በአንድ ወቅት ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በአደባባይ በሚሰብክበት ጊዜ፣ አንድ ሌባ በህዝቡ መሃል እየተንቀሳቀሰ ነበር።
ሌባው ወደዚህ የመጣው ስብከቱን ለመሰማት ሳይሆን ከሰዎች ኪስ ለመስረቅ ነበር፡፡ ነገር ግን፣ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ መናገር ሲጀምር ሌባው በስብከቱ ተማርኮ ፈዞ ቆመ፥ የመጣበትንም የመጀመሪያ ዓላማውን ረሳው፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ ቃላት ማራኪ ከመሆናቸው የተነሳ የሌባወን ሕሊና በጥልቀት ነኩ።
ሌባው ስለ ንስሐ፣ ስለ ይቅርታ እና በጎ ሕይወት ከቅዱስ የሐንስ አፈወርቅ ከሰማ በኋላ የወንጀል ሕይወቱን ለመተው ወሰነ፡፡ ከስብከቱ በኋላ፣ ወደ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቀረበ ኃጢአቱንም ተናዘዘ፤ እናም መንገዱን እንዴት መለወጥ እንዳለበት ምክርን ጠየቀ። በርኀራኄው የሚታወቀው ቅዱስ ዮሐንስም ሌባውን ተቀብሎ አዲስ ሕይወት እንዲጀምር ረዳው፡፡
ይህ ታሪክ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስብከቶች ከየትኛውም ሕይወት የመጡ ሰዎችን፣ ከመልካም ምግባር የራቁትን ሳይቀር ወደ እግዚአብሔር መመለስ ለመቻላቸው ምስክር ነው።
ስብከቱ አእምሮአዊ ብቻ ሳይሆን ሕይወትን የሚለውጥ፣ የአድማጮቹን ልብ የሚነካና መልካም ሕይወት እንዲመሩ የሚያደርግም ነው።
ሌባው ወደዚህ የመጣው ስብከቱን ለመሰማት ሳይሆን ከሰዎች ኪስ ለመስረቅ ነበር፡፡ ነገር ግን፣ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ መናገር ሲጀምር ሌባው በስብከቱ ተማርኮ ፈዞ ቆመ፥ የመጣበትንም የመጀመሪያ ዓላማውን ረሳው፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ ቃላት ማራኪ ከመሆናቸው የተነሳ የሌባወን ሕሊና በጥልቀት ነኩ።
ሌባው ስለ ንስሐ፣ ስለ ይቅርታ እና በጎ ሕይወት ከቅዱስ የሐንስ አፈወርቅ ከሰማ በኋላ የወንጀል ሕይወቱን ለመተው ወሰነ፡፡ ከስብከቱ በኋላ፣ ወደ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቀረበ ኃጢአቱንም ተናዘዘ፤ እናም መንገዱን እንዴት መለወጥ እንዳለበት ምክርን ጠየቀ። በርኀራኄው የሚታወቀው ቅዱስ ዮሐንስም ሌባውን ተቀብሎ አዲስ ሕይወት እንዲጀምር ረዳው፡፡
ይህ ታሪክ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስብከቶች ከየትኛውም ሕይወት የመጡ ሰዎችን፣ ከመልካም ምግባር የራቁትን ሳይቀር ወደ እግዚአብሔር መመለስ ለመቻላቸው ምስክር ነው።
ስብከቱ አእምሮአዊ ብቻ ሳይሆን ሕይወትን የሚለውጥ፣ የአድማጮቹን ልብ የሚነካና መልካም ሕይወት እንዲመሩ የሚያደርግም ነው።