#ቅድስት
"ይህ መልእክት ለቅዱሳን ወንድሞች ሁሉ እንዲነበብ በጌታ አምላችኋለሁ"
1.ተሰ 5፥27
የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት ቅድስት ተብሎ የሚጠራ መሆኑ ይታወቃል!
ቅድስት በሚል ቅጽል የሚጠሩት፦
1. ሥላሴ
2. እመቤታችን
3. ጾም
4. ሰንበት
5. ቤተ ክርስቲያን
6. ነፍስ
7. መንፈስ ናቸው
ቅድስት ማለት 👉 ንጽሕት ክብርት ጽንእት ልዩ ማለት ነው።
ምሥጢሩ መለኮታዊ ቅድስናን የምንካፈልበት ጥግ የሚነገርበት ነው
በጣም ከፍተኛው የትምህርትም የሕይወትም ደረጃ ነው!
ልዕልና ነፍስ/የነፍስ ከፍታ የሚገኝበት
የመንፈስ ዕርገት/ንጥቀት/ምጥቀት/ርቀት
የሥጋ ንጽሕና የሚነገርበት ሳምንት ነው።
እግዚአብሔር ባህርያዊ ቅድስናውን በጸጋ እንዳካፈለን አውቀን ቸርነቱን የምናደንቅበት፤ ቸር መሆንን የምንለማመድበት ሳምንት ነው።
"እንግዲህ እንደ እግዚአብሔር ምርጦች ቅዱሳን ሆናችሁ የተወደዳችሁም ሆናችሁ፥ ምሕረትን፥ ርኅራኄን፥ ቸርነትን፥ ትህትናን፥ የዋህነትን፥ ትዕግሥትን ልበሱ" ፣ ቆላ 3 ፥12።
ቅድስና ማለት ከእግዚአብሔር ጋር መጣበቅ ማለት ነው
ይህም ሱታፌ ሥላሴ ወይም ኅብረተ ሥላሴ ወይም እግዚአብሔርን የመምሰል (Theosis) መደምደሚያ ነው።
የጸጋ አምላክነት/የጸጋ እግዚአብሔርነት ይገኝበታል!
ቅድስና በሂደት የሚገኝ እንደ እሳት እየተቀጣጠለ እንደ ነበልባል ወደ ሰማይ የሚያምዘገዝግ ሃይማኖታዊ ኃይል ነው!
የክርስትና ማብቂያው ይህን የቅድስና ሕይወት መለማመድ፣ማደግና በመጨረሻም ፍጹም በመሆን መዳን ነው።
"ዳሩ ግን። እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁኑ ተብሎ ስለ ተጻፈ የጠራችሁ ቅዱስ እንደ ሆነ እናንተ ደግሞ በኑሮአችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ"
1ኛ ጴጥ1፥15-16።
ስለ ክፉ ምኞት በዓለም ካለው ጥፋት አምልጣችሁ ከመለኮት ባሕርይ ተካፋዮች በተስፋ ቃል እንድትሆኑ፥ በእነዚያ ክብርና በጎነት የተከበረና እጅግ ታላቅ የሆነ ተስፋን ሰጠን።
በበጎነትም እውቀትን፥ በእውቀትም ራስን መግዛት፥ ራስንም በመግዛት መጽናትን፥ በመጽናትም እግዚአብሔርን መምሰል"
2ኛ ጴጥ 1፥4&6
በተቀደሰ ሕይወት እንድንመላለስ የቅዱሳን አምላክ ቅዱስ እግዚአብሐር ይርዳን!!!
አሜን
ሠናይ ሰንበት!
ከመጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ ከፍያለው
"ይህ መልእክት ለቅዱሳን ወንድሞች ሁሉ እንዲነበብ በጌታ አምላችኋለሁ"
1.ተሰ 5፥27
የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት ቅድስት ተብሎ የሚጠራ መሆኑ ይታወቃል!
ቅድስት በሚል ቅጽል የሚጠሩት፦
1. ሥላሴ
2. እመቤታችን
3. ጾም
4. ሰንበት
5. ቤተ ክርስቲያን
6. ነፍስ
7. መንፈስ ናቸው
ቅድስት ማለት 👉 ንጽሕት ክብርት ጽንእት ልዩ ማለት ነው።
ምሥጢሩ መለኮታዊ ቅድስናን የምንካፈልበት ጥግ የሚነገርበት ነው
በጣም ከፍተኛው የትምህርትም የሕይወትም ደረጃ ነው!
ልዕልና ነፍስ/የነፍስ ከፍታ የሚገኝበት
የመንፈስ ዕርገት/ንጥቀት/ምጥቀት/ርቀት
የሥጋ ንጽሕና የሚነገርበት ሳምንት ነው።
እግዚአብሔር ባህርያዊ ቅድስናውን በጸጋ እንዳካፈለን አውቀን ቸርነቱን የምናደንቅበት፤ ቸር መሆንን የምንለማመድበት ሳምንት ነው።
"እንግዲህ እንደ እግዚአብሔር ምርጦች ቅዱሳን ሆናችሁ የተወደዳችሁም ሆናችሁ፥ ምሕረትን፥ ርኅራኄን፥ ቸርነትን፥ ትህትናን፥ የዋህነትን፥ ትዕግሥትን ልበሱ" ፣ ቆላ 3 ፥12።
ቅድስና ማለት ከእግዚአብሔር ጋር መጣበቅ ማለት ነው
ይህም ሱታፌ ሥላሴ ወይም ኅብረተ ሥላሴ ወይም እግዚአብሔርን የመምሰል (Theosis) መደምደሚያ ነው።
የጸጋ አምላክነት/የጸጋ እግዚአብሔርነት ይገኝበታል!
ቅድስና በሂደት የሚገኝ እንደ እሳት እየተቀጣጠለ እንደ ነበልባል ወደ ሰማይ የሚያምዘገዝግ ሃይማኖታዊ ኃይል ነው!
የክርስትና ማብቂያው ይህን የቅድስና ሕይወት መለማመድ፣ማደግና በመጨረሻም ፍጹም በመሆን መዳን ነው።
"ዳሩ ግን። እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ሁኑ ተብሎ ስለ ተጻፈ የጠራችሁ ቅዱስ እንደ ሆነ እናንተ ደግሞ በኑሮአችሁ ሁሉ ቅዱሳን ሁኑ"
1ኛ ጴጥ1፥15-16።
ስለ ክፉ ምኞት በዓለም ካለው ጥፋት አምልጣችሁ ከመለኮት ባሕርይ ተካፋዮች በተስፋ ቃል እንድትሆኑ፥ በእነዚያ ክብርና በጎነት የተከበረና እጅግ ታላቅ የሆነ ተስፋን ሰጠን።
በበጎነትም እውቀትን፥ በእውቀትም ራስን መግዛት፥ ራስንም በመግዛት መጽናትን፥ በመጽናትም እግዚአብሔርን መምሰል"
2ኛ ጴጥ 1፥4&6
በተቀደሰ ሕይወት እንድንመላለስ የቅዱሳን አምላክ ቅዱስ እግዚአብሐር ይርዳን!!!
አሜን
ሠናይ ሰንበት!
ከመጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ ከፍያለው