ባለ ጦር በጦሩ ይተማመናል።
ባለ ጡንቻው በጡንቻው ይመካል።
ጦር እና ጡንቻ ከፈጣሪ ዘንድ ናቸው።
የሚልካቸውም፣ የሚያጠፋቸውም እሱ ነው።
እግዚአብሔርን በቅንነት የያዘ ለድል አይጓጓም።
በሶምሶን እና በዳዊት ላይ አድሮ ድልን በምሳሌ ያስተማረን የድንግል ማሪያም ልጅ ብቻ ነው።
ቅረቡኝ ልቀራባችሁ፣ ጥሩኝ ወደ ድል ተራራ ላውጣችሁ እያለ ነው።
አምላከ ቅዱሳን ሲረሳ መከራ አምጥቶ እንዲታወስ ያደርጋል።
ጥበቡ ረቂቅ ነው። እንደ ምድር ነገሥስታት በአፈ ቀላጤዎች የማይወደስ።
በዲዳዎች የሚወደስ፣ ጸጋው የማይለካ፣ ቸርነቱ የማይመዘን፣ ትዕግስቱ የማይወሰን።
እግዚአብሔር ሲወድ ጅቡን ሰው፣ እግዚአብሔር ሲጠላ ሰውን ጅብ " የሚያደርገው
የዓለም ፈጣሪ ሥሉስ ቅዱስ ነው። በስሙ ላደሩት ሰይጣን አቅም የለውም።
ሲያስታውሱት የሚያስታውስ፣ ሲረሱት የሚታገዝ ፣ ጊዜ የሚሰጥ።
ከእሳት መካከል ገለባን የሚያተርፍ።
ከውሀ መካከል ገለባን የሚያወድም።
አመጣጡ የማይገመት ፣ ለቀረቡት የሚገለጥ።
የቅዱሳን አመላክ ፣ ፀሐይ የምስራቋ የእመብርሃን ልጅ።
በከብቶች ማደሪያ የተወለደ፣ የትህትና አባት።
በእንጨት መስቀል የተሰቀለ የመከራ አባት።
በፈጠረው ዓለም የተሰደደ የስደተኞች አባት።
ሕዝቡን ለመማር የወረደ የምህረት አባት።
ሁሉንም እንደ ስራው የሚከፍል የፍትህ አባት።
በጭንቀት መካከል የሚደርስ፣ በጥጋብም መካከል የማይጠፋ።
ጉልበታሙን የሚያመክን፣ ጭቁኑን የሚያነግሥ።
ሁልጊዜ በንስሀ መንገድ ለሚሄዱት ወዳጆቹ የሚከሰት።
ስጋ ደሙን ለጠጡት ወዳጆቹ የቀረበ።
ለሚለግሱ ድልን የሚለግስ ደግ።
ለሚራሩ ርህራሄውን የሚሰጥ ሩህሩህ።
በአፍ መመጻደቅ ውስጥ የሌለ፣ በድዳዎቹ በየዋሆቹ ውስጥ ያለ።
ፍቅር መግቦ ፍቅር የሚቀበል።
ትህትና ሰጥቶ ትህትና የሚቀበል።
ደግነትን ሰጥቶ ደግነትን የሚቀበል።
መከራንም ሰጥቶ መከረኞችን የሚቀበል።
ስደትን ሰጥቶ ስደትን የሚቀበል።
መገረፍን ሰጥቶ መገረፍን የሚቀበል።
የተገፉት አባት ፣ አምላከ ኢትዮጵያ ማራናታ ቶሎ ና
አምላከ ኢትዮጵያ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አድነን።
አምላከ ቅዱሳን ኤልሻዳይ አለሁ በለን። ያለፈው በደል በንስሐ ታጥቦ እንደ ገና ንጹህ ካልሆን ጩኸታችን የተኩላ ነው የቀበሮ ጸሎት።
🌷ሰናይ ምሽት✝
ባለ ጡንቻው በጡንቻው ይመካል።
ጦር እና ጡንቻ ከፈጣሪ ዘንድ ናቸው።
የሚልካቸውም፣ የሚያጠፋቸውም እሱ ነው።
እግዚአብሔርን በቅንነት የያዘ ለድል አይጓጓም።
በሶምሶን እና በዳዊት ላይ አድሮ ድልን በምሳሌ ያስተማረን የድንግል ማሪያም ልጅ ብቻ ነው።
ቅረቡኝ ልቀራባችሁ፣ ጥሩኝ ወደ ድል ተራራ ላውጣችሁ እያለ ነው።
አምላከ ቅዱሳን ሲረሳ መከራ አምጥቶ እንዲታወስ ያደርጋል።
ጥበቡ ረቂቅ ነው። እንደ ምድር ነገሥስታት በአፈ ቀላጤዎች የማይወደስ።
በዲዳዎች የሚወደስ፣ ጸጋው የማይለካ፣ ቸርነቱ የማይመዘን፣ ትዕግስቱ የማይወሰን።
እግዚአብሔር ሲወድ ጅቡን ሰው፣ እግዚአብሔር ሲጠላ ሰውን ጅብ " የሚያደርገው
የዓለም ፈጣሪ ሥሉስ ቅዱስ ነው። በስሙ ላደሩት ሰይጣን አቅም የለውም።
ሲያስታውሱት የሚያስታውስ፣ ሲረሱት የሚታገዝ ፣ ጊዜ የሚሰጥ።
ከእሳት መካከል ገለባን የሚያተርፍ።
ከውሀ መካከል ገለባን የሚያወድም።
አመጣጡ የማይገመት ፣ ለቀረቡት የሚገለጥ።
የቅዱሳን አመላክ ፣ ፀሐይ የምስራቋ የእመብርሃን ልጅ።
በከብቶች ማደሪያ የተወለደ፣ የትህትና አባት።
በእንጨት መስቀል የተሰቀለ የመከራ አባት።
በፈጠረው ዓለም የተሰደደ የስደተኞች አባት።
ሕዝቡን ለመማር የወረደ የምህረት አባት።
ሁሉንም እንደ ስራው የሚከፍል የፍትህ አባት።
በጭንቀት መካከል የሚደርስ፣ በጥጋብም መካከል የማይጠፋ።
ጉልበታሙን የሚያመክን፣ ጭቁኑን የሚያነግሥ።
ሁልጊዜ በንስሀ መንገድ ለሚሄዱት ወዳጆቹ የሚከሰት።
ስጋ ደሙን ለጠጡት ወዳጆቹ የቀረበ።
ለሚለግሱ ድልን የሚለግስ ደግ።
ለሚራሩ ርህራሄውን የሚሰጥ ሩህሩህ።
በአፍ መመጻደቅ ውስጥ የሌለ፣ በድዳዎቹ በየዋሆቹ ውስጥ ያለ።
ፍቅር መግቦ ፍቅር የሚቀበል።
ትህትና ሰጥቶ ትህትና የሚቀበል።
ደግነትን ሰጥቶ ደግነትን የሚቀበል።
መከራንም ሰጥቶ መከረኞችን የሚቀበል።
ስደትን ሰጥቶ ስደትን የሚቀበል።
መገረፍን ሰጥቶ መገረፍን የሚቀበል።
የተገፉት አባት ፣ አምላከ ኢትዮጵያ ማራናታ ቶሎ ና
አምላከ ኢትዮጵያ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አድነን።
አምላከ ቅዱሳን ኤልሻዳይ አለሁ በለን። ያለፈው በደል በንስሐ ታጥቦ እንደ ገና ንጹህ ካልሆን ጩኸታችን የተኩላ ነው የቀበሮ ጸሎት።
🌷ሰናይ ምሽት✝