TIKVAH-ETHIOPIA dan repost
“ የትራንስፓርትም ዋጋ ጨምሮባቸዋል። መድኃኒትም ከውጭ ነው የሚመጣውና በሁሉም ዋጋ ጨምሮባቸው በጣም በከፍተኛ ሲቃይ ናቸው ህሙማኑ ” - ማህበሩ
“ 400 ሺሕ ሰዎች ዲያሌሲስ ያስፈልጋቸዋል። አብዛኛዎቹ ዲያሊስ ማድረግ ስለማይችሉ ትተው ነው ያሉት ” በማለት የኩላሊት ህክምና እጥበት በጎ አድራጎት ማኅበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።
የማኀበሩ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሰለሞን አሰፋ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ምን አሉ?
“ ብዙ ወጣቶች ናቸው ዲያሌሲስ እያደረጉ ያሉት። ኩላሊት ደግሞ ከዘመድ ካልሆነ ከእኛ ሀገር ከሌላ ቦታ ማገኘት አይቻልም።
ትልቁ ችግር የኩላሊት ማግኘት ነው። ህሙማኑ የኩላሊት ንቅለ ተከላ ፍላጎት ቢኖራቸውም የሚሰጣቸው ሰው የለም። ቢኖርም እንኳ ቢኖር አንዳንዱ ማች አያደርግም።
አብዛኞቹ ዲያሌሲስ ማድረግ ላይ ነው ትኩረታቸውን የሚያደርጉት ንቅለ ተከላውን እስከሚያደርጉ ድረስ።
የትራንስፓርትም ዋጋ ጨምሮባቸዋል። መድኃኒትም ከውጭ ነው የሚመጣው በሁሉም ዋጋ ጨምሮባቸው በጣም ከፍተኛ ሲቃይ ላይ ናቸው ህሙማኑ።
ድጋፍ የሚያደርገው ሰውም በጣም እየቀነሰ ስለመጣ ህሙማኑ በጣም ትልቅ ችግር ውስጥ ነው። ዲያሌሲስ ሁለት ጊዜ፣ አንዴ የሚያደርጉ አሉ። አንዳንዶች የሚበሉትን፣ የሚጠጡትን እየቀነሱ ይገኛሉ” ብለዋል።
በኢትዮጵያ ስንት የኩላሊት ህሙማን አሉ ? ከእነዚህ መካከል ስንቶቹ ህክምና የመከታተል እድል አግኝተዋል ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም ምላሽ ሰጥተዋል።
ዋና ሥራ አስኪያጁ ፦
“ 400 ሺሕ የሚሆኑ ሰዎች ዲያሌሲስ ያስፈልጋቸዋል። አብዛኛዎቹ ዲያሌሲስ ማድረግ ስለማይችሉ ትተው ነው።
ግማሹ ጸበል ይሄዳል። ስለማንሰማ እንጂ ህይወታቸው የሚያልፈው ይበዛሉ። ዲያሌሲስ በማድረግ የሚታገለውን ነው የምናውቀው። ያም ቢሆን ሲቸግረው አንድም ሁለትም ጊዜ ዲያሌሲስ የሚያደርግ አለ በወር ውስጥ።
ይተዛዘናሉ። ሦስት ጊዜ ዲያሌሲስ የሚያደርገው ሰውዬ ‘ሁለት ይበቃኛል’ ብሎ አንዱን ለሌላ ይሰጣል። በእንደዚህ እየታገሉ ነው ያሉት።
የምንችለውን እያደረግን ለተወሰኑ ሰዎች ነው ለመድረስ የቻልነው ለብዙ ሰዎች መድረስ አልቻልንም። ምንክንያቱም ድጋፉ በደንብ ተጠናክሮ እየቀጠለ አይደለም።
ህብረተሰቡም ደግሞ ስለ ጉዳዩ ያገባኛል ብሎ ትኩረት ሰጥቶ ሲረዳ አንመለከትም። የሚያጭበረብረው ሰውም በዝቷል ” ሲሉ አስረድተዋል።
ማህበሩ ፤ “ ሰው ለመርዳት ችግር የለበትም ይረዳል። ትልቁ ችግር ማስታወስ ላይ ነው ያለው። እናንተም ለህብረተሰቡ በማስታወስ እርዱን ” ሲል አሳስቧል።
“ ትልቅ መፍትሄ ይሆናል ብለን የምናስበው ከሞተ ሰው ኩላሊት እንዲወሰድ የህግ ማዕቀፍ ሲወጣ ነው ” ያለው ማኀበሩ፣ “ ሲጸድቅ ሰዎች ሰላም ያገኛሉ። እስከዚያ ድረስ ዲያሌሲስ እያደረጉ መቆየት ግድ ይላቸዋል ” ብሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ 400 ሺሕ ሰዎች ዲያሌሲስ ያስፈልጋቸዋል። አብዛኛዎቹ ዲያሊስ ማድረግ ስለማይችሉ ትተው ነው ያሉት ” በማለት የኩላሊት ህክምና እጥበት በጎ አድራጎት ማኅበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።
የማኀበሩ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሰለሞን አሰፋ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ምን አሉ?
“ ብዙ ወጣቶች ናቸው ዲያሌሲስ እያደረጉ ያሉት። ኩላሊት ደግሞ ከዘመድ ካልሆነ ከእኛ ሀገር ከሌላ ቦታ ማገኘት አይቻልም።
ትልቁ ችግር የኩላሊት ማግኘት ነው። ህሙማኑ የኩላሊት ንቅለ ተከላ ፍላጎት ቢኖራቸውም የሚሰጣቸው ሰው የለም። ቢኖርም እንኳ ቢኖር አንዳንዱ ማች አያደርግም።
አብዛኞቹ ዲያሌሲስ ማድረግ ላይ ነው ትኩረታቸውን የሚያደርጉት ንቅለ ተከላውን እስከሚያደርጉ ድረስ።
የትራንስፓርትም ዋጋ ጨምሮባቸዋል። መድኃኒትም ከውጭ ነው የሚመጣው በሁሉም ዋጋ ጨምሮባቸው በጣም ከፍተኛ ሲቃይ ላይ ናቸው ህሙማኑ።
ድጋፍ የሚያደርገው ሰውም በጣም እየቀነሰ ስለመጣ ህሙማኑ በጣም ትልቅ ችግር ውስጥ ነው። ዲያሌሲስ ሁለት ጊዜ፣ አንዴ የሚያደርጉ አሉ። አንዳንዶች የሚበሉትን፣ የሚጠጡትን እየቀነሱ ይገኛሉ” ብለዋል።
በኢትዮጵያ ስንት የኩላሊት ህሙማን አሉ ? ከእነዚህ መካከል ስንቶቹ ህክምና የመከታተል እድል አግኝተዋል ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም ምላሽ ሰጥተዋል።
ዋና ሥራ አስኪያጁ ፦
“ 400 ሺሕ የሚሆኑ ሰዎች ዲያሌሲስ ያስፈልጋቸዋል። አብዛኛዎቹ ዲያሌሲስ ማድረግ ስለማይችሉ ትተው ነው።
ግማሹ ጸበል ይሄዳል። ስለማንሰማ እንጂ ህይወታቸው የሚያልፈው ይበዛሉ። ዲያሌሲስ በማድረግ የሚታገለውን ነው የምናውቀው። ያም ቢሆን ሲቸግረው አንድም ሁለትም ጊዜ ዲያሌሲስ የሚያደርግ አለ በወር ውስጥ።
ይተዛዘናሉ። ሦስት ጊዜ ዲያሌሲስ የሚያደርገው ሰውዬ ‘ሁለት ይበቃኛል’ ብሎ አንዱን ለሌላ ይሰጣል። በእንደዚህ እየታገሉ ነው ያሉት።
የምንችለውን እያደረግን ለተወሰኑ ሰዎች ነው ለመድረስ የቻልነው ለብዙ ሰዎች መድረስ አልቻልንም። ምንክንያቱም ድጋፉ በደንብ ተጠናክሮ እየቀጠለ አይደለም።
ህብረተሰቡም ደግሞ ስለ ጉዳዩ ያገባኛል ብሎ ትኩረት ሰጥቶ ሲረዳ አንመለከትም። የሚያጭበረብረው ሰውም በዝቷል ” ሲሉ አስረድተዋል።
ማህበሩ ፤ “ ሰው ለመርዳት ችግር የለበትም ይረዳል። ትልቁ ችግር ማስታወስ ላይ ነው ያለው። እናንተም ለህብረተሰቡ በማስታወስ እርዱን ” ሲል አሳስቧል።
“ ትልቅ መፍትሄ ይሆናል ብለን የምናስበው ከሞተ ሰው ኩላሊት እንዲወሰድ የህግ ማዕቀፍ ሲወጣ ነው ” ያለው ማኀበሩ፣ “ ሲጸድቅ ሰዎች ሰላም ያገኛሉ። እስከዚያ ድረስ ዲያሌሲስ እያደረጉ መቆየት ግድ ይላቸዋል ” ብሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia