EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Tibbiyot


ETHIOPIAN FOOD AND DRUG AUTHORITY /EFDA/
This is EFDA'S official Telegram Channel
For more updates please visit
Free call 8482
join the Channel
t.me/ethiopianfoodanddrugauthority

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri








ከደረጃ በታችና የተጭበረበሩ መድኃኒቶችን ለመከላከል የባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ

በአዳማ ከተማ በተካሄደው የባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ ላይ በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ምግብን መድኃኒት ባለስልጣን የመድኃኒት ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ስዩም ወልዴ እንደተናገሩት የአለም ጤና ድርጅት በ2017 ባወጣው ጥናት መሰረት በታዳጊ ሀገራት ከ10 መድኃኒቶች አንዱ ከደረጃ በታችና የተጭበረበሩ እንደሆኑ ገልፀው ችግሩን ለመፍታት ከፍተኛ የሆነ አለም አቀፋዊ ትብብር፣ የግንዛቤ ማስጨበጫና ያላሰለሰ ስራ  እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል።

ባለስልጣኑ ከደረጃ በታችና የተጭበረበሩ መድኃኒቶች ቁጥጥር ጋር በተያያዘ የድርጊት መርኃ ግብር ማዘጋጀቱን ገልፀው ጉዳይ የተወሰኑ ተቋማትን ትብብር ብቻ ሳይሆን የሁሉንም አካላትና አለም አቀፋዊ ትብብርን የሚጠይቅ መሆኑን ገልፀው ባለስልጣኑ ለሁሉም መድኃኒቶች ልዩ መለያ ኮድ ለመጠቀም ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በተዘጋጀው የድርጊት መርኃ ግብር ላይ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች፣ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ ኢንተርፖል፣ ጉምሩክ ኮሚሽን፣  የሙያ ማህበራት፣ የፍትህ አካላት፣ የመድኃኒት አምራቾችና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ውይይት ውጤታማ ያደረጉ ሲሆን ከተሳታፊዎች በተነሱ አስተያየቶች መሰረት የተዘጋጀው የድርጊት መርኃ ግብር የባለድርሻ አካላትን አስተያየት መሰረት አድርጎ በቅርቡ ወደስራ ይገባል ተብሎ ይጠበቃል።

4 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.