ፍርሃት የገዛው ትውልድ!
ይህ ትውልድ ፍርሃት የገዛው ትውልድ ነው፡፡ ፍርሃት የገዛው ትውልድ በሁሉም ሁኔታ ውስጥ ፍርሃት ያገኘዋል፡፡
ሰዎች አይወዱኝም ብሎ ይፈራል፤ የሚወደው ሰው ሲያገኝ ደግሞ የወደደው ሰው መልሶ እንዳይጠላው ይፈራል፡፡
ተቀባይነት አጣለሁ ብሎ ይፈራል፤ ተቀባይነት የሚሰጠው ሰው ሲያገኝ ደግሞ መልሶ እንዳይገፋው ይፈራል፡፡
ከሰው ጋር መሆን ይፈራል፤ ከሰው ሸሽቶ ብቻውንም ቢሆንም ይፈራል፡፡
የቀረበው ሰው እንዳይጎዳው ይፈራል፤ ሰውየው ከጎዳው ደግሞ እንደገና ላለመጎዳት ሲል ከዚያ ሰው መለየትን ሲያስብ ሰውየውን እጎዳዋለሁ ብሎ ደግሞ ይፈራል፡፡
ሳላገባ ብቻዬን ልቀር ነው ብሎ ይፈራል፤ ካገባሁ ግን እጎዳለሁ ብሎ ስለሚያስብ ማግባትን ይፈራል፡፡
ስለሚፈራ እንቅልፍ አይወስደውም፤ እንቅልፍ ስላልወሰደው ደግሞ ይፈራል፡፡
እንዳይነግድ ክስረትን ይፈራል፤ እንዲሁ ቁጭ እንዳይል ድህነትን ይፈራል፡፡
ደፍሮ ከወጣ አደጋን ይፈራል፤ ፈርቶ ከቀረ ደግሞ ሰዎች ፈሪ ነው ብለው ያስባሉ ብሎ ይፈራል፡፡
ከፍርሃት የተነሳ መሆንና ማድረግ ያለብህን ሳታደርግ አንድ መቶ አመት ከምትኖር ፍርሃትህን ተጋፍጠህና ቀና ብለህ አስር አመት በዓላማ ኖረህ ብታልፍ ይሻልሃል፡፡
ከፍርሃት ነጻ የሆነ ሕይወት ሊኖር ያለመቻሉን ያህል ፍርሃትን ተጋፍጦ ከመኖር ውጪ ስኬት የለም!
ምንጭ : Dr. eyob
@Sewsinor
@Sewsinor
ይህ ትውልድ ፍርሃት የገዛው ትውልድ ነው፡፡ ፍርሃት የገዛው ትውልድ በሁሉም ሁኔታ ውስጥ ፍርሃት ያገኘዋል፡፡
ሰዎች አይወዱኝም ብሎ ይፈራል፤ የሚወደው ሰው ሲያገኝ ደግሞ የወደደው ሰው መልሶ እንዳይጠላው ይፈራል፡፡
ተቀባይነት አጣለሁ ብሎ ይፈራል፤ ተቀባይነት የሚሰጠው ሰው ሲያገኝ ደግሞ መልሶ እንዳይገፋው ይፈራል፡፡
ከሰው ጋር መሆን ይፈራል፤ ከሰው ሸሽቶ ብቻውንም ቢሆንም ይፈራል፡፡
የቀረበው ሰው እንዳይጎዳው ይፈራል፤ ሰውየው ከጎዳው ደግሞ እንደገና ላለመጎዳት ሲል ከዚያ ሰው መለየትን ሲያስብ ሰውየውን እጎዳዋለሁ ብሎ ደግሞ ይፈራል፡፡
ሳላገባ ብቻዬን ልቀር ነው ብሎ ይፈራል፤ ካገባሁ ግን እጎዳለሁ ብሎ ስለሚያስብ ማግባትን ይፈራል፡፡
ስለሚፈራ እንቅልፍ አይወስደውም፤ እንቅልፍ ስላልወሰደው ደግሞ ይፈራል፡፡
እንዳይነግድ ክስረትን ይፈራል፤ እንዲሁ ቁጭ እንዳይል ድህነትን ይፈራል፡፡
ደፍሮ ከወጣ አደጋን ይፈራል፤ ፈርቶ ከቀረ ደግሞ ሰዎች ፈሪ ነው ብለው ያስባሉ ብሎ ይፈራል፡፡
ከፍርሃት የተነሳ መሆንና ማድረግ ያለብህን ሳታደርግ አንድ መቶ አመት ከምትኖር ፍርሃትህን ተጋፍጠህና ቀና ብለህ አስር አመት በዓላማ ኖረህ ብታልፍ ይሻልሃል፡፡
ከፍርሃት ነጻ የሆነ ሕይወት ሊኖር ያለመቻሉን ያህል ፍርሃትን ተጋፍጦ ከመኖር ውጪ ስኬት የለም!
ምንጭ : Dr. eyob
@Sewsinor
@Sewsinor