ሡጁዱል ዒባዳህ
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
18፥110 «በጌታውም "አምልኮ" አንድንም አያጋራ» በላቸው፡፡ وَلَا يُشْرِكْ بِعِبَادَةِ رَبِّهِ أَحَدًا
"ዒባዳህ" عِبَادَة የሚለው ቃል "ዐበደ" عَبَدَ ማለትም "አመለከ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "አምልኮ" ማለት ነው፦
18፥110 «በጌታውም "አምልኮ" አንድንም አያጋራ» በላቸው፡፡ وَلَا يُشْرِكْ بِعِبَادَةِ رَبِّهِ أَحَدًا
"ሡጁድ" سُجُود የሚለው ቃል "ሠጀደ" سَجَدَ ማለትም "ሰገደ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ስግደት" ማለት ነው፥ በጥቅሉ "ሡጁዱል ዒባዳህ" سُجُود الْعِبَادَة ማለት "የአምልኮ ስግደት" ማለት ነው፦
6፥56 «እኔ እነዚያን ከአሏህ ሌላ የምትጠሩዋቸውን ከማምለክ ተከልክያለሁ» በላቸው፡፡ قُلْ إِنِّي نُهِيتُ أَنْ أَعْبُدَ الَّذِينَ تَدْعُونَ مِن دُونِ اللَّهِ
7፥206 እነዚያ እጌታህ ዘንድ ያሉት መላእክት እርሱን ከማምለክ አይኮሩም፥ ያወድሱታልም፡፡ ለእርሱ ይሰግዳሉ፡፡ إِنَّ الَّذِينَ عِندَ رَبِّكَ لَا يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِهِ وَيُسَبِّحُونَهُ وَلَهُ يَسْجُدُونَ ۩
የባሕርይ ስግደት"Ontological Prostration" ለአንዱ አምላክ ብቻ የሚቀርብ የአምልኮ ስግደት ሲሆን ለአንዱ አምላክ ለአሏህ ብቻ የሚቀርብ መጎባደድ፣ መተናነስ፣ ማሸርገድ፣ መዋረድ ነው፦
22፥77 እናንተ ያመናችሁ ሰዎች ሆይ! በሶላታችሁ አጎንብሱ፣ "በግንባራችሁም ተደፉ"፣ ጌታችሁንም አምልኩ፣ ትድኑ ዘንድ መልካምን ነገር ሥሩ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا ارْكَعُوا وَاسْجُدُوا وَاعْبُدُوا رَبَّكُمْ وَافْعَلُوا الْخَيْرَ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ ۩
"በግንባራችሁም ተደፉ" ለሚለው የገባው የግሥ መደብ "ኢሥጂዱ" اسْجُدُوا ሲሆን በሶላት ውስጥ ያለው ሡዱድ ለአሏህ ብቻ የሚቀርብ ሡጁዱል ዒባዳህ ነው፥ የትም ሆነን ሁሉን ለሚችል፣ ሁሉን ለሚያውቅ፣ ሁሉን ለሚያይ፣ ሁሉን ለሚሰማ መለኮት የሚቀርብ ስግደት የአምልኮ ስግደት ነው። ፍጡራን ግን ሁሉንም የመቻል፣ የማወቅ፣ የማየት እና የመስማት ባሕርይ ስለሌላቸው ለእርሱ በሩቅ የሚቀርብ ስግደት ሺርክ ነው፦
35፥18 የምታስጠነቅቀው እነዚያን ጌታቸውን በሩቅ የሚፈሩትን፣ ሶላትንም አስተካክለው ያደረሱትን ብቻ ነው፡፡ إِنَّمَا تُنذِرُ الَّذِينَ يَخْشَوْنَ رَبَّهُم بِالْغَيْبِ وَأَقَامُوا الصَّلَاةَ
መላእክት፣ ነቢያት፣ ጻድቃን እና ሰማዕታት መለኮት ስላልሆኑ ሁሉን ቻይ፣ ሁሉን ዐዋቂ፣ ሁሉን ተመልካች እና ሁሉን ሰሚ ስላልሆኑ ለእነርሱ በሩቅ የሚቀርበው ስግደት ሺርክ ነው፦
4፥36 አሏህንም አምልኩ! በእርሱም ምንንም አታጋሩ፡፡ وَاعْبُدُوا اللَّهَ وَلَا تُشْرِكُوا بِهِ شَيْئًا
አምላካችን አሏህ ነባቢ መለኮት ነው፥ "እኔም ጌታችሁ ነኝና አምልኩኝ" ይለናል፦
21፥92 ይህቺ ኡማህ አንዲት ኡማህ ስትሆን በእርግጥ ኡማችሁ ናት፥ እኔም ጌታችሁ ነኝና አምልኩኝ፡፡ إِنَّ هَـٰذِهِ أُمَّتُكُمْ أُمَّةً وَاحِدَةً وَأَنَا رَبُّكُمْ فَاعْبُدُونِ
21፥25 ከአንተ በፊትም "እነሆ ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጂ ከመልእክተኛ አንድንም አልላክንም፡፡ وَمَا أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِي إِلَيْهِ أَنَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدُونِ
ከጥንት ጀምሮ "እነሆ ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት ነቢያትን ሲልክ የነበረውን አንዱን አምላክ አሏህ ማምለክ ምንኛ መታደል ነው? እናንተ ሰዎች ሆይ! ቅጣትን ትጠነቀቁ ዘንድ እናንተን እና እነዚያንም ከእናንተ በፊት የነበሩትን የፈጠረውን ጌታችሁን አምልኩ፦
2፥21 እናንተ ሰዎች ሆይ! ቅጣትን ትጠነቀቁ ዘንድ እናንተን እና እነዚያንም ከእናንተ በፊት የነበሩትን የፈጠረውን ጌታችሁን አምልኩ፡፡ يَا أَيُّهَا النَّاسُ اعْبُدُوا رَبَّكُمُ الَّذِي خَلَقَكُمْ وَالَّذِينَ مِن قَبْلِكُمْ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ
ክርስቲያኖች ሆይ! የአምልኮ ሐቅ ገንዘቡ የሆነውን አንዱን አምላክ አሏህን እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
18፥110 «በጌታውም "አምልኮ" አንድንም አያጋራ» በላቸው፡፡ وَلَا يُشْرِكْ بِعِبَادَةِ رَبِّهِ أَحَدًا
"ዒባዳህ" عِبَادَة የሚለው ቃል "ዐበደ" عَبَدَ ማለትም "አመለከ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "አምልኮ" ማለት ነው፦
18፥110 «በጌታውም "አምልኮ" አንድንም አያጋራ» በላቸው፡፡ وَلَا يُشْرِكْ بِعِبَادَةِ رَبِّهِ أَحَدًا
"ሡጁድ" سُجُود የሚለው ቃል "ሠጀደ" سَجَدَ ማለትም "ሰገደ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ስግደት" ማለት ነው፥ በጥቅሉ "ሡጁዱል ዒባዳህ" سُجُود الْعِبَادَة ማለት "የአምልኮ ስግደት" ማለት ነው፦
6፥56 «እኔ እነዚያን ከአሏህ ሌላ የምትጠሩዋቸውን ከማምለክ ተከልክያለሁ» በላቸው፡፡ قُلْ إِنِّي نُهِيتُ أَنْ أَعْبُدَ الَّذِينَ تَدْعُونَ مِن دُونِ اللَّهِ
7፥206 እነዚያ እጌታህ ዘንድ ያሉት መላእክት እርሱን ከማምለክ አይኮሩም፥ ያወድሱታልም፡፡ ለእርሱ ይሰግዳሉ፡፡ إِنَّ الَّذِينَ عِندَ رَبِّكَ لَا يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِهِ وَيُسَبِّحُونَهُ وَلَهُ يَسْجُدُونَ ۩
የባሕርይ ስግደት"Ontological Prostration" ለአንዱ አምላክ ብቻ የሚቀርብ የአምልኮ ስግደት ሲሆን ለአንዱ አምላክ ለአሏህ ብቻ የሚቀርብ መጎባደድ፣ መተናነስ፣ ማሸርገድ፣ መዋረድ ነው፦
22፥77 እናንተ ያመናችሁ ሰዎች ሆይ! በሶላታችሁ አጎንብሱ፣ "በግንባራችሁም ተደፉ"፣ ጌታችሁንም አምልኩ፣ ትድኑ ዘንድ መልካምን ነገር ሥሩ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا ارْكَعُوا وَاسْجُدُوا وَاعْبُدُوا رَبَّكُمْ وَافْعَلُوا الْخَيْرَ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ ۩
"በግንባራችሁም ተደፉ" ለሚለው የገባው የግሥ መደብ "ኢሥጂዱ" اسْجُدُوا ሲሆን በሶላት ውስጥ ያለው ሡዱድ ለአሏህ ብቻ የሚቀርብ ሡጁዱል ዒባዳህ ነው፥ የትም ሆነን ሁሉን ለሚችል፣ ሁሉን ለሚያውቅ፣ ሁሉን ለሚያይ፣ ሁሉን ለሚሰማ መለኮት የሚቀርብ ስግደት የአምልኮ ስግደት ነው። ፍጡራን ግን ሁሉንም የመቻል፣ የማወቅ፣ የማየት እና የመስማት ባሕርይ ስለሌላቸው ለእርሱ በሩቅ የሚቀርብ ስግደት ሺርክ ነው፦
35፥18 የምታስጠነቅቀው እነዚያን ጌታቸውን በሩቅ የሚፈሩትን፣ ሶላትንም አስተካክለው ያደረሱትን ብቻ ነው፡፡ إِنَّمَا تُنذِرُ الَّذِينَ يَخْشَوْنَ رَبَّهُم بِالْغَيْبِ وَأَقَامُوا الصَّلَاةَ
መላእክት፣ ነቢያት፣ ጻድቃን እና ሰማዕታት መለኮት ስላልሆኑ ሁሉን ቻይ፣ ሁሉን ዐዋቂ፣ ሁሉን ተመልካች እና ሁሉን ሰሚ ስላልሆኑ ለእነርሱ በሩቅ የሚቀርበው ስግደት ሺርክ ነው፦
4፥36 አሏህንም አምልኩ! በእርሱም ምንንም አታጋሩ፡፡ وَاعْبُدُوا اللَّهَ وَلَا تُشْرِكُوا بِهِ شَيْئًا
አምላካችን አሏህ ነባቢ መለኮት ነው፥ "እኔም ጌታችሁ ነኝና አምልኩኝ" ይለናል፦
21፥92 ይህቺ ኡማህ አንዲት ኡማህ ስትሆን በእርግጥ ኡማችሁ ናት፥ እኔም ጌታችሁ ነኝና አምልኩኝ፡፡ إِنَّ هَـٰذِهِ أُمَّتُكُمْ أُمَّةً وَاحِدَةً وَأَنَا رَبُّكُمْ فَاعْبُدُونِ
21፥25 ከአንተ በፊትም "እነሆ ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጂ ከመልእክተኛ አንድንም አልላክንም፡፡ وَمَا أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِي إِلَيْهِ أَنَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدُونِ
ከጥንት ጀምሮ "እነሆ ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት ነቢያትን ሲልክ የነበረውን አንዱን አምላክ አሏህ ማምለክ ምንኛ መታደል ነው? እናንተ ሰዎች ሆይ! ቅጣትን ትጠነቀቁ ዘንድ እናንተን እና እነዚያንም ከእናንተ በፊት የነበሩትን የፈጠረውን ጌታችሁን አምልኩ፦
2፥21 እናንተ ሰዎች ሆይ! ቅጣትን ትጠነቀቁ ዘንድ እናንተን እና እነዚያንም ከእናንተ በፊት የነበሩትን የፈጠረውን ጌታችሁን አምልኩ፡፡ يَا أَيُّهَا النَّاسُ اعْبُدُوا رَبَّكُمُ الَّذِي خَلَقَكُمْ وَالَّذِينَ مِن قَبْلِكُمْ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ
ክርስቲያኖች ሆይ! የአምልኮ ሐቅ ገንዘቡ የሆነውን አንዱን አምላክ አሏህን እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም