ከአዲስ አበባ የሚወጡ 4 የፍጥነት መንገዶች ለመገንባት ጥናት እየተደረገ ይገኛል
ከአዲስ አበባ በተለያዩ መስመሮች የሚወጡ 4 አዳዲስ የፍጥነት መንገዶችን ለመገንባት የሚያስችል ጥናት እየተደረገ ይገኛል፡፡
ከአዲስ አበባ ደሴ ፣
ከአዲስ አበባ ጅማ ፣
ከአዲስ አበባ ደብረማርቆስ እና
ከአዲስ አበባ ነቀምት በሚዘልቁት መንገዶች ላይ ነው፡፡
አራቱን የፍጥነት መንገዶች ለመገንባት የሚያስፈልገው ወጪ የሚሸፈነው በመንግስትና የግል አጋርነት ትብብር ነው፡፡
ከፍጥነት መንገዶቹ መካከል የአዲስ ጅማ እና አዲስ ደብረ ማርቆስ ፕሮጀክቶች ለገንዘብ ሚኒስቴር የመንግስት የግል አጋርነት ቦርድ የቀረቡ ሲሆን ቀሪዎቹም በቅርቡ ይቀርባሉ ተብለው ይጠበቃል ።
ፕሮጀክቶቹም በገንዘብ ሚኒስቴር የመንግስት የግል አጋርነት ትብብር ቦርድ ከጸደቁ በኋላ ወደ ቀጣይ ስራ ይገባሉ።
ከአዲስ አበባ በተለያዩ መስመሮች የሚወጡ 4 አዳዲስ የፍጥነት መንገዶችን ለመገንባት የሚያስችል ጥናት እየተደረገ ይገኛል፡፡
ከአዲስ አበባ ደሴ ፣
ከአዲስ አበባ ጅማ ፣
ከአዲስ አበባ ደብረማርቆስ እና
ከአዲስ አበባ ነቀምት በሚዘልቁት መንገዶች ላይ ነው፡፡
አራቱን የፍጥነት መንገዶች ለመገንባት የሚያስፈልገው ወጪ የሚሸፈነው በመንግስትና የግል አጋርነት ትብብር ነው፡፡
ከፍጥነት መንገዶቹ መካከል የአዲስ ጅማ እና አዲስ ደብረ ማርቆስ ፕሮጀክቶች ለገንዘብ ሚኒስቴር የመንግስት የግል አጋርነት ቦርድ የቀረቡ ሲሆን ቀሪዎቹም በቅርቡ ይቀርባሉ ተብለው ይጠበቃል ።
ፕሮጀክቶቹም በገንዘብ ሚኒስቴር የመንግስት የግል አጋርነት ትብብር ቦርድ ከጸደቁ በኋላ ወደ ቀጣይ ስራ ይገባሉ።