ዐፄ ምኒልክ ከዐድዋ ድል በኋላ ለአውሮጳና ለሞስኮ መንግሥታት በላኩት ደብዳቤያቸው፤ የኢትዮጵያውያንን ታላቅ የሆነ የመንፈስ ልእልና የተላበሱ፣ ሰብአዊነትን፣ ርኅራኄንና ይቅር ባይነትን ገንዘብ ያደረጉ እና የላቀ የሞራል ከፍታ/High Moral Standards ያላቸው የታላቅ ሕዝብ መሪ እንደሆኑ አስመስክረዋል። ለአብነትም ዐጤ ምኒልክ ከዐድዋ ድል በኋላ መጋቢት 23 ቀን 1988 ዓ.ም. ለፈረንሳዊው ሙሴ ሸፍኔ በላኩለት ደብዳቤያቸው፤
"… ከአላጌ ጦርነት በኋላ፣ ጣሊያኖችን ጦርነት ይቅር፣ የክርስቲያንም ደም በከንቱ አይፍሰስ፣ እርቅ ይሻላል ብላቸው እምቢ ብለው መጥተው በጥጋባቸው ዓድዋ ላይ ተዋግ ተው ድል ሆኑ፡፡ እኔ ግን በድቁርናቸው ብዛት የነዚያን ሁሉ ሰዎች ደም በከንቱ መፍሰሱን እያየሁ ድል አደረግኳቸው ብዬ ደስ አይለኝም፡፡"
ብለዋል
"… ከአላጌ ጦርነት በኋላ፣ ጣሊያኖችን ጦርነት ይቅር፣ የክርስቲያንም ደም በከንቱ አይፍሰስ፣ እርቅ ይሻላል ብላቸው እምቢ ብለው መጥተው በጥጋባቸው ዓድዋ ላይ ተዋግ ተው ድል ሆኑ፡፡ እኔ ግን በድቁርናቸው ብዛት የነዚያን ሁሉ ሰዎች ደም በከንቱ መፍሰሱን እያየሁ ድል አደረግኳቸው ብዬ ደስ አይለኝም፡፡"
ብለዋል