🎖 #ምስጢሮችህን_ራስህ_ጋር_ማቆየት_ቻል🎖
✍አሚር ሰይድ
ከጀርመን እስር ቤቶች በአንዱ ጠባቂዎቹ የጭካኔና የበደል ዱላቸውን ዘወትር በታሳሪዎች ላይ ያሳርፋሉ። “ሽሚት” የተባለ ረጅም የእስራት ጊዜ የተፈረደበት አንድ ሰው በፍርግርጉ ውስጥ አለ። ይህ እስረኛ በጥበቃዎች አክብሮት የተሞላበት መልካም አያያዝ ሲደረግለት ቀሪዎቹ የእስርቤቱ እስረኞች እነሱን ሊሰልል የመጣ ሰው አድርገው ይገምቱታል።
....በአንድ ወቅት በዚህ ግምታቸው ምላሽ ይሆን ዘንድ ከፖሊሶች ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት እንደሌለው እየማለ ነገራቸው። ማንም አላመነውም “የእስር ቤቱ ጠባቂዎች ለምን ከእኛ የተለየ እንክብካቤና አያያዝ እንደሚያደርጉልህ ማወቅ አንፈጋለን" አሉት።
ሸሚትም “እስኪ ንገሩኝ ለዘመዶቻችሁ የምትፅፉትን ሳምንታዊ ደብዳቤ ምን ብላችሁ ነው የምትጀምሩት??"
“ስለ እነዚህ የተረገሙ ጠባቂዎች የእስርና የግፍ ጭካኔያቸው በደብዳቤዎቻችን ላይ አንነግራቸዋለን" አሉት።
“እኔ ግን በየሳምንቱ ለባለቤቴ ደብዳቤ እፅፋለሁ። በመጨረሻው መስመር ላይ የእስር ቤቱንና የጠባቂዎቹን መልካም አያያዝ እጠቅሳለሁ። አንዳንዴም ስማቸውን እየዘረዘርኩ አወድሳቸዋለሁ"
"አያያዛቸው ጭካኔ የተሞላበትና ከባድ መሆኑን እያወቅክ እንዴት ታወድሳቸዋለህ?" ብለው
ጠየቁት።
“ምክንያቱም ደብዳቤዎቻችን በጥበቃዎች ሳይነበቡ ከእስር ቤት አይወጡምና በፁሁፋችን ውስጥ የሰፈረውን እያንዳንዷን ነገር ጠንቅቀው ያውቃሉ የደብዳቤያችሁን የአፃፃፍ ዘይቤ ለውጡ" በማለት መከራቸው።
በሚቀጥለው ሳምንት ሁሉም እስረኞች የአፃፃፍ ስልታቸውን ቀይረው ወደ ቤተሰቦቻቸው ደብዳቤን ላኩ። ከቀናት በኋላ የእስር ቤቱ ጠባቂዎች አያያዛቸው በከፋ መልኩ ተቀየረ። ሁሉንም እስረኞች ማሰቃየት ጀመሩ። አሁን ሽሚትም አልቀረለትም አብሯቸው ይደበደብ ጀመር።
ሁኔታው ግራ የገባው ሸሚት ከጥቂት ቀናት በኋላ እስረኞቹን “በደብዳቤያችሁ ላይ የፃፋችሁት ምንድን ነው? " ሲል ጠየቃቸው።
እንዲህ አሉት "የተረገሙትን ጠባቂዎች አታለን ጥሩ አያያዝ የምናገኝበት ዘዴ እንዳስተማርከን ፅፈናል" አሉት።
ሸሚዝ ጉንጮቹን እየደበደበና ፀጉሩን እንደ እብድ እየነጨ አቀርቅሮ ተቀመጠ።
⚠️⚠️ #እናም_ወዳጄ
ሌሎችን መርዳት መልካም ተግባር ቢሆንም ከማን ጋር ማውራት እንዳለብህ ልታውቅ ይገባሀል። ሁሉም አድማጭ ሚስጢር ጠባቂ አይደለም። ልብህን ለሁሉም ሰው ክፍት አታድርግ። የመኖርህ ጌጥ የሆኑትን ምስጢሮችህን ራስህ ጋር ማቆየት ካልቻልክ እመነኝ ሌሎች ሰዎች ምስጢርህን ለመጠበቅ የሚችል ልብ አይኖራቸውም።
#ምንጭ☞ታሪኮችን ተርክላቸዉ መፅሀፍ
🔰#ለሌሎች_ያጋራሉ
join👇👇👇
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
✍አሚር ሰይድ
ከጀርመን እስር ቤቶች በአንዱ ጠባቂዎቹ የጭካኔና የበደል ዱላቸውን ዘወትር በታሳሪዎች ላይ ያሳርፋሉ። “ሽሚት” የተባለ ረጅም የእስራት ጊዜ የተፈረደበት አንድ ሰው በፍርግርጉ ውስጥ አለ። ይህ እስረኛ በጥበቃዎች አክብሮት የተሞላበት መልካም አያያዝ ሲደረግለት ቀሪዎቹ የእስርቤቱ እስረኞች እነሱን ሊሰልል የመጣ ሰው አድርገው ይገምቱታል።
....በአንድ ወቅት በዚህ ግምታቸው ምላሽ ይሆን ዘንድ ከፖሊሶች ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት እንደሌለው እየማለ ነገራቸው። ማንም አላመነውም “የእስር ቤቱ ጠባቂዎች ለምን ከእኛ የተለየ እንክብካቤና አያያዝ እንደሚያደርጉልህ ማወቅ አንፈጋለን" አሉት።
ሸሚትም “እስኪ ንገሩኝ ለዘመዶቻችሁ የምትፅፉትን ሳምንታዊ ደብዳቤ ምን ብላችሁ ነው የምትጀምሩት??"
“ስለ እነዚህ የተረገሙ ጠባቂዎች የእስርና የግፍ ጭካኔያቸው በደብዳቤዎቻችን ላይ አንነግራቸዋለን" አሉት።
“እኔ ግን በየሳምንቱ ለባለቤቴ ደብዳቤ እፅፋለሁ። በመጨረሻው መስመር ላይ የእስር ቤቱንና የጠባቂዎቹን መልካም አያያዝ እጠቅሳለሁ። አንዳንዴም ስማቸውን እየዘረዘርኩ አወድሳቸዋለሁ"
"አያያዛቸው ጭካኔ የተሞላበትና ከባድ መሆኑን እያወቅክ እንዴት ታወድሳቸዋለህ?" ብለው
ጠየቁት።
“ምክንያቱም ደብዳቤዎቻችን በጥበቃዎች ሳይነበቡ ከእስር ቤት አይወጡምና በፁሁፋችን ውስጥ የሰፈረውን እያንዳንዷን ነገር ጠንቅቀው ያውቃሉ የደብዳቤያችሁን የአፃፃፍ ዘይቤ ለውጡ" በማለት መከራቸው።
በሚቀጥለው ሳምንት ሁሉም እስረኞች የአፃፃፍ ስልታቸውን ቀይረው ወደ ቤተሰቦቻቸው ደብዳቤን ላኩ። ከቀናት በኋላ የእስር ቤቱ ጠባቂዎች አያያዛቸው በከፋ መልኩ ተቀየረ። ሁሉንም እስረኞች ማሰቃየት ጀመሩ። አሁን ሽሚትም አልቀረለትም አብሯቸው ይደበደብ ጀመር።
ሁኔታው ግራ የገባው ሸሚት ከጥቂት ቀናት በኋላ እስረኞቹን “በደብዳቤያችሁ ላይ የፃፋችሁት ምንድን ነው? " ሲል ጠየቃቸው።
እንዲህ አሉት "የተረገሙትን ጠባቂዎች አታለን ጥሩ አያያዝ የምናገኝበት ዘዴ እንዳስተማርከን ፅፈናል" አሉት።
ሸሚዝ ጉንጮቹን እየደበደበና ፀጉሩን እንደ እብድ እየነጨ አቀርቅሮ ተቀመጠ።
⚠️⚠️ #እናም_ወዳጄ
ሌሎችን መርዳት መልካም ተግባር ቢሆንም ከማን ጋር ማውራት እንዳለብህ ልታውቅ ይገባሀል። ሁሉም አድማጭ ሚስጢር ጠባቂ አይደለም። ልብህን ለሁሉም ሰው ክፍት አታድርግ። የመኖርህ ጌጥ የሆኑትን ምስጢሮችህን ራስህ ጋር ማቆየት ካልቻልክ እመነኝ ሌሎች ሰዎች ምስጢርህን ለመጠበቅ የሚችል ልብ አይኖራቸውም።
#ምንጭ☞ታሪኮችን ተርክላቸዉ መፅሀፍ
🔰#ለሌሎች_ያጋራሉ
join👇👇👇
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
t.me/IslamisUniverstiy_public_group