ማስታወሻ፡— በአዲስ ኪዳን ውስጥ፥ ሦስት የመንፈስ ቅዱስ ሙላት ዓይነቶች የሚታዩ ይመስላል። በመጀመሪያ፥ በመንፈስ ቅዱስ መሞላት መንፈሳዊ ብስለት ላለው ሰው የተሰጠ አገላለጽ ይመስላል። ለዚህም ምክንያቱ ግለሰቡ አብዛኛውን ጊዜ ለመንፈስ ቅዱስ በመታዘዝ መኖሩ ነው ( የሐዋ. 6፡3)። ምንም እንኳ ሁሉም ክርስቲያኖች በዚህ ዓይነት ሕይወት ባይኖሩም፥ እግዚአብሔር ከሁላችንም ይህንኑ ይጠብቃል። ጳውሎስ በኤፌሶን 5፡18 ስለ መንፈስ ቅዱስ ሙላት የተናገረው ከዚህ አንጻር ነው። ሁለተኛ፥ አዲስ ኪዳን አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሔር ለአንድ ሰው የሚሰጠውን የተለየ የሕይወት ዘመን አገልግሎት ለማመልከት በመንፈስ ቅዱስ መሞላትን ይጠቅሳል። መጥምቁ ዮሐንስ ለነቢይነት አገልግሎቱ ከተወለደ ጀምሮ በመንፈስ ቅዱስ እንደ ተሞላ ተነግሮለታል (ሉቃስ 1፡15-17)። ጳውሎስ የአሕዛብ ሐዋርያ ይሆን ዘንድ በመንፈስ ቅዱስ እንደ ተሞላ ተገልጾአል (የሐዋ. 9፡17)። ሦስተኛ፥ በመንፈስ ቅዱስ መሞላት ማለት አንድ ሰው ድንገተኛ ሁኔታን ለመቋቋም እንዲችል መንፈስ ቅዱስ ሲያስታጥቀው ማለት ሊሆንም ይችላል። ተግባሩ ከተጠናቀቀ በኋላ ይሄ ማስታጠቅ ይወሰዳል። በሐዋርያት ሥራ ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ሙላት በአብዛኛው ያገለገለው በዚህ መልኩ ነው። ጴጥሮስ በሃይማኖት መሪዎች ፊት በቆመ ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ ነበር። እስጢፋኖስ ቀደም ሲል በመንፈስ ቅዱስ እንደተሞላ የተገለጸ ሲሆን፥ ሊሠዋ ሲልም እንደገና ተሞልቷል። ጳውሎስ በምትሐተኛው ላይ የተግሣጽ ቃል በተናገረ ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ እንደ ተሞላ ተገልጾአል (የሐዋ. 4፡8፥ 31፤ 7፡55፤ 13፡9)።]
የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) በቤተ ክርስቲያንህ ብዙ ክርስቲያኖች በቅድስና ለመኖር ከላይ ከተጠቀሱት ነገሮች የሚቸገሩት በየትኞቹ አካባቢ ነው? ለ) አንተስ? ሐ) መንፈስ ቅዱስ በሕይወትህ እርሱን የሚያሳዝን ነገር ካላ እንዲያሳይህ ጠይቀው። መንፈስ ቅዱስ ይቅር እንዲልህና በሕይወትህ የሚገኙትን መጥፎ ልማዶች፥ ጥሩ ያልሆኑ አስተሳሰቦችና ኃጢአቶች የምታሸንፍበትን ኃይል እንዲሰጥህ ጠይቅ።
(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ.አይ.ኤም ከታተመውና የአዲስ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር አገልግሎታቸውን ይባርክ፡፡)
የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) በቤተ ክርስቲያንህ ብዙ ክርስቲያኖች በቅድስና ለመኖር ከላይ ከተጠቀሱት ነገሮች የሚቸገሩት በየትኞቹ አካባቢ ነው? ለ) አንተስ? ሐ) መንፈስ ቅዱስ በሕይወትህ እርሱን የሚያሳዝን ነገር ካላ እንዲያሳይህ ጠይቀው። መንፈስ ቅዱስ ይቅር እንዲልህና በሕይወትህ የሚገኙትን መጥፎ ልማዶች፥ ጥሩ ያልሆኑ አስተሳሰቦችና ኃጢአቶች የምታሸንፍበትን ኃይል እንዲሰጥህ ጠይቅ።
(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ.አይ.ኤም ከታተመውና የአዲስ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር አገልግሎታቸውን ይባርክ፡፡)