ለከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ለቀጣይ ሦስት ዓመታት በየዓመቱ 15 ቢሊየን ብር መመደቡን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ ገልጸዋል።
የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት የተጠቃሚዎች ሽግግር እና የማስጀመር መርሐ-ግብር በጅማ ከተማ እየተካሄደ ነው።
ሚኒስትሯ በዚህ ወቅት÷ በከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔትና የሥራ ፕሮጀክት ከ1 ነጥብ 7 ሚሊየን በላይ ዜጎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።
መንግሥት ተግባራዊ ያደረገውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ መሰረት በማድረግ በገጠር እና በከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ሥራዎች ዜጎችን ለመደጎምና በዘላቂነት ኑሯቸውን ለማሻሻል ለቀጣይ ሦስት ዓመታት በየዓመቱ 60 ቢሊየን ብር መመደቡንም አመልክተዋል።
ከዚህም ውስጥ በየዓመቱ 15 ቢሊየን ብር ለከተማ ሴፍቲኔት አንደተመደበ ጠቁመዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ በሁሉም ክልሎች እና በነባር የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ከተሞች ውስጥ 143 ሺህ 26 የቤተሰብ አባላት ወደ ዘላቂ የኑሮ ማሻሻያ የሚሸጋገሩበት እና 699 ሺህ 112 ዜጎች በቀጥታ ድጋፍና በአካባቢ ልማት ወደ ፕሮጀክቱ እንደሚቀላቀሉ ገልጸዋል።
የከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮጀክት የተጠቃሚዎች ሽግግር እና የማስጀመር መርሐ-ግብር በጅማ ከተማ እየተካሄደ ነው።
ሚኒስትሯ በዚህ ወቅት÷ በከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔትና የሥራ ፕሮጀክት ከ1 ነጥብ 7 ሚሊየን በላይ ዜጎች ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።
መንግሥት ተግባራዊ ያደረገውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ መሰረት በማድረግ በገጠር እና በከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ሥራዎች ዜጎችን ለመደጎምና በዘላቂነት ኑሯቸውን ለማሻሻል ለቀጣይ ሦስት ዓመታት በየዓመቱ 60 ቢሊየን ብር መመደቡንም አመልክተዋል።
ከዚህም ውስጥ በየዓመቱ 15 ቢሊየን ብር ለከተማ ሴፍቲኔት አንደተመደበ ጠቁመዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ በሁሉም ክልሎች እና በነባር የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ከተሞች ውስጥ 143 ሺህ 26 የቤተሰብ አባላት ወደ ዘላቂ የኑሮ ማሻሻያ የሚሸጋገሩበት እና 699 ሺህ 112 ዜጎች በቀጥታ ድጋፍና በአካባቢ ልማት ወደ ፕሮጀክቱ እንደሚቀላቀሉ ገልጸዋል።