የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሊግ ካምፓኒውን ውሳኔ አገደ
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ አክስዮን ማህበር ያሳለፈውን ውሳኔ ማገዱን ይፋ አድርጓል።
አራት ክለቦች እና ሰባት ተጨዋቾች የይግባኝ አቤቱታ ማስገባታቸውን ተከትሎ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ውሳኔውን በይደር እንዲቆይ ውሳኔ አሳልፏል።
ፌዴሬሽኑ የቅጣት ውሳኔውን እና የቀረበውን አቤቱታ መርምሮ ውሳኔ ለማሳለፍ ጊዜ በማስፈለጉ ምክንያትም
የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ አክስዮን ማህበር ያሳለፈው ውሳኔ ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ መርምሮ ተገቢውን ውሳኔ እስኪሰጥ ሳይፈፀም ታግዶ እንዲቆይ ትህዛዝ ተሰጥቷል።
ከዚህ በተጨማሪም አክስዮን ማህበሩ ተጨዋቾች እና ክለቦችን ለመቅጣት ያስቻለውን ሰነድ ለኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፅህፈት ቤት በአምስት ቀናት ውስጥ እንዲያቀርብ ታዟል።
#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ አክስዮን ማህበር ያሳለፈውን ውሳኔ ማገዱን ይፋ አድርጓል።
አራት ክለቦች እና ሰባት ተጨዋቾች የይግባኝ አቤቱታ ማስገባታቸውን ተከትሎ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ውሳኔውን በይደር እንዲቆይ ውሳኔ አሳልፏል።
ፌዴሬሽኑ የቅጣት ውሳኔውን እና የቀረበውን አቤቱታ መርምሮ ውሳኔ ለማሳለፍ ጊዜ በማስፈለጉ ምክንያትም
የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ አክስዮን ማህበር ያሳለፈው ውሳኔ ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ መርምሮ ተገቢውን ውሳኔ እስኪሰጥ ሳይፈፀም ታግዶ እንዲቆይ ትህዛዝ ተሰጥቷል።
ከዚህ በተጨማሪም አክስዮን ማህበሩ ተጨዋቾች እና ክለቦችን ለመቅጣት ያስቻለውን ሰነድ ለኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፅህፈት ቤት በአምስት ቀናት ውስጥ እንዲያቀርብ ታዟል።
#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews