ማስታወቂያ
ጉዳዩ፡- የብሄራዊ ድህረ-ምረቃ (NGAT) መግቢያ ፈተና እና ምዝገባ ቀናት የተራዘሙ መሆኑን ስለማሳወቅ
በ2017 ዓ.ም የሶስተኛ ዙር የNGAT አመልካቾች ምዘገባ መጋቢት 01/2017 መጠናቀቁ እና ፈተናው መጋቢት 05/2017 ከ3፡00 ጀምሮ እንደሚሰጥ መገለጹ ይታወሳል። ይሁን እንጂ በአንዳንድ ተፈታኞች ጥያቄ መሰረት ምዝገባው እስከ መጋቢት 04/2017 ዓ.ም እስከ ምሽቱ 12:00 የተራዘመ ሲሆን ፈተናው ደግሞ መጋቢት 12/2017 ከ3:00 ጀምሮ ይሰጣል።
በዚሁ መሰረት በተለያየ ምክንያት ምዝገባ ያመለጣችሁ አመልካቾች ምዝገባችሁን ቀደም ሲል በተገለጸው ሊንክ በመግባት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ፈተናውን ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ስዓት በምትመደቡበት የፈተና ማዕከላት ተገኝታችሁ እንድትፈተኑ እናሳስባለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
1. ተፈታኞች ወደ ፈተና ማዕከል በምትሄዱበት ወቅት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡
2. ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከመጀመሩ 30 ደቂቃ በፊት በፈተና ማዕከል መገኘት ይጠበቅበታል፡፡
3. የሞባይል ስልክ ይዞ በፈተና ማዕከል መገኘት ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
4. የፈተና ማዕከላት ምደባ በምዝገባ ፕላትፎርም የሚገለጽ ይሆናል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር
ጉዳዩ፡- የብሄራዊ ድህረ-ምረቃ (NGAT) መግቢያ ፈተና እና ምዝገባ ቀናት የተራዘሙ መሆኑን ስለማሳወቅ
በ2017 ዓ.ም የሶስተኛ ዙር የNGAT አመልካቾች ምዘገባ መጋቢት 01/2017 መጠናቀቁ እና ፈተናው መጋቢት 05/2017 ከ3፡00 ጀምሮ እንደሚሰጥ መገለጹ ይታወሳል። ይሁን እንጂ በአንዳንድ ተፈታኞች ጥያቄ መሰረት ምዝገባው እስከ መጋቢት 04/2017 ዓ.ም እስከ ምሽቱ 12:00 የተራዘመ ሲሆን ፈተናው ደግሞ መጋቢት 12/2017 ከ3:00 ጀምሮ ይሰጣል።
በዚሁ መሰረት በተለያየ ምክንያት ምዝገባ ያመለጣችሁ አመልካቾች ምዝገባችሁን ቀደም ሲል በተገለጸው ሊንክ በመግባት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ፈተናውን ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ስዓት በምትመደቡበት የፈተና ማዕከላት ተገኝታችሁ እንድትፈተኑ እናሳስባለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
1. ተፈታኞች ወደ ፈተና ማዕከል በምትሄዱበት ወቅት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡
2. ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከመጀመሩ 30 ደቂቃ በፊት በፈተና ማዕከል መገኘት ይጠበቅበታል፡፡
3. የሞባይል ስልክ ይዞ በፈተና ማዕከል መገኘት ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
4. የፈተና ማዕከላት ምደባ በምዝገባ ፕላትፎርም የሚገለጽ ይሆናል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር