Let's Save Orthodoxy and humanity( ሰብእናንና ኦርቶዶክሳዊነትን እንታደግ)!!⁉️


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


ሰብእናንና የመንፈስ ልዕልናን ካዳበሩ ቤተሰቦች ጋር በመተባበር በሰብእናና በኦርቶዶክሳዊነት ላይ የሚፈጸምን(የተፈጸመን) ሥርዓታዊ፣መዋቅራዊ፣ሕጋዊ፣መናፍስታዊ፣ስነልቦናዊ ..ጥቃቶችንና አጥቂዎችን እንዲሁም ከጥቃት የመዳኛ መንገዶችን(መፍትሔ) የሚመለከትበት ቻናል ነው::

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


ያልተሰሙ_ድምጾች dan repost
ዘግይቶ የደረሰኝ መረጃ  
                                                                                                                               የኦርቶዶክሳዉያን መታረጃ ቄራ በ ሆነችዉ በ ኦሮሚያ ምድር ኦርቶድካዉያንን ከምድረ ገጽ የማጥፋት ሰይጣናዊ ተግባር ተባብብሶ እንደቀጠለ ነዉ። በምሥራቅ አርሲ ዞን ጠና ወረዳ በቀቅሳ የሚባል ቦታ ላይ ሁለት ኦርቶዶክሳዉያን (አባትና ልጅ) በመጥረቢያ እንገታቸዉ ተቀልቶ መገደላቸዉን ነዋሪዎቹ ተናገሩ።ድርጊቱ የተፈጸመዉ በዕለተ ረቡዕ(የካቲት 27/2017ዓ/ም) ሲሆን የድርጊቱ ፈጻሚዎች "ካፊሮችን(ክርስቲያኖችን) ማረድና መግደል ጅነትን ያወርሰናል" ብለዉ የሚያምኑ ጽንፈኛና አክራሪ ወሀቢያ እስላሞች መሆናቸዉንም ተናግረዋል።ሰቆቃችንን የምናሳዉቅበት ተቁምና አካል በማጣታችን እንጂ ያለ መከራ ዉለን ያደርንበት አንድም ቀን የለም ሲሉ የመረረ ሀዘናቸዉን ተናግረዋል።


ነገር ግን፥ወንድሞች ሆይ
እናንተ የተማራችሁትን ትምህርት የሚቃወሙትን መለያየትንና ማሰናከያን የሚያደርጉትን ሰዎች እንድትመለከቱ እለምናችኋለሁ ፥ ከነርሱ ዘንድ ፈቀቅ በሉ፤
እንዲህ ያሉት ለገዛ ሆዳቸው እንጂ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ አይገዙምና ፥በመልካምና በሚያቈላምጥ ንግግርም ተንኰል የሌለባቸውን ሰዎች ልብ ያታልላሉ ። ሮሜ16:17-18


ታጣቂዎች አንድ ሰው ገድለው፤ ቤቶች አቃጥለው ስምንት ሰዎች አፍነው ወስደዋል!

የክስታኔ ጉራጌ (በተለምዶ የሶዶ ጉራጌ) ከኦሮሚያ ክልል በሚያዋሰንባቸው አካባቢዎች ከኦሮሚያ ክልል በሚመጡ ታጣቂዎች (ኦነግ ሸኔ) ተደጋጋሚ ጥቃትና ዘረፋ እንደሚፈፀም ተገለፀ። ባለፉት አራት አመታት በእነዚ አካባቢ በመሸጉ ታጣቂዎች የዜጎች ሰላምና ደህንነት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ተብሏል።

ነዋሪው በሰላም ሰረቶ መግባት፤ በነፃነት አምርቶ መሰብሰብ ቅንጦት እየሆነ ነው ብለዋል። አካባቢው በኮማንድ ፖስት የሚመራ ቢሆንም ሰላም ማምጣት አልተቻለም፤ በየጊዜው የሰላም ማስፈን ውይይቶች የሚያደረጉት የፀጥታ ሀይሎችም ተጨባጭ ለውጥ በአካባቢው ማስፈን አንዳልቻሉ ተናግረዋል። የመከላከያ ሀይል ጥቃትና ዝርፍያ ከተፈፀመ በኋላ ከመምጣት ውጪ የዜጎች የየቀኑ ደህንነትና በሰላም መንቀሳቀስ ማረጋገጥ አለመቻሉን አንስተዋል።

በቅርብ ከአንድ ወር በፊት የማዕከላዊ ክልል የፀጥታ አመራሮችና የአጎራባች ኦሮሚያ ክልል የፀጥታ ሀይሎች በጋራ የሰላም ውይይት በሚል በቡታጀራ መደረጉን የሚገለፁት ምንጫችን፤ ውይይቱ ለይስሙላ ሆኖ በቦኖ አይገዶ ቀበሌ ስምንት የቀበሌው ነዋሪዎች በታጣቂዎች ተወስደዋል ብለዋል።

ታጣቂዎች ተደጋጋሚ ጥቃትና ዘርፋ የሚፈፅሙባቸው፤ አማውንቴ ሞረጌ ቀበሌ፣ ገሬኖ እንስት ተክል ቀበሌና ቦኖ አይገዶ ቀበሌ መሆናቸው እየታወቀ ህዝቡ ተደጋጋሚ ቅሬታ እያቀረበ መፍትሄ ማጎኘት እንዳልተቻለ ተናግረዋል።

ከቦኖ አይገዶ የተወሰዱ 8 ሰዎች እስከ 600,000 እየተጠየቁ መሆኑ በመግለፅ አንዳንድ የታጋቾች ቤተሰብ ገንዘብ ልመና ወደ አዲስ አበባ መሄዳቸውን ገልፀዋል። በኮማንድ ፖስት የሚመሩት እነዚህ ቀበሌዎች ተደጋጋሚ ጥቃት፣ ዘረፋና የሰዎች እገታ እንደሚፈፀም መረጃ ሰጪው አንስተዋል።

ከዚህ በተጨማሪ በአይመለል ቀበሌ ቅዳሜ የካቲት 29 2017 ዓ.ም ከኦሮማያ ክልል በመጡ ታጣቂዎች አንድ ሰው ሲገደል፤ አራት የገበሬ ቤቶች ተቃጥለዋል። ጥቃት ከተፈፀመበት ቀበሌ ታጣቂዎቹ ሰዎች ለመውሰድ ያደረጉት ጥረት በአካባቢው ነዋሪዎች ብርቱ ጥረት መክሸፉን ገልፀዋል። በጥቃቱ የተገደሉት አቶ አሸብር ብረሐኑ የተባሉ በጣም ታዋቂ በተደጋጋሚ የታጣቂዎች ጥቃት ሲመክቱ የነበሩ፤ ለአካባቢው ከፍተኛ መስዋት ሲከፍሉ የነበሩ ናቸው ብለዋል ምንጫችን። ጥቃቱ ከተፈፀመ በኋላ የመከላከያ ሀይል ወደ ቦታ መግባቱ ምንጫችን ጨምረው ገልፀዋል።

በዚሁ በሶዶ ወረዳ ዳጮ ሀሙስ ገበያ ቀበሌ ዜጎች የታጣቂዎች ጥቃት ሰግተው ወደ ቡዪ ከተማ እየተሰደዱ መሆናቸው ተገልፆል። ትልልቅ የእርሻ ማሳ ያላቸው ባለሀብቶች ሳይቀር ለደህንነታቸው ሲሉ ወደ ከተማ መሄዳቸው ተገልፆል። ይህ አካባቢ ቀደም ሲል ከ30 በላይ ዜጎች የተገደሉበት ከዱግዳ ወረዳ በቅርብ እርቀት እንደሚገኝም ተገልፆል።

ከግዮን አማራ ገጽ




የአብነት መምህሩና ተማሪዎቻቸው ጭፍጨፋ የሥርዓቱ ሃይማኖት ጠልነት ማሳያ ነው!

-በራያ በመንግስት ኃይሎች የተፈፀመውን ጭፍጨፋ አስመልክቶ ከእናት ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ

በራያ አላማጣ ወረዳ፣ጥሙጋ ቀበሌ፣ ጥሙጋ ኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን ሥር የሚገኙ አረጋዊ የአብነት መምህርና ተማሪዎቻቸው በጭካኔ ተረሽነዋል። የሰባ ሦስት ዓመቱ የኔታ ገብረ መድኅን በአካባቢው የታወቁና የተከበሩ የድጓ ሊቅ፣ በአገር ደረጃ በርካታ ደቀ መዛሙርትንም ያፈሩ ነበሩ። የካቲት ፳፯ ቀን ሐሙስ ለአርብ አጥቢያ ወንበር ዘርግተው ማስተማር እንደጀመሩ ወደ ፲ ሰዓት ከ ፵ ደቂቃ ላይ ያልታሰበ እሩምታ ተኩስ ተጀመረ ይላሉ ኹኔታውን በቅርበት የተከታተሉ እማኝ።

እሩምታው እንደቆመ ፈራ ተባ እያልን ለማረጋገጥ ወደ አብነት ትምህርት ቤቱ ስንደርስ ዘጠኙ መሬት ላይ ወድቀዋል። በዚኽም መምህሩና ሦስት ተማሪዎቻቸው ወዲያው ሲሞቱ አምስቱ ደግሞ ክፉኛ ቆስለዋል። ከቆስሉት ተማሪዎች መካከል አንዱ ከጊዜ በኋላ ሕይወቱ አልፏል። የመንግሥት የፀጥታ ኃይል የደንብ ልብስ የለበሱ ያሏቸው ሰዎች መጥተው ‘ስንት ሰው እንደሞተ አረጋግጣችሁ ንገሩን፣ መረጃውን ግን ለማንም ብትናገሩ እንገላችኋለን’ እያሉ እንደዛቱ ለመገንዘብ ችለናል። በዚኽም ግድያው ኾን ተብሎና ታቅዶ ለመደረጉ ፍንጭ ይሰጣል።

በደረሰን መረጃ መምህሩ ማየት የተሳናቸው ናቸው። በዛሬው ዕለትም በአጥቢያው ሥር የሚገኘው ኹለተኛው የአብነት ትምህርት ቤት አራት ቤቶች ቃጠሎ ተከስቷል። ፓርቲያችን እንዲኽ ያለውን የጭካኔ ተግባር በጽኑ የሚያወግዘው ሲኾን የብልጽግና መንግሥት በቀጥታም ይኹን በተዘዋዋሪ ማንነትና ሃይማኖት ተኮር የዘር ጭፍጨፋዎች እንዲፈጸሙ ያደርጋል ወይም እንዳላየ ያልፋል በሚል በተደጋጋሚ ስንገልጽ ኖረናል።

ድርጊቱ መፈጸሙ ተገልጾ በይፋ አለመወገዙና የድርጊቱ ፈጻሚዎች ላይ እርምጃ ለመውሰድ እንቅስቃሴ ስለመደረጉ ምንም ፍንጭ አለመኖሩ  ድርጊቶቹ በዓላማ የሚፈጸሙ መኾናቸውን ማሳያ እንደሆነ ፓርቲያችን ያምናል። ታሪክ እንደሚነግረን በዓለም ላይ የሚፈጸሙ ዘር ጭፍጨፋዎች መንግሥታዊ መዋቅርን የተከተሉና በማስተባበያ(denial) የታጀቡ ናቸው። 

በዚኹ አጋጣሚ ጭፍጨፋው በአገር ውስጥና ዓለምአቀፍ ገለልተኛ አካላት እንዲጣራ ውጤቱም ለሕዝብ ይፋ እንዲደረግ የድርጊቱ ፈጻሚዎችም ለሕግ እንዲቀርቡ ግፊትና ጥረታችንን እንደምንቀጥል እየገለጽን ለሟቾች እረፍተ ነፍስን ለቤተሰቦቻቸውና እንዲኽ ዓይነቱን ሊቅና ምልክት ላጣው ለመላ የእምነቱ ተከታይ ደግሞ መጽናናትን እንመኛለን።

እግዚአብሔር አገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ!

እናት ፓርቲ
መጋቢት ፪ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ


እምየ ተዋህዶ Emye Tewahedo dan repost
#መምህር_ፅጌ_አስተርአየ_እንደ_ጻፉት ...
.........✍️ ጅራፍ እና የፈሲታ ተቆጢታ" ✍️

ጅራፍ ራሱ ገርፎ ራሱ ይጮሃል።
የፈሲታ ተቆጢታም ራሱ አጩሆ ራሱ ይቆጣል።

የፈሲታ ተቆጢታ መሆን አሳፋሪ ነው ።

➾ ..... መታገስ መፍራት አይደለም።........✍️


➾ ➾➾ ይድረስ ለእስልምና ተከታዮች ወገኖቻችን "
እኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተካታዮች ለእናንተ ለወንድሞቻችን አክብሮት እና አፍቅሮት እንዳለን ኢትዮጵያ ሀገራችን ምስክር ናት። የታሪክ መዛግብቶቻችንም የተገለጡ ምስክሮች ናቸው። እንደ ሀገር ኢትዮጵያ የጋራ ሀገራችን ናት ።ይህንን እናምናለን። የጋራ ሀገር ባደረግናት ኢትዮጵያ በጋራ ኑረናል።በጋራም እየኖርን ነው።በጋራም እንኖራለን። አንዱ ልጅ አንዱ የእንጀራ ልጅ መሆን የለበትም የሚለውን ይህንን እኛም እናምናለን። ምናልባት አሁን ይህንን ተግባር እያስሄዱ ያሉ ነጋሽ ቤተ እምነቶችም ያስተውሉ። ምክንያቱም ነገ ሌላ ቀን ነው ። አንድ "ነገር ግን እንተማመን ። ታሪክ ታሪክ ነው። የኢትዮጵያ ቤ/ክርስቲያን በኢትዮጵያ ላሉ ቤተ እምነቶች በሙሉ ኢትዮጵያን በመሥራት እና ሠርታ በማካፈል ብቸኛዋ እና ወደር አልባዋ ቤተ እምነት ናት ።
◊➾እንደ ታሪካችን እንቀጥል። ታናሽ ወንድም ከታላቅ ወንድሙ በላይ ገዘፍኩ ።ወፈርኩ ቢልም እንኳን ታላቅ ወንድም ግን መሆን አይችልም።ይህንን ለመሆን እንደገና መወለድን ይጠይቃል።ይህ ደግሞ መቼም ሊሆን አይችልም። ታናሹም በታናሽነቱ ጸንቶ ራሱን ያበርታ። ታላቁም በታላቅነቱ ጸንቶ ታላቅነቱን ያበርታ። ኦርቶ ዶክስ አክባሪ ናት። ኦርቶ ዶክስ ወዳጅም ናት። ኦርቶዶክስ ስደተኛ ተቃባይ ናት። ለዚህ ደግሞ ሙሐመድ ምስክር ነው። በእንግዳነት እና በስደት የመጣ አካል የትኛውንም ያህል ለማዳ ቢሆን መነሻውን ግን መዘንጋት የለባትም። የኢትዮጵያ ቤ/ክርስቲያን በግድ አታሳምንም። በግድ የሚታመን አምላክም የላትም። በግድ የሚመለክ ጌታም ኑሯት አያውቅም። የሚገርመው መቼም አይኖራትም ።

➾ ሌሎች ቤተ እምነቶች በዚህ ልክ መብዛት የቻሉትም ኦርቶዶክስ ዓለምን በነጻ ፈቃድ የሚመራ ጌታ የመሠረታት ቤተ እምነት ስለሆነች ነው። እንጅ ሁሉም ቤተ እምነ ቶች" ወደ ኢትዮጵያ ሲገቡ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የቤተ መንግሥቱ እመቤት ነበረች። ሁሉንም ማድረግ ትችል ነበር። የሚመለሰውን መመለስ '' የሚከሰሰውን መክሰስ የሚታነጸውን ማነጽ፥ የሚፈርሰውን ማፍረስ ትችል ነበር ።ይህንን ግን አላደረገችውም። ምክንያቱ ደግሞ ኦርቶዶክስ የፍቅር ሃይማኖት ናት። ምናልባት ያለፉ ታሪኮችን በማንሳት መወቃቀሱ ጠቃሚ አይመስለኝም።ይህም ቢሆን እኛ ኦርቶዶክሳውያን የምናፍርበት ታሪክ የለንም ።ብዙ ጊዜ አጼ ዮሐንስ እንዲህ አደረጉ እየተባለ ይወራል። ተዉ አንጅ? እኛስ ? ግራኝ መሐመድ ምድራችን እንዳወደመ እንድንነግራችሁ ፈልጋችሁ ይሆንን ?እንከባበር እንጅ።ስንከባበር ነው የሚያምርብን።

የእኛ መምህራን " መጻሕፍትን ያለ ስም ያሳትማሉ የእናንተ ኡስታዞች ፈጣሪያችን ዘግናኝ ስድብ ሰድበው በአደባባይ መጻሕፍት ያሰራጫሉ። ይሄ ለምን ይመስላችኋል ? ምን እንደሆናችሁ አስባችሁት ይሆን?

➾የእኛ መምህራን ከኡስታዞቻችሁ ጋራ በሶሻል ምድያው ክርክር ሲያደርጉ ፊታቸውን ተሸፍነው ይከራከራሉ ።የእናንተ በአደባባይ ተገልጠው ሃይማኖታቸን ያረክሳሉ ።ይሄ ለምን ይምስላችኋል ?
የእኛ መምህራን በእስልምና ዙሪያ መጽሐፍ አሳትመው ገበያ ላይ እንዳይውል ተደርጎባቸዋል ።ዛቻ እና ማስፈራሪያ ተደርጎባቸዋል። የእናንተ ኡስታዞች በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ በእናታችን በድንግል ማርያም ላይ በመጽሐፍም በቃልም ተሳልቀው ተዘባብተው በነጻነት ይኖራሉ ።ይሄ ለምን ይመስላችኋል ?

➾ሀገር መሥራቿ ቤተ እምነት በሠራችው ሀገር መኖር አልችል ብላ ስደት ላይ ናት።ስደተኛ ተቀባይዋ አሁን ስደት ላይ ናት። በሐረር ፦ በሱማሌ ፥ በአፋር በጅማ በኬሜሴ በደሴ በነጻነት የመኖር መብቷ የተገደበ እና የተገፈፈ ሁኗል ። ሻሽ ጠምጥሞ ካባ ደርቦ በዓለ መስቀልን በዓለ ጥምቀትን ማክበር እና መውጣት መግባት ስጋት ከሆነ ሰነባብቷል ። ይሄ ለምን ሆነ ?
አሁን ደግሞ በሶሻል ምድያው የራሳችሁ ኡስታዞች እየወጡ ጀግና ካለ ይምጣና ይሞክረን እያሉ ፎከሩ። ሥዕላትን ታቦትን ቅዱሳንን ጣኦት ብለው በመስደብ አከረሩ። በመጣችሁበት የእኛ ወጣቶች ሲመጡ ወገቤን አላችሁ። ይሄ ምን ማለት ነው ?

➾ኡሰታዞቻችሁ ለዘመናት ቅዱሳንን ያረከሱበት ፥ የሰደቡበት ያንቋሸሹበት ቪዲዮ ከእጃችን ላይ ነው እኮ። ያን ጊዜ የት ነበራችሁ ? ምነው እንደ በቅሎ እንጋልባችሁ፤ እንደ ፈረስ እንደጫናችሁ ፦ እንደ ሕጻን እንቅጣችሁ አላችሁንሳ ?

➾ እኛ ሥጋዊ ሞትን የሚፈራ አማኝ የለንም። ምክንያቱም ሞት በእኛ ሃይማኖት ከሞተ ቆይቷል።ብንኖርም ብንሞት ለእግዚአብሔር ነው። ስለዚህ እንከባበር። ከእናንተ ቤት የተጫረው እሳት ከእኛም ቤት አለ ።ልጆቻችሁን አሳርፉ ➾።ልጆቻችን እናሳርፍ ።ከዚህ ውጭ እናንተ ዝም በሉ እኛ እንስደባችሁ ከማለት የበለጠ ጋጠ ወጥነት የለም። ጥጋባችሁን በልክ አድርጉት። መኖር ቢያቅተን መሞት አያቅተንም።ምክንያቱም መሞት ለእኛ መኖር ነውና።

➾እፎይ➾" የተባለውን ወጣትም ሆነ የትኞቹንም
ወጣቶች ማሳደድን አቁሙ። ሌላ መዓት በምድሪቱ ላይ እንዳታመጡ። ይሄ የእናንተ ውሳኔ ነው ። እስቲ ስድብ ከሆነ ችግሩ ስድብም ሆነ ሰዳቢም እንቋጠር ።ስንት ኡስታዝ በዚች ቤተ ክርስቲያን ላይ አፉን ከፈተ ? ስንቱ የስድብ የነቀፋ ድርስት ደረሰ ? ዝም ማለታችን ሳናውቅ ቀርተን መሰላችሁ እንዴ ? እንከባበር ።
ለማንኛውም ቤ/ክርስቲያናችን ትወዳችኋላች። ፍቅሯን ገፍታችሁ ከመጣችሁ ግን የአጼ ካሌብ ልጅ ፤ የግርማ ስዩም እና የጠጠውድም፥ የአጼ ቴዎድሮስ እና የአጼ ዮሐንስ ልጆጅ መሆናችን ለመጨረሻ ጊዜ እንነግራችኋለን። በፍጥነት አስተካክሉ ። ሌላ ቦታ ላይ ክብሪቱ ሳይጫር መልስ ስጡ ። የሚስተካከልን አስተካክሉ ። ይህ የወንድሞቻችሁ የኦርቶዶክሳውያኑ ድምጽ ነው። የፈሲታ ተቆጢታ አትሁኑ ። ይሁን እንጅ ይህንንም ሁሉ እያደረጋችሁን በክርስቶስ ፍቅር እንወዳችኋለን።ምክንያቱም ሃይማኖታችን ጠላቶቻችሁን ውደዱ ይለናልና ። እናንተም መውደድ ባትችሉም እንኳን፤ በሕጋችሁ መውደድ ባይኖርም እንኳን ለሕሊናችሁ ብላችሁ አታሳዱን ማቴ 5 ፥45

ነገር ግን የፈሲታ ተቆጢታ አትሁኑ። ይሄ የግፍ ግፍ ነው ።


መለያየትን የሚያነሣ ሰው ጠማማ እንዲሆን በራሱም ላይ ፈርዶ ኀጢአትን እንዲያደርግ ዐውቀህ፥አንድ ጊዜ ሁለት ጊዜም ከገሠጽኸው በኋላ እንዲህ ከሚመስል ሰው ራቅ ።
ወደ ቲቶ 3:11


ከ142 በላይ ንፁሃን በፋግታ ለኮማ ወረዳ ተጨፍጭፏል!

የብልፅግና አሸባሪ ሃይል ወደ አማራ ክልል ከገባ ጀምሮ በአንድ ወረዳ ብቻ ከ142 በላይ ንፁሃንን መጨፍጨፉን አረጋግጠናል። በትናንትናው ዕለት ብቻ ህፃናትን ጨምሮ ከ4 በላይ ንፁሃንን በአዊ ዞን ፋግታ ለኮማ ወረዳ የተጨፈጨፉ መሆኑን በአካል በመገኘት አረጋግጠናል። አማራን ሊያጠፋ የመጣን አሸባሪ ሃይ መደምሰስና ማሸነፍ ግድታ ነው።

መረጃው የአማራ ፋኖ በጎጃም ነው!


እምየ ተዋህዶ Emye Tewahedo dan repost
የሆነ ጊዜ በስልጤ ክርስቲያኖች ላይ ስለተፈፀመው ግፍ ከራሳቸው አፍ የመስማት አጋጣሚ ነበረኝ።
ያ ሁሉ ግፍና መከራ መነሻው "ጎንደር ላይ ሙስሊም ተገፍቷል" የሚል እንደነበር ሁላችንም እናውቃለን።
ታዲያ በዚህ ሰበብ በወራቤ ከተማ ላይ በክርስቲያኖች ላይ የተፈፀመው ነገር እጅግ አስቀያሚ ነው። እዚያ ያሉት ክርስቲያኖች ስለተባለው ነገር የሚያውቁት ነገር የለም።
በቀጥታ የከተማው ፖሊስና ሚሊሻ አጅቧቸው የሩፋኤል ቤ/ክንን ጋዝ አርከፍክፈውበት፣ በሩን ሰው መጥቶ እንዳይከላከል አድርገው፣ በይፋና በግልፅ አነደዱት።
ምናልባት የወራቤ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች መጥተው እንዳይከላከሉ ብለው በቀጥታ የዩንቨርስቲውን በር በፖሊስ ዘግተውባቸው በተቀናጀ መልኩ አቃጠሉት።

ይህ ሁሉ ሲፈፀም የመንግስት ፖሊስና የከተማው አስተዳደር ሰዎች የሚያውቁትና በበላይነት ያስተባበሩት ጉዳይ ነው። ስማቸውና መልካቸውም ዛሬ ድረስ የሚታወቅ ግልፅ ሰዎች ነበሩ።

ነገሩ በፍርድ ቤት ተይዞ እየተንከባለለ ያለ ጉዳይ ቢሆንም እስከ ዛሬ የወራቤ ክርስቲያኖች ኢምንት ፍትህ አላገኙም። ይልቁንም የተቃጠለባቸውን ቤ/ክ መልሰው ለማሰራት እንኳ አቅቷቸው ለልመና ደጅ ከወጠ ስንት ዘመናቸው!
በከተማው ይኖሩ የነበሩ ክርስቲያኖችን ያ ግፍ ትራውማ ፈጥሮባቸው የገዛ ቤታቸውን በርካሽ ሽጠው ወደ ቡታጅራና ሎሎች ከተሞች ተሰደዋል። የቀሩት ክርስቲያኖች ግን ከዚያ ስብራት እስካሁን ማገገም አቅቷቸው አሉ።

እንግዲህ የሰውን ሃይማኖት ማክበርና ፍትሐዊ ሕሊና ይህንንና መሰል እልፍ ግፎችንም ማየት ይጠይቃል። የተበዳይነት ገፀ-ባህርይ ተላብሶ መገኘት የትም አያደርስም። ሞልቶ የፈሰሰ ብዙ ግፍ ተሸክሞ እያኖረ ያለ ሌላም አካል ስለመኖሩ ደጋግሞ ማሰብ መልካም ነው።

ዲ/ን አክሊሉ ደበላ


‎★ ይድረስ ለእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ★

★ እናንተ ቤት የምትለኩሱትን እሳት እንዴት ታዩታላቹ ?

★ሼር በማድረግ አድርሷቸው ★

ሰሞኑን በቲክቶክ ፕላቶ ፎርም በእስልምናና በክርስትና መጻሕፍት ዙሪያ በሚወያዩ ወጣቶች የተነሱ ጥያቄዎችን መሠረት በማድረግ ከሙስሊም ወገኖች ለምን ተጠየቅን በሚል ግልፍተኝነት ጉዳዩን ከቲክቶክ ወደ ተቋማዊ ጉዳይ ከፍ አድርገውታል እኛ ዝምያልነው የቲክቶክ ጉዳይ ነው ብለን ነበር።እናንተ በተቋም ደረጃ ካመጣችሁት እኛም ጥያቄ አለን።

‎አንዳንድ ኢስላም ወንድሞችና ኡዝታዞች ክርስትናን በኢስላሞች ዘንድ የተጠላ ለማድረግ በሌላ በኩል ደግሞ ክርስቲያኖችን ወደ እስልምና ለመውሰድ በርካታ ክብረ ነክ መፅሐፍትን ጽፈዋል፣ እየፃፉም ይገኛሉ።

‎ክርስትናን ከእስልምና እያነጻፀሩ እጅግ በሚያስነውር መልኩ ከሚጽፉትና የክርስቶስን አምላክነት ከሚፃረሩት መካከል ቀዳሚዎቹ ቀመር ሁሴንና ኡዝታዝ አቡ ሃይደር ይጠቀሳሉ። አቡ ሃይደር "ላለመደናገር ማመሳከር" በሚል መጽሐፉ ክርስትናን በማጥላላት፣ ክርስቶስን ፍጡር በማድረግ ነውረኛ ጽሑፍ ፅፏል። በየዩቲዩብ የሚናገረው ፀባ ጫሪ ንግግሩና ደም አፋሳሽ የሽብር መልዕክቱ በስፋት ተሰራጭቷል።

‎ሸይኽ ሐሰን ታጁ "ሰይፉን ፍለጋ" እና "የኀመረ-ኖህ ቅጥፈት በእስልምና እውነት" የሚሉ ድርሰቶችን በመፃፍ በክርስትናውና እስልምናው መካከል ልዩነቶች እንዲሰፉና መከባበር እንዲያከትምለት የድርሻውን አበርክቷል። አሁንም ድረስ ለስሙ አምባሳደር ተብሎ ተቀምጦ ከፍተኛ የሽብር ተግባራትን ውስጥ ለውስጥ እንደሚሰራ ተደርሶበታል።የመንግስትን ፓሊስ ከማስፈጸምና ሃገራዊ ሥራዎችን ከመሥራት ይልቅ ጽንፈኝነት በማባባስና የሽብር ወላፈን በማቀጣጠል የተጠመደ መሰሪ ሰው በመሆኑ መንግሥት እርምጃ ውሳኔ ሊያስተላልፍበት ይገባል።

‎ዶ/ር እንድሪስ የተባለ ሰውም የቁራኑ ኢሳና የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ ክርስቶስ የተለያዩ ቢሆኑም "ኢየሱስ የኢስላም ነቢይ" የሚል ክብረ ነክ መፅሀፍ አሳትሞ አሰራጭቷል። በክርስቲያኖችና በሙስሊሞች መካከል ከፍተኛ ፀብ፣ጥላቻ፣አምቧጓሮ እንዲፈጠር አድርጓል።

‎አሁን ላይ በክርስቲያኖችና ኢስላሞች መካከል ሰፋፊ የመለያያ አጥሮች በማስቀመጥና ከፍተኛ የጥላቻ መርዝ በመርጨት የሚታወቀው አህመዲን ጀበልም "303 ጥያቄዎች ለክርስቲያኖች" የሚል ድርሰት ፅፎ ተገቢው መልስ ተሰጥቶታል። ዋሂድ እና ኤልያህ እንዲሁም ሰልማን የተባሉ አክቲቪስቶችም የየራሳቸውን መጽሐፍ ፃፉ ርካሽ የሆኑ ቃላትን በመጠቀም ከፍተኛ ደም አፋሳሽ ቅስቀሳዎችን አደረጉ ።

‎እኒህ ከላይ የጠቀስናቸው ግለሰቦችና መጻሕፍት ክርስትናን ለማጥላላት፣ክርስቲያኖች ላይ ግድያ ለማምጣት የተጻፉና የሰበኩ ናቸው። በስብከት ደረጃ ደግሞ እጅግ ብዙ ኡዝታዞችንና አክቲቪስቶችን መጠቃቀስ ይቻላል። ለዓመታት ደም ደም የሚል ንግግሮችንና ፀባ ጫሪ መልዕክቶችን ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። ይህ ሁሉ ሲሆን ክርስቲያኖች በመጽሐፍትም በማህበራዊ ሚዲያ መድረኮችም ለተነሱ ጥያቄዎች በራሳቸው ድንበር ላይ ሆነው በቂ ምላሽና ማብራሪያ ከመስጠት በስተቀር እስልምናን የሚነካ አንዳች ነገር አልተናገሩም።

‎ አክራሪዎች የፃፏቸው መጽሐፍትም ሆኑ ድርሰቶች በሙስሊሞችና በሌላው እምነት ዙሪያ ያስገኙት ጥቅም የለም። ይልቁንም የመለያያ ድልድይ ሰሩ እንጂ። በሁለቱም ዘንድ የነበረው ጥላቻ እጅግ እንዲያይል እና ሁሉም ራሱን ከመከላከል ወጥቶ ወደ ማጥቃት እንዲሸጋገር በር ከፍቷል።

‎አክራሪ ፀሐፍት ያስገኙት ጥቅም ቢኖር ክርስቲያኖች እምነታቸው ላይ እንዲጣበቁና እንዲያውቁ ብቻ ነው። ሃይማኖት ለማስለወጥ የተፃፉ የጥላቻ መጽሐፍት ሃይማኖትን አጥብቆ የሚይዝ ወጣት እንዲፈጠር፣ ሞጋችና ሌላውን ጠያቂ ክርስቲያን እንዲበዛ አድርገዋል።

‎የራሳቸውን እምነት በቅጡ ተርጉመው ያላስተማሩ አክራሪያን የማያውቁትንና በአግባቡ ያልተረዱትን መጽሐፍ ቅዱስ ሚሊየን ጊዜ ለማብራራት ሞክረው አልተሳካላቸውም። ክርስትናን ለቆ ኢስላም የሆነም በታሪክ አጋጣሚ አላገኙም።በገንዘብ እየተደለሉ ኑሮን ለማሸነፍ ሃይማኖቴን ለወጥኩ የሚሉት እነርሱ የድራማ ተዋናዮች ስለሆኑ በንቀት እናልፈዋለን።

‎አሁን ለፈተፈቱት ጉዳይ በልካቸው እየተሰፈረ ሲመለስላቸው እሪታና ዋይታ፣ ሰላማዊ ሰልፍና ዛቻ ጀመሩ። ምን ጠብቀው ኖሯል? ድሮ ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ! ድንበር ዘለልነት የመጨረሻ ጣጣው ይህ ነው።

ሙስሊሞች አንድ እውነት ተረዱ ዘመኑ የዕውቀትና የመረጃ ዘመን ነው ወጣቱ ትውልድ ቁርዐኑንም ሆነ ሐዲሳቱን በሚገባው ቋንቋ እየተረጎመ መመርምር የሚችልበት ዘመን ላይ ነው ያለነው።ከራሳቹ መጽሐፍ ለምትጠየቁት ጥያቂ በቂና አሳማኝ መልስ መስጠት እንጂ ኡኡኡ ያዙኝ ልቀቁኝ የሚለው የሜዳ ላይ ጩኸት ጥያቄዎችን አያሳቆምም ትውልዱ ከእንግዲህ በአረብኛ ብቻ የተጻፈ ጽሑፍ አይቶ አሜን ብሎ አይቀመጥም በየቋንቋው ስለተተረጎሙ እያንዳንዱን መጽሐፍት እያራገፈ መጠየቁን ይቀጥላል።አንድ ግለሰብ ላይ ስትዘምቱ ሺዎች ተፈጥረው እንደሚያድሩ ዕወቁ።
መ/ር ታሪኩ አበራ


እየመታሽ ጩኺ


"...እያጠቁ እንደተጠቁ ለማስመሰል፣እየናቁ እንደተናቁ ሰዎች እንዲረዷቸው ፣እየሰደቡ በስድብ የጎበጡ እንዲመስሏቸው እየመቱ እና እያጠቁ ነገር ግን ድምጻቸውን ከፍ አድርገው ይጮኸሉ። የእነርሱን ምት እንዳይገንባቸው እየመቱ ይጮኸሉ።

ከእስልምና እምነት ተከታይ ትላልቅ መምህራን እስከ ማኅበራዊ ድኅረ ገጽ ተጠቃሚ ድረስ በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ የንቀት እና የስድብ ስብከት ሲሰብኩ "እኝን ተው በላቸው " ያለ አንድም የለም።

ኢየሱስ ከንፈር ስሟል፣ ኢየሱስ እብድ ነው።ጳውሎስ ይቃዣል
ኢየሱስ ሞኝ ነው፣ እግዚአብሔር ትውስታውን የተነጠቀ አምላክ ነው ፣ እግዚአብሔር ሚስት የሚይዝ ነው ....ወዘተ ብለው በመጽሐፍ በድምጽ እና በቪዲዮ እነርሱ ሲለቁ የሚናጋ ሀገር የለም።

ሌላኛው ወጥቶ ግን የእነርሱን መንገድ በሚመስል ጎዳና በግልጥ ሲናገር ከአምባሳደር እስከ ዱርአደር ይነሳል።

አንደኛው ሲያደርግ ጽድቅ ሌላው ሲፈጽመው ኩነኔ የሚመስል ተመሳሳይ ግብር ካለ ከሁሉም ይወገድ።"

Kune Demelash kassaye -Arba Minch


"ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጧልና ፤
ይህም ጸጋ ኀጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኀኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፤
ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል ባሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል ።"
ወደ ቲቶ 2:11-13


"የቤተ ክርስቲያን ህልውና ሆነም ቀረም ተስፋው ያለው ከምእመናን እና ከእግዚአብሔር ብቻ ነው።"

በድሎት ብዛት የተኛው ቤታችን ለአጥፊዎች ቸር ይሆናል ለመልካሞች በመመሪያና በመክበስበስ የታጠረ ነው።

ማህበራቱም የጥፋት ሥርዓቱ እንዳይተችባቸው ወገባቸውን ታጥቀው እያገለገሉት ስለሆነ የሰልፍ ድጋፍ ማድረግ ብቻ ነው የቀራቸው።
ወጣ ብለው ቀድመው የተረዱትንም ጠልፈው ሽባ አድርገው ያስተኟቸዋል።
የቤተ ክርስቲያን ህልውና ሆነም ቀረም ተስፋው ያለው ከምእመናን እና ከእግዚአብሔር ብቻ ነው።

ከምሥሪቀ 🌞 ጉባኤ ቤት ገጽ


"በኦርቶዶክሳዊያን ላይ የተከፈተ ወንጌላዊ ጦርነት"ነቢያተ ዓቢይ


"ይህን ጦርነት እንደማሸንፍ ኢየሱስ ስለነገረኝ ነው..."ዓቢይ

https://youtu.be/Sv_6YmGTri0?si=NCRSRnpTwVX97aRH


Zemedkun Bekele (ዘመዴ) dan repost
ጠያቂው ተጠየቅ እንጂ…!

"…ክርስቶስ ማነው…? በሚል 303 ጥያቄዎች አሉኝ ብሎ እሱ በማያምንበት ለእኔ ግን ጌታዬ አምላኬና መድኃኒቴ በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ጥያቄ አቅርቧል። በመጽሐፍ መልክም አሳትሟል። መልካም መብቱ ነው። አሕመዲን ጀበል በጌታ ላይ ተሳልቋል፣ በምስጢረ ሥላሴ ላይ አሹፏል፣ ቀልዷል ብለን ሰልፍ አልወጣንም። ይገደልም አላልንም።

"…አሕመዲን ጀበል በኢየሱስ ክርስቶስ ስለማያምን የፈለገውን የመጻፍ መብት አለው ከተባለ እፎይም ሆነ እኔ ስለማላምንበት ስለ መሀመድ ብጽፍ ለምን ትናደዳለህ? አንተ የእኔን በመናቅህ ዝም እንዳልኩህ እኔም የአንተን ስንቅ ዝም ማለት ነው እኮ ያለብህ። አንተ የእኔን ድንበር አልፈህ ለማዋረድ ስትሞክር እኔ በድንበሬ ላይ ቆሜ የአንተን ባዋርድ ለምንድነው ጎረቤት ሁላ እስኪረበሽ የምትንጫጫው። አንተ "ለነቢይህ" ፍቅር፣ አክብሮት፣ ውዴታ አለኝ ካልክ እኔ ለአምላኬና ለመድኃኒቴ ለኢየሱስ ክርስቶስ ምንም ዓይነት ፍቅር፣ መስዋዕትነት የማልከፍል ይመስልሃል?

"…ንጽጽር ብለህ ያለ አቅምህ መጽሐፍ ቅዱስ ትንተና የጀመርከው አንተው ራስህ ነህ። አንተ የማታውቀውን መጽሐፍ ቅዱስ ገልጠህ ስትዳክር ዝም ብለን ቆይተን፣ መልስም ከዚያው ከመጽሐፍ ቅዱስ ስንሰጥህ ከርመን፣ አይ ቆይ እስኪ ለምን ደግሞ ከቁርዓኑና ከሐዲሱ መልስ አንጠይቃቸውም ብለን ስንነሣ ቆንጨራ ይዞ መፎከር ምን የሚሉት ነው? ወይ አስቀድሞ አለመፎከር፣ አቅምን ዐውቆ መኖርም ጥሩ ነው። ግጠመኝ ካልክ በኋላ አንተ በእኔ መጽሐፍ ቅዱስ ልትሞግተኝ ስትመጣ፣ እኔ ደግሞ በአንተው ቁርዓን ልሞግትህ ስነሣ የምን መነጫነጭ ነው?

"…በመስታወት ቤት የሚኖር ሰው የድንጋይ ውርወራ ጠብ ውስጥ ፈጽሞ አይገባም። ባለጊዜ ነን ተብሎ እንደ ሕጻን በልቅሶ፣ በጩኸት ፍላጎትን ለማሳካት መሯሯጥ ያስገምታል።

• እፎይ…!




"የቆምንለት አላማ ሀይማኖታችንን መጠበቅና የሀገራችንን ሉዓላዊነት ማስከበር የአርበኞች የአባቶቻችንን እና የቅዱሳኑን አደራ መወጣት እስከሆነ ድረስየድርሻችሁን እንድትወጡ ትኩረታችሁንም በዚህ ታላቅ ገዳም ላይ እንድታደርጉ በቅዱሳኑ እና ነጻ ሀገርና እምነት በአጥንትና በደማቸው ባስረከቡን በአርበኞቻችን ስም አሳስባችኋለሁ።"

    በደብረ አልያስ ወረዳ የሚገኘው የብሔረ ብጹአን አጼ መልክዓ ሥላሴ አንድነት ገዳም  ከባድ አደጋ ላይ ነው።ሃይማኖትን ማውደም ተቀዳሚ ተግባሩና የተነሳለት አጀንዳው የሆነ የጨፍጫፊው የሂትለራዊው መንግስት ዙፋን ጠባቂ የመከላከያ ሰራዊት ታላቁን የብሔረ ብጹአን አጼ መልክዓ ሥላሴ አንድነት ገዳምን ለማውደም በዛሬው እለት  በየካቲት 30/2017 ዓ.ም በሦስት አግጣጫ በመዝመት የገዳሙን መግቢያ ሁለት የተራራ በሮች በመክበብ ላይ ይገኛል።

     በየካቲት 28/2017 ዓ.ም ከሁለት ቀን በፊት ገዳሙን ለመደብደብ ስትራቴጅክ ቦታ ወደሆነው ምችግ የተራራው ጫፍ እንደደረሰ ለሚዲያ አካላት ማድረሴ ይታወቃል ።በዚህ አያይዤም የበረኸኛው ቀስተደመና ብርጌድ ፋኖዎች ወደ ገዳሙ ላለማስወረድ በምችግ አፋፍ እንደተዋደቁና ጠላትን በእጅጉ በመምታት ጉዞውን እንደገቱት ገልጫለሁ። ከባድ መሳሪያ zu 23 እና መድፍ አስከትሎ ወደጓይ የመጣውን ተጨማሪ የጠላት ሀይል በየጠንጠር እና በጅረሰብ ግንባር የተዋጉት ቀስተደመናዎች እና የበላይ ዘለቀና የበረኸኛው ጅበላ ሙተራ ብርጌድ ደብረ ኤልያስ ከተማ በመግባት እቅዱን በማክሸፋቸው ጠላት መመለሱን መግለጼ ይታወቃል።

