Ministry of Revenues of Ethiopia/የገቢዎች ሚኒስቴር


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


የገቢዎች ሚኒስቴር ኢኮኖሚው የሚያመነጨው ገቢ እንዲሰበስብ ኃላፊነት የተሰጠው የፌዴራል ተቋም ነው፡፡
የጉምሩክ ኮሚሽንን በስሩ ይዞ ተደራጅቷል፡፡

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


«ገቢ ለልማት» ጋዜጣ

ጥር 28/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

ውድ የጋዜጣችን አንባቢዎች፤ እንደተለመደው ገቢ ለልማት ጋዜጣ ዕትም 180 ብዙ ጠቃሚ መልዕክቶችን ይዞ ቀርቧል፡፡ ስለሆነም ለውጤታማነቱ የናንተ አስተያየት ከፍተኛ ድርሻ አለውና በማንበብ አስተያየትዎን ይስጡን፡፡

ከፌስቡክ ገጽ በተጨማሪ ጋዜጣዋን በሚኒስቴሩ ቴሌግራም እና ዌብሳይት ገጽ እንዲሁም ህትመቷ በነጻ እየተሰራጨባቸው ባሉ የገቢዎችም ሆነ ጉምሩክ ዋና መ/ቤቶች እና ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች፤ በከተማ አስተዳደር እና ከክልል እስከ ወረዳ ባሉ የገቢው ዘርፍ ጽ/ቤቶች በመውሰድ እንድታነቡ ጋብዘናችኋል፡፡

ጋዜጣውን ለማገኘት ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ፡- https://shorturl.at/vPOdg




ሚዲያ በሀገር ግንባታ ሂደት ውስጥ ትልቁን ድርሻ ይወስዳል

ጥር 27/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

የገቢዎች ሚኒስቴር የበላይ አመራሮች የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በአዲስ አበባ ያስገነባውን አዲስ ስቱዲዮ ጎብኝተዋል::

በጉብኝታቸውም ክብርት ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ ግንባታው የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በሀገር ግንባታ ላይ እየሰራቸው ያሉ ጠንካራ ሥራዎችን የሚመጥን ስቱዲዮ ነው ያሉ ሲሆን በቀጣይም ለሚሰራቸው አብሮነትን አና ወንድማማችነትን የሚፈጥሩ አሰባሳቢ ሃገራዊ ትርክቶች ይበልጥ ምቹ መሆኑን ገልጸዋል::

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://rb.gy/52pals




የገቢዎች ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት እየተከናወነ ያለው በልዩ መለያ ኮድ (QR COD) የተደገፈ የ ደረሰኝ ህትመት ያለበትን ሂደት ጎበኙ

ጥር 27/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

ከየካቲት 03 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ተግባር የሚገባዉ ልዩ መለያ ኮድ (QR COD) ደረሰኝ ህትመትን አስመልክቶ የገቢዎች ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ፣ የታክስ ስርአት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ መስከረም ደበበ፣ የታክስ ኦፕሬሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ አብዱረህማን ኢድ ጣሂር፣ በብርሃን እና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ተገኝተዉ ህትመቱ ያለበትን ሂደት ጎብኝተዋል፡፡

የደረሰኝ አጠቃቀምን ለማሻሻል እየተሰሩ ካሉ ዋነኛ ተግባራት ዉስጥ ደረሰኝን በልዩ መለያ ኮድ (QR COD) የተደገፈ ማድረግ መሆኑ ታምኖ ወደተግባር ተገብቷል፡፡

በዚህም መሰረት የደረሰኝ ህትመቱን በኃላፊነት ወስዶ እየሰራ ያለዉ የብርሃንና ሰላም የህትመት ድርጅት የደረሰኝ ህትመቱ አሁን ያለበትን ሂደት በተመለከተ ለሚኒስቴር መስሪያቤቱ ከፍተኛ አመራሮች ሂደት አስጎብኝቶ ሪፖርትም አቅርቧል፡፡

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://shorturl.at/Hce3U




The cooperation of the World Bank and the Ministry of Revenues

February 4, 2024 (Ministry of Revenues)

The Minister of Revenues H.E Ms. Aynalem Nigussie has received the World Bank director for Ethiopia, Eritrea, South Sudan, Sudan, Eastern and Southern Africa region Ms. Maryam Salhim at her office.

The main aim of the visit is to discuss the issues of mission for development policy operation and tax policy reform.

The minister of Revenues H.E Ms. Aynalem Nigussie highlighted that the government of Ethiopia is performing various initiatives to boost the revenues sector. Among those initiatives tax digitalization is the most prominent. The main aim of the initiative is to create to boost domestic revenues as her.

Ms. Maryam Salhim (director for Ethiopia, Eritrea, South Sudan, Sudan, Eastern and Southern Africa region) on her side said that Ethiopia is one of the countries that supported by the World Bank. The initiatives executed by the Ethiopian government will have a substantial impact on enhancing domestic revenues.

By:- Shimelis sisay
photo:- Yetinayet Endayafru




#የደስታ_መግለጫ

ጥር 27/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

ክብርት መሪያችን ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ በድጋሚ የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ሆኖ መመረጥ የግል ስኬት ብቻ ሳይሆን እንደተቋም ያሳዩትን ቁርጠኝነት፣ የአመራር ብቃት እና ለሕዝብ አገልጋይነት ያላቸውን ጽናት የሚያሳይ ነው!


የአሰራር ስርዓትን ማዘመን የተቋሙ የለዉጥ ሂደት አንድ አካል ነው

ጥር 26/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

የገቢዎች ሚኒስቴር ከአለም ባንክ ተወካይ ቡድን ጋር በታክስ አስተዳደር በኤክሳይስ ታክስ መመሪያዎች እና ታክስ ማበረተቻን በተመለከ በጋራ ለመስራት ተወያዩ፡፡

በመድረኩም የአለም የታክስ ህግ ተገዥነትን እንዲሁም ታክስ ከሃገራዊ ምርት አንፃር ያለዉ ጥምርታን ከፍ ለማድረግ ያስችላሉ ያሏቸዉን የታክስ ማበረታቻ ፤ታክስ አስተዳደር እና የኤክሳይስ ታክስ መመሪያዎች ላይ ዉጤታማ እና አለማቀፍ ተሞክሮ ያላቸዉ የአሰራር ስርአቶች በዓለም ባንክ ተወካዮች ቡድን መሪ በ አቶ ራጁ አዉታሸ ቀርበው ዉይይት ተደርባቸዋል፡፡

የገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ኦፕሬሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴታ አቶ አቡዱረህማን ኢድ ጣሂር ሚኒስቴር መስሪያቤቱ አሁንም በለዉጥ ሂደት ዉስጥ መሆኑን ገልፅዉ ባንኩ በተለያዩ ጉዳዮች ከእኛ ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑና እያከናወነው ላለው ለዉጣ ትኩረት የሚሰጥ ሃሳብ ይዛችሁ በጋራ ለመስራት በመምጣታችሁ ደስተኛ ነን በለዋል ::

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡-https://shorturl.at/mpERB

10 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.