀመጥበት ቤት ነው።
• የቤተ ክርስቲያኑ መገልገያ የሆኑት አልባሳት፣ መጻሕፍት የሚጠበቁት በዚህ ቤት ነው። (ሕዝ 44፥19፤ ፍት. መን. 12)
የማጥመቂያ ቤት/ክርስትና ቤት
• ሥርዓተ ጥምቀት የሚፈጸምበት ቤት ነው።
• ወንዶች በአርባ ቀን ሴቶች በሰማንያ ቀን ከሥላሴ ልጅነት የሚያገኙት በዚህ ሥርዓት ነው።
ደጀ ሰላም
• ከቤተ ክርስቲያኑ በስተምዕራብ በኩል የሚሠራ ቤት ነው።
• በቤተ ክርስቲያኑ ቅጽር ውስጥ የሚሠራ ሲሆን እንደ አካባቢው አገልግሎቱ ሊለያይ ይችላል።
• ለጸሎተ ፍትሐት፣ ለካህናት ማረፊያ፣ ለእንግዳ መቀበያ ወዘተ አገልግሎቶች ማስፈጸሚያ ሊውል ይችላል።
እንደ ቤተ ክርስቲያኑ አቅም ሊሠሩ የሚገባቸው ቤቶች ፦
• ሀ/ የሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት
• ለ/ የሰ/ት/ቤቶች ክፍሎች
• ሐ/ የምእመናን መማሪያ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ
• መ/ የእንግዶች/የካህናት ማረፊያ ቤቶች
• ሠ/ የመንፈሳዊ ት/ቤትና የተግባረ እድ መማሪያ ክፍሎች
• ረ/ ቤተ መጽሐፍት
• ሰ/ የመገልገያ ዕቃዎችና ጧፍ፣ ዕጣን ሽያጭ ክፍሎች
ማጠቃለያ:
ቤተ ክርስቲያን ስንል የአንድ ሕንፃ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፣ አብረውት የሚቆሙና የሚያገለግሉ ቤቶችም ጭምር ነው። እነዚህ ቤቶች የየራሳቸው አገልግሎት ያላቸው ሲሆን፣ ለቤተ ክርስቲያኒቱ እድገትና ምእመናን መንፈሳዊ ሕይወት ወሳኝ ናቸው።
ይህን መልዕክት ለሌሎችም በማጋራት ያወቅንውን እንድናሳውቅና ና በረከትን እንድናገኝ እንጋብዛችኋለን እንዲሁም ማንኛውም አይነት ጥያቄ ካላችሁ ግሩፑ ላይ አሳውቁን እንመልሳለን
በቀጣይ በቤተክርስቲያን ውስጥ ሊኖሩ የሚገቡ ንዋያተ ቅድሳትና የአቀማመጥና የአጠቃቀም ሥርዓት....
|| @AHATI_BETKERSTYAN
ሰላም ውድ የ አሐቲ ቤተክርስቲያን ቻናል ቤተሰቦቻችን ! ዛሬ ደግሞ የቤተ ክርስቲያን አተካከልና አሠራር እንመለከታለን።
ቤተ ክርስቲያን ስንል ሕንፃ ቤተ ክርስቲያንን ጨምሮ ብዙ ትርጓሜዎች እንዳሉት ይታወቃል። በዚህ ጽሑፍ ላይ፣ የቤተ ክርስቲያን ሕንፃ አሠራርንና ሥርዓትን እንመለከታለን። እግዚአብሔር በሁሉም ቦታ ቢኖርም፣ እኛ ውሱን ፍጥረታት በሆነ ቦታ ላይ ተሰብስበን እንድናመልከው አዟል። ይህ ቦታ ለእኛ መሰባሰቢያ ብቻ ሳይሆን እርሱም ከእኛ እንደማይለይ ማረጋገጫ ነው።
፩ . በብሉይ ኪዳን የነበረው ቤተ መቅደስ
እግዚአብሔር እስራኤላውያን በመካከላቸው እንዲኖር መቅደስ እንዲሠሩ አዟቸዋል (ዘጸ 25፥8)። ሰዎችም ምሕረት፣ ይቅርታና በረከት ለማግኘት ወደዚህ ቦታ ይሄዱ ነበር (ዘጸ 33፥7)። ስለዚህም ቤቱ "ቤተ እግዚአብሔር" ተባለ (2 ዜና 36፥18)።
• ደብተራ ኦሪት (ድንኳን):
• ይህ የመጀመሪያው የአምልኮ ቦታ ሲሆን በሲና ተራራ ላይ ለሙሴ ተገልጦለታል።
• ለአምልኮ አገልግሎት የሚውሉ ሁለት ክፍሎች ነበሩት፦ ቅድስተ ቅዱሳን እና ቅድስት።
• እግዚአብሔር ለሙሴ "እንደማሳይህ ሁሉ እንደ ማደሪያው ምሳሌ እንዲሁ ሥሩት" (ዘጸ 25፥9) ብሎታል። ይህም የቤተ መቅደስ ሥራ ያለ ሥርዓት እንደማይሠራ ያሳያል።
. መቅደሰ ሰሎሞን:
• ንጉሥ ሰሎሞን የሠራው ቤተ መቅደስ ሦስት ክፍሎች ነበሩት፦ ኤላም (ዙሪያ)፣ ሃይከል (አዳራሽ) እና ዳቤር (ቅድስተ ቅዱሳን)።
• እነዚህ ቦታዎች ለአዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያን መሠረት ናቸው።
፪. በሐዲስ ኪዳን የነበረው ቤተ ክርስቲያን
የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች የራሳቸው የጸሎት ቤት በተወሰነ ቦታ አላደረጉም የተለያየም ሕንፃ አልሰሩም ነበር፡፡ ነገር ግን ወደ አይሁድ ቤተ መቅደስ በመሄድ ከአይሁድ ጋር የጸልዩ ነበር፡፡
• እንዲሁም በግል የክርስቲያን ቤቶች እየተገኙ በተለያዩ ክፍሎች እየተሰበሰቡ ይጸልዩ ፣ማእድንም ይባርኩ ፣ቅዱስ ቁርባንም ያዘጋጁ ነበር፡፡ ይህን የመሳሰሉትንአገልግሎቶች ይፈጽሙባቸው የነበሩትን ምኩራቦች የጸሎት መሰብሰቢያዎች እያሉ ይጠሩአቸው ነበር፡፡
• እየዋለ እያደረ ግን አማኒው እየበዛ ስለሄደ በእነዚህ ጠባብ ክፍልና ጠባብም ግቢ አምልኮት እግዚአብሔርን ለመፈጸም አልተቻለም፡፡ ስለዚህ ክርስቲያኖች ታላላቅ ሕንፃዎችን እያሳነፁ ቤተክርስቲያን መሥራት በዚያም መሰብሰብ አምልኮተ እግዚአብሔርንም መፈጸም ጀመሩ፡፡
• በአፍሪካ የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን በ60 ዓ.ም በእስክንድሪያ የተመሠረተችው በሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ ነው።
• ይህችም ቤተክተርስቲያን ሐዋርያት ለስብከተ ወንጌል ወደዓለም ከተሰማሩ በኋላ ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ በእስክንድሪያ በጰራቅሊጦስ ስም አሠረቶ ሰኔ 5 ቀን በ61ዓ.ም የቅዳሴ ቤተክርስቲያን በዓል አክብሯል።
• በቤተ ክርስቲያን ዙሪያ የሚሠሩ ቤቶች
ቤተ ክርስቲያን ሲሠራ አንድ ሕንፃ ብቻ ሳይሆን ከቤተ ክርስቲያኑ ጋር አብረው አገልግሎት የሚሰጡ ቤቶችም ያስፈልጋሉ። እነዚህ ቤቶች በሁለት ይከፈላሉ፦
• ግድ ከቤተ ክርስቲያኑ ሳይለዩ አብረው የሚሠሩ አስፈላጊ ቤቶች
• እንደ ቤተ ክርስቲያኑ አቅም ሊሠሩ የሚገባቸው ቤቶች
. የግድ ከቤተ ክርስቲያኑ ሳይለዩ አብረው የሚሠሩ አስፈላጊ ቤቶች የሚከተሉት ናቸው
ቤተልሔም
• በቤተ ክርስቲያኑ በምሥራቅ በኩል የሚሠራ ቤት ነው።
• ዲያቆናቱ ለመሥዋዕት የሚሆነውን ኅብስትና ወይን የሚያዘጋጁበት ነው።
• ስያሜው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደበት በቤተ ልሔም ዘይሁዳ ምሳሌ ነው።
• ምሥጢሩ ዲያቆናት ሕብስቱን በቤተልሔም አዘጋጅተው ወደ ቤተ ክርስቲያን መሥዋዕት መምጣታቸው በቤተልሔም የተወለደው በጎልጎታ ለመሥዋዕት የቀረበው ክርስቶስ ይህ ነው ለማለት ነው። መቅደስ የጎልጎታ ምሳሌ ነው።
የግብር ቤት
• ለመሥዋዕት የሚሆነው ስንዴ የሚሰየምበት/የሚደቅቅበት/የሚፈጭበት በቤተ ክርስቲያኑ ቅጽረ ግቢ የሚሠራ ቤት ነው።
• ስንዴው መገበሪያ ተብሏል፤ መፍጨቱ ደግሞ መሰየም ይባላል። ይህም የመሥዋዕቱ አቀራረብ ቋንቋ ነው።
ዕቃ ቤት
• የቤተ ክርስቲያን ንዋየ ቅድሳት የሚቀመጥበት ቤት ነው።
• የቤተ ክርስቲያኑ መገልገያ የሆኑት አልባሳት፣ መጻሕፍት የሚጠበቁት በዚህ ቤት ነው። (ሕዝ 44፥19፤ ፍት. መን. 12)
የማጥመቂያ ቤት/ክርስትና ቤት
• ሥርዓተ ጥምቀት የሚፈጸምበት ቤት ነው።
• ወንዶች በአርባ ቀን ሴቶች በሰማንያ ቀን ከሥላሴ ልጅነት የሚያገኙት በዚህ ሥርዓት ነው።
ደጀ ሰላም
• ከቤተ ክርስቲያኑ በስተምዕራብ በኩል የሚሠራ ቤት ነው።
• በቤተ ክርስቲያኑ ቅጽር ውስጥ የሚሠራ ሲሆን እንደ አካባቢው አገልግሎቱ ሊለያይ ይችላል።
• ለጸሎተ ፍትሐት፣ ለካህናት ማረፊያ፣ ለእንግዳ መቀበያ ወዘተ አገልግሎቶች ማስፈጸሚያ ሊውል ይችላል።
እንደ ቤተ ክርስቲያኑ አቅም ሊሠሩ የሚገባቸው ቤቶች ፦
• ሀ/ የሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት
• ለ/ የሰ/ት/ቤቶች ክፍሎች
• ሐ/ የምእመናን መማሪያ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ
• መ/ የእንግዶች/የካህናት ማረፊያ ቤቶች
• ሠ/ የመንፈሳዊ ት/ቤትና የተግባረ እድ መማሪያ ክፍሎች
• ረ/ ቤተ መጽሐፍት
• ሰ/ የመገልገያ ዕቃዎችና ጧፍ፣ ዕጣን ሽያጭ ክፍሎች
ማጠቃለያ:
ቤተ ክርስቲያን ስንል የአንድ ሕንፃ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፣ አብረውት የሚቆሙና የሚያገለግሉ ቤቶችም ጭምር ነው። እነዚህ ቤቶች የየራሳቸው አገልግሎት ያላቸው ሲሆን፣ ለቤተ ክርስቲያኒቱ እድገትና ምእመናን መንፈሳዊ ሕይወት ወሳኝ ናቸው።
ይህን መልዕክት ለሌሎችም በማጋራት ያወቅንውን እንድናሳውቅና ና በረከትን እንድናገኝ እንጋብዛችኋለን እንዲሁም ማንኛውም አይነት ጥያቄ ካላችሁ ግሩፑ ላይ አሳውቁን እንመልሳለን
በቀጣይ በቤተክርስቲያን ውስጥ ሊኖሩ የሚገቡ ንዋያተ ቅድሳትና የአቀማመጥና የአጠቃቀም ሥርዓት....
|| @AHATI_BETKERSTYAN