   በዛሬው እለት በየካቲት 30/2017 ዓ.ም ግን ይህ ሀይማኖትን አጥፊው የወንበዴ ስብስብ ሀይሉን በእጥፍ በማጠናከር  በከባድ መሳሪያዎች በመታገዝ ወይም በመታጀብ በጎፍጭማ:በመጋል ቡሬ እና በጓይ ቀበሌ አድርጎ አስፍቶ በመጓዝ  የገዳውን መግቢያ የተራራ በሮች ለመያዝ ተቃርቧል።

ውድ የአማራ ፋኖዎች!! ውድ ኢትዮጵያውያን!! ውድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኞች!! ሊያውቁልን ይገባል በድጋሚም የማሳስበው በጥብቅ እንድታወግዙና የተቃውሞ ድምጻችሁን እንድታሰሙ ሲሆን በአቅራቢያችን ያላችሁ የፋኖ ሀይላትም የቆምንለት አላማ ሀይማኖታችንን መጠበቅና የሀገራችንን ሉዓላዊነት ማስከበር የአርበኞች የአባቶቻችንን እና የቅዱሳኑን አደራ መወጣት እስከሆነ ድረስ የድርሻችሁን እንድትወጡ ትኩረታችሁንም በዚህ ታላቅ ገዳም ላይ እንድታደርጉ በቅዱሳኑ እና ነጻ ሀገርና እምነት በአጥንትና በደማቸው ባስረከቡን በአርበኞቻችን ስም አሳስባችኋለሁ።

     ውድ የፋኖ ሀይላት ትላንትና  በተናጠል  እነ አሳምነው ጽጌን የመሳሰሉ የአማራ ሕዝብ ጠበቃ ጀግኖቻችንን የበሉ እና ብዙ ገዳማትን ዋልድባን ብሔረ ብጹአንንና መስጊዶችን ወዘተ ያወደሙ ባለመደራጀታችን ነበር ።

      ዛሬ ግን ፋኖ በዚህ ልክ የምስራቅ አፍሪካን ጅኦ ፖለቲክስ ሰላም ያስከብራል ተብሎ የተነገረለት ታላቅ ተቋም በኮርና በእዝ በክፍለጦር ተቋቁሞ ባለበት እና በተደራጀንበት ሰዓት ይህ የትውልዱ ተምሳሌት የሆነው ታላቅ የብሔረ ብጹአን አጼ መልክዓ ሥላሴ አንድነት ገዳም በነዚህ አጥፊዎች እንዳይወድም እና በመዘናጋት ምክንያት ዘመን የማይሽረው ስህተት እንዳንሰራ ታሪክ እንዳይወቅሰን እንድናስብበት አደራየ የይድረሳችሁ።

     እናንተም ውድ የሚድያ ባለሙያወች ትኩረት ሰጥታችሁ ይህን ታለቅ ገዳም ለመታደግ እንድትረባረቡና የኢትዮጵያዊነት ግዴታችሁን እንድትወጡ አደራየ ይድረሳችሁ።

                    ትኩረት!!!!!
ለታላቁ የብሔረ ብጹአን አጼ መልክዓ ሥላሴ አንድነት ገዳም!!!!

   
የአማራ ፋኖ በጎጃም የቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሤ 6ኛ ክ/ጦር የበረኸኛው ቀስተ ደመና ብርጌድ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ዘላለም ዘሪሁን ገልጿል ።

የካቲት 30/06/2017 ዓ.ም




ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን) dan repost
"ገንዘብ ባይኖር፣ ጥቅም ባይኖር፣ ክብር ባይኖር ቤተ ክርስቲያን የሚመጣ ካህን በጣም ጥቂት ብቻ ነው። አገልግሎቱ ላይ ገንዘብና ጥቅም ተጣብቆበት ነው መከራ የምናየው። ጥቅም እንጀራ ባይኖር ቤተ ክርስቲያንን ለሕይወት የሚፈልጋት ጥቂት ነው፣ ጳጳስ መኾን የሚፈልግ የለም። መስቀል ለመሸከም ማንም አይፈልግም"

ንዋይ ካሳሁን


#በዓለ_ቤተ_ክርስቲያን
#ምኵራብ
ሠናይ ሰንበት🙏
• መነሻችን፦ አእምሮ ጠባዕይ፣ ሕገ ልቡና
• በሕገ ኦሪት ፦ ደብተራ ኦሪት፣ ምኩራብ/ቤተ መቅደስ፣
• በሐዲስ ኪዳን፦ ቤተ ክርስቲያን፣
• መጨረሻችን፦ መንፈሳዊ አእምሮ፣ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት፡፡

[ ] ጥሬ ትርጉም:- ምኵራብ ማለት መሰባሰቢያ/ማምለኪያ/መስገጃ ማለት ነው ፡፡

[ ] Definition:- Synagogue is a congregation or assembly of Jews met for the purpose of worship, or the performance of religious rites.
(Chambers's Twentieth Century Dictionary)

[ ] ለመጀመሪያ ጊዜ ምኩራብ የሚለው ቃል ጥቅም ላይ መዋል የጀመረው እስራኤል መቅደሳቸው ፈርሶ ወደ ባቢሎን ከፈለሱ በኀላ ነው፤ በየሰፈራቸው በሚቀርባቸው ስፍራ አምልኮትን የሚፈጽሙባቸውን ቤተ ጸሎት ሰርተው ምኩራብ ብለው ይጠሩ ነበር፡፡
The synagogue first came into prominence in the religious life of the Jewish people during the exile, and, since the destruction of the temple and the dispersion of the Jews, constitutes their customary place of worship.
(Chambers's Twentieth Century Dictionary)

[ ] አምልኮት የተጀመረው በመላእክት ሀገር በመላእክት አእምሮ ነው፡፡
የአምልኮ ማረፊያ መነሻውም ሆነ መድረሻው አእምሮ ነው፤ እግዚአብሔር ልባችንን/አእምሯችንን አጥብቆ የሚፈልገው ለዚህ ነው፡፡
የሚመች አገልግሎት ያለው አእምሮ ውስጥ ነውና፤ሮሜ 12:1፡፡
ወደ ሰው ስንመጣ ደግሞ ለአምላክ ለመገዛት የተሰጠን የመጀመሪያው ሕግ የተቀረጸው በጽላት አልነበረም በአዳም የልብ ሰሌዳ ላይ እንጂ፡፡
ከአዳም ቀጥለው የመጡ አበውም እስከ ሙሴ ድረስ በዚሁ ሕግ (በሕገ ልቡና) ተመርተዋል፡፡

በዘመነ ሙሴ እግዚአብሔር ሕግን በጽላት ቀርጾ ሰጠ፤ ለጽላቱ ማንበሪያ ታቦቱን ፤ለአምልኮው መፈጸሚያ ድንኳን እንዲሠራ ለሙሴ ባሳየው መሠረት ሠሩ ፤ ዘፀ 25:40፡፡

ይህ ሲያያዝ ከሰሎሞን ደረሰ፡፡
ሰሎሞን የመጀመሪያውን ቤተ መቅደስ በድንቅ ሁኔታ ሠራ፤1ነገ 8:1-11፡፡
ይህ መቅደስ ወደ ባቢሎን ሲማረኩ ተቃጠለ፤2ዜና መዋ 36:17-22፡፡

ሁለተኛው ቤተ መቅደስ በዘሩባቤል ተሠራ፤ዕዝ 3፡2፡፡
ይህም መቅደስ ሲሠራ 46 ዓመት የፈጀ ነው፤ ሄሮድስ ወልደ አንዶፊር አሳምሮ አድሶት ነበር ፤ዮሐ 2:20፡፡

ጌታችን ያስተማረበት፤ ተአምራት ያደረገበት ይህ መቅደስ ነው፡፡በዚህ መቅደስ፦
• በ12 ዓመቱ ከሊቃውንት ጋር ተቀምጦ ተገኝቶበታል ፣ ሉቃ 2:46::
• እድሜው 30 ዓመት ከሆነ በኀላ በብዛት አስተምሮበታል፣ ሉቃ 21:37::
• በአህያ ተቀምጦ ለየት ያለ ምልክትን አሳይቶበታል ማቴ 21:1-18
• ነጋዴዎችን በጅራፍ አባሮበታል ዮሐ 2:16
• በዕለተ ዓርብ መጋረጃውን ለሁለት ከፍሎታል፣ማቴ 27:51፤ማር 15:38፡፡
ይህ የአይሁድ ምኩራብ በኢየሩሳሌም የሚገኘው ዋናው ይሁን እንጂ በምድረ እስራኤል ብዙ ምኩራባት መኖራቸው ግልጽ ነው፡፡
ይህም ምኩራብ ከጌታ ልደት ወዲህ በመጀመሪያው ክ/ዘመን በ70 ዓ.ም በሮሙ ንጉሥ በጥጦስ አገዛዝ ፈራርሷል፡፡

[ ] ጌታችን ይህንን ምኩራብ ያጸዳበት ምክንያት
1. በወቅቱ የነበሩ ከሊቃነ፡ካህናቱና ከምኩራቡ ሹማምንት ጀምሮ እስከ ሕዝቡ ድረስ ያሉት ምኩራብን ለንግድ ዓላማ በማዋል ይቀልዱበት ነበር ፤ አምልኮቱን ዘንግተው፤ ሥርዓተ መሥዋዕቱን ትተው የሰባውን የወፈረውን በግ ፤ የጠራውን የነጠረውን ወርቅ ለራሳቸው እያስቀሩ ፤የከሳውን የጠቆረውን በግ እና የማይረባውን ወርቅ ለእግዚአብሔር እያሉ ይሳለቁ ነበርና ነው፡፡ ለዚህም "የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት" በማለቱ ይታወቃል፤ዮሐን 2 : 16፡፡

2. ሥርዓተ ኦሪት መሥዋዕተ ኦሪት ማለፉን ለማሳየት:-
በመቅደሱ ዙሪያ የተደረደሩት እንስሳትና አርጋብ ለመሥዋዕትነት የሚሸጡ ናቸው፤ ይሁን እንጂ ከአሮን ጀምሮ ሲታረዱና ሲቃጠሉ ቢኖሩም ዘለዓለማዊ መዳንን ማምጣት አልቻሉም፤ ስለዚህም ክርስቶስ የእንስሳትን የአርጋብ መሥዋዕት በቃ! መሥዋዕት ሆኜ የምቀርበው እኔ ነኝ ሲል እንስሳቱን አስወጣቸው፡፡

3. ሰውነታችንን ንጹሕ እንድናደርግ፦
የከበረው የሰው ልጅ ማንነት የእግዚአብሔር ማደሪያ መሆን አለበት፤ ይህ እንዲሆን ደግሞ
• እንስሳዊ ጠባይ
• ፍቅረ ንዋይ
• የመንፈስ ቅዱስ ጸጋን መሸጥ
እነዚህን ተግባራት ማስወገድ አለባችሁ፤ ክቡር ማንነታችሁን ለሌብነት፤ለወንበዴነትና ለአስመሳይነት አትጠቀሙበት ሲለን ነው፡፡

[ ] የምኩራቡ ፍጻሜያዊ ትርጉም
የምኩራብ ፍጻሜ ትርጉም ቤተ ክርስቲያን ናት
ይኸውም ሊታወቅ ክርስቶስ በተሰቀለ ጊዜ የምኩራቡ መጋረጃ ተቀዷል፤ ይህ ደግሞ የሦስተኛው ቤተ መቅደስ(ቤተ ክርስቲያን) መመሥረት ብሥራት ነው፤ሉቃ 23:45፡፡
• የአይሁድ ምኩራብ ታቦት የለውም ቤተ፡ክርስቲያን ግን ታቦትም ናት ታቦትም አላት
• የምኩራብ መሠረት ሕገ ሙሴ ኦሪት ሲሆን የቤተ ክርስቲያን መሠረትና ራስ/ጉልላት ግን ራሱ ክርስቶስ ነው፤ኤፌ 2:20፤5:23 ፡፡

[ ] ምኩራብና ቤተክርስቲያን በሊቃውንት ሲነጻጸሩ
• "እስመ መጽሐፍሰ ለምኩራብ ወተዐውቆ ለቤተ ክርስቲያን-----ትንቢት ለምኩራብ ሃይማኖት ለቤተ ክርስቲያን ነውና"፡፡

• "ምኩራብ አነመት ፀምረ ወቤተ ክርስቲያን ተዐጽፈቶ-----ምኩራብ ሸመነችው (ትንቢቱን ሱባዔውን) ቤተ፡ክርስቲያን ለበሰችው/ተጎናጸፈችው"፡፡

• "ምኩራብ አጸረት አስካለ ውስተ ምክያድ ወአሕዛብ ሰትዩ ስቴ ምሥጢር ------ምኩራብ/ቤተ አይሁድ የወይን ፍሬን በአውድማ ረገጠች/ጨመቀች አህዛብ (ምእመናን) የምሥጢር ጽዋውን ተጎነጬ"፡፡
ሃይ.አበ ዘዮሐ.አፈወርቅ፤ 66:21-23፡፡

ስለዚህ ምኩራብ የሚለው ስያሜ ምኩራብ ሰም ሆኖ ቤተ ክርስቲያን ወርቅ ሆና የምትነገርበት፤
የእኛ ሰውነት በወርቅ ፍቅር፣ንጽሕናና ቅድስና ደምቆ አሸብርቆ የሚታይበት ወቅት ነው፡፡
ዋናው በዓልነቱም የቤተ ክርስቲያን ነው፤ ምኩራብ ታስቦ ቤተ ክርስቲያን ግን ከሙሽራዋ ጋር ነግሣ ትኖራለች!!!!!!

እኛም ልባችንን ከፍተን ፤ አእምሯችንን በንስሐ አጥበን
• " የምሕረት አምላክ ሆይ ግባ"
• "የቸርነት አምላክ ሆይ ግባ"
• "የይቅርታ ንጉሥ ሆይ ግባ"
ለማለት ያብቃን!!!!!!

መዋዕለ ጾሙን በሰላም ያስፈጽመን!!!

አሜን!!!!

መጋቤ ሐዲስ ነቅዐጥበብ ከፍያለው

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